Recent Blog Posts - Blog

የመድህን እና የማጓጓዣ ሕግ ይርጋ

ይህ ጽሑፍ በቀጥታ የተወሰደው በፍትሐብሔር ሥነ-ሥርዓት ሕግ የመጀመሪያ ደረጃ መቃዎሚያዎች ከሚለው ተሻሽሎ ከታተመው መጽሐፍ ላይ ነው። ሆኖም ለዚህ የበየነ-መረብ ጽሑፍ ለንባብ እንዲመች በግርጌ ተቀምጠው የነበሩት ማጣቀሻዎች በፅሑፉ ውስጥ እንዲከተቱ ተደርጓል።

በዚህ መጽሐፍ ውስጥ የኢትዮጵያ የንግድ ሕግ አዋጅ ቁጥር 166/1952 ከ50 ዓመታት በላይ ያገለገለ ቢሆንም በከፊል በአዋጅ ቁጥር 1243/2013 የተሸሻለ/የተተካ/ ቢሆንም የድሮው የንግድ ሕግ አዋጅ ቁጥር 166/1952 ውስጥ መጽሐፍ 3 (ሦስት) ማለትም ከአንቀጽ 561 እስከ 714 እና መጽሐፍ 4 (አራት) ማለትም ከአንቀጽ 715 እስከ 967 ያሉ ድንጋገጌዎች ያልተሻሩ ለመሆኑ በአዲሱ የኢትዮጵያ የንግድ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 በመግቢያው አንቀጽ 3(3) ላይ በግልፅ ተደንግጓል። ስለዚህ የንግድ ሕግ ይርጋዎች በአዲሱ ሕግ እና በድሮው ሕግ ያልተሻሩ ድንጋጌዎችን ከሰበር አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ጋር በመጽሐፉ በጥልቀት ተዳሷል።

  1810 Hits

Crypto-currency and Financial Consumer Protection in Ethiopia

In recent years, crypto-currencies have gained popularity across the globe, including in Ethiopia. People use them for various purposes — sending money as gifts, purchasing goods and services, or more commonly, as speculative investments hoping for financial returns. However, while crypto might seem like the future of finance, it comes with real risks — especially for consumers.

  1762 Hits

Why Ethiopia Should Ratify the African Disability Rights Protocol

Introduction

In January 2018, African states gathered in Addis Ababa to adopt the Protocol to the African Charter on Human and Peoples' Rights on the Rights of Persons with Disabilities in Africa (African Disability Rights Protocol). This groundbreaking instrument aims to protect and promote the human rights of persons with disabilities (PWDs) across the continent, aligning with—yet going beyond—the scope of the UN Convention on the Rights of Persons with Disabilities (CRPD).

Although the Protocol came into force on June 5, 2024, Ethiopia has yet to sign or ratify it. This article reflects on the key potential benefits of ratifying the Protocol for Ethiopia and its disability community.

  1056 Hits

በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎች ላይ ትኩረት የሚሹ አወዛጋቢ ነጥቦችና መፍትሔዎቻቸው

ማስታዎሻ፡- ውደ አንባቢያን ይህ ጽሑፍ የተወሰደው በፍትሐብሔር ሥነ-ሥርዓት ሕግ የመጀመሪያ ደረጃ መቃዎሚያዎች በሚል ከታተመው በ2017 ዓ.ም ተሻሻሎ በቀረበው መጽሐፌ ላይ ሲሆን የግርጌ ማስታዎሻዎቹ እና ማጣቀሻዎቹ ለዚህ ጽሑፍ ሲባል ለንባብ በሚመች አግባብ እንደገና ተቀናጅተው ተሰርተዋል፡፡ በዚህ ጽሑፍ የተካተቱት አብዛኛዎቹ ነጥቦች አወዛጋቢ ሆኖም በሕግ ባለሙያው ብዥታ እና ልዩነት የሚፈጥሩ ነጥቦች በመጽሐፉ የመጀመሪያ ዕትም ያልነበሩ አሁን ላይ በችሎት በሚገጥሙ ክርክሮች ሰበር ጭምር መፍትሔ የሰጣቸውን እና ሰበር መፍትሔ ያልሰጠባቸውን ደግሞ የመጽሐፉ አዘጋጅም የራሱን ምልከታ እና መፍትሔ የሚላቸውን ሃሳቦች ያሰቀመጠባቸው ጉዳዮች ናቸው፡፡

  2231 Hits

የተሻሻለው የጸረ ሙስና ልዩ የሥነ ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ አዋጅን ለማሻሻል የወጣው አዋጅ ቁጥር 882/2007 አንቀጽ 3(1) ድንጋጌ ዙሪያ የቀረበ መነሻ የሆነ አጭር የሕግ ማስታወሻ

"In Claris non fit interpretation." (When the text is clear, no interpretation is needed.")

መግቢያ
በዚህ አጭር መነሻ የሆነ የሕግ ማስታወሻ ላይ በተሻሻለው የጸረ ሙስና ልዩ የሥነ ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ አዋጅን ለማሻሻል የወጣው አዋጅ ቁጥር 882/2007 አንቀጽ 3(1) ድንጋጌ ዙርያ የቀረበ ሲሆን፤ በተለይም በዚህ ድንጋጌ ስር ስለተመለከተው የዋስትና መብት እና የዋስትና ክልከላ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ያልተያዙ ሰዎችና የተያዙ ሰዎች ላይ የሚተገበርበትን ሁኔታ የመጀመሪያ ምልከታ ለማድረግ ተሞክሯል። ይህንን የሕግ ማስታወሻ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ዋና ጉዳይ አንድ ደንበኛዬ የሆነ ሰው በሙስና ወንጀል ክስ የቀረበበት መሆኑን ከሌላ ሰው ከሰማ በኋላ ጉዳዩን አጣርቶ የሙስና ወንጀል ክሱ የቀረበበት የሙስና ወንጀል ችሎት ዘንድ ባልተያዘበት ሁኔታ በገዛ ፍቃዱ በቀረበ ጊዜ ችሎቱ የአዋጅ ቁጥር 882/2007 አንቀጽ 3(1) ድንጋጌን መሠረት በማድረግ በቂሊንጦ ማረፍያ ቤት ሆኖ ጉዳዩን እንዲከታተል ሲል በቅርቡ የሰጠው ትእዛዝ ነው።

  1503 Hits

በግልግል ዳኝነት አዋጅ መሠረት የእግድ ትእዛዝ አፈጻጸም

አዋጅ ቁጥር 1237/2013 የግልግል ዳኝነትና የእርቅ አሠራር አዋጅ የሚል ርዕስ ተሰጥቶታል፡፡ የአዋጁን ሰፊ ድርሻ የሚወስደው በግልግል ዳኝነት ሂደት ላይ ስላሉ ነገሮች ድንጋጌዎችን በማውጣት ነው፡፡ ቀሪው ደግሞ ስለ ዕርቅ /conciliation/ ይናገራል፡፡ የዚህ ጽሑፍ ዓላማ በግልግል ዳኝነት ሂደት ስለሚሰጡ የዕግድ ትእዛዞች በተለይ አፈጻጸማቸውን ከአዋጁ አንጻር መመልከት ነው፡፡

  2630 Hits

በውርስ ሕግ አተረጓጎም ዙሪያ በተሰጡ አንዳንድ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አስገዳጅ የሕግ ትርጎሞች ላይ የቀረበ ትችት

ይህ ጽሑፍ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከውርስ ሕጉ አጠቃላይ አወቃቀር እና አደረጃጀት ወጥተው በአንደኛው የውርስ ሕግ ክፍል የተደነገገን ድንጋጌ አግባብነት ለሌለው ሌላ የውርስ ሕግ ክፍል ተግባራዊ በማድረግ አንዳንዴም በጉዳዩ ላይ ተፈጻሚነት ያላቸዉን የውርስ ሕግ ድንጋጌዎች በመተዉ አጠቃላይ የዉል ሕግ ድንጋጌዎችን መሠረት በማድረግ ገዥ ትርጉም መስጠታቸውን እና ይህም ሕጉን የተከተለ አለመሆኑን ይከራከራል፡፡ እንዲሁም በዚህ ምክንየት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በራሱ ተቃራኒ እና ምክንየታዊ ያልሆኑ ውሳኔዎች እየተሰጡ መሆኑን በማሳየት የውርስ ሕጉ ሊተረጎም እና ተግባራዊ ሊሆን የሚችልበትን መንገድ ይጠቁማል፡፡

  7014 Hits

ፍትሕ እና ጤና

በሀገራችን የፍትሕ ሥርዓት ውስጥ ራሳቸውን በተለየ መልኩ የፍትሕ አካላት በማለት በየዓመቱ ሚያዝያ/ግንቦት ወር የፍትሕ ሣምንት የሚያከብሩ የፖሊስ፣ የማረሚያ ቤቶች አስተዳደር፣ ዐቃቤ ሕግ እና ፍ/ቤቶችን እንመለከታለን፡፡ በየዓመቱም በአዲስ አበባ ከተማችን በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ቅጥር ገቢ ድንኳን እየተተከለ ሥራዎቻቸውን በፎቶ ግራፎች፣ በጽሑፎችና በውይይት በተደገፈ ለሕዝብ በተለይም ለፍ/ቤቱ ባለጉዳዮች ያስጎበኛሉ፡፡ ነገር ግን ፍትሕ ተቋሞቻችን በመሠረታዊነት ከሚመዘኑበት የሥራዎቻቸው ቅልጥፍና፣ ውጤታማነትና ተገማችነት ባሻገር በአካል ለሚመለከታቸው ህንፃዎቻቸው፣ ግቢያቸው፣ የችሎት አዳራሾቻቸው/ክፍሎቻቸው፣ ቢሮዎቻቸው፣ መጸዳጃ ቤቶቻቸው ቢጎበኙ በተለይም ለጤና ተስማሚነታቸው ምን ይመስላሉ? የሚለው ጉዳይ ለዚህ ጽሁፍ ዐብይ መነሻ ምክንያት ነው፡፡

  2069 Hits

የሥራ ውል ያለ ማስጠንቀቂያ የሚቋረጥባቸው መንገዶች

የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 27 ስር ያለ ማስጠንቀቂያ የስራ ውል የሚቋረጥባቸው ሁኔታዎች ተጠቅሰዋል፡፡ በዚህም ጽሁፍ በአንቀጽ 27 ስር ከተመለከተቱት ዝርዝር ሁኔታዎች የተወሰኑት በመጥቀስ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች ጋር በማገናዘብ አጭር ዳሰሳ ለማደረግ ተሞክሯል፡፡ 

  4883 Hits

ቼክና ዋስትና

በአንድ አገር የገበያ ሥርዓት ውስጥ ክፍያ የሚካሄድበት ደንብ አለ፡፡ የክፍያ ሥርዓቱም በዓይነት፣ በጥሬ ገንዘብ፣ በሰነድ ወይም በኤሌክትሮኒክስ ሊሆን ይችላል፡፡ በዓይነት ወይም በጥሬ ገንዘብ የሚደረጉ ግብይቶች በአብዛኛው ተጨማሪ ወጭ የሚጠይቁ፣ ለአያያዝ የማይመቹ እና የደህንነት ሥጋት ያለባቸው የክፍያ መፈፀሚያ ዓይነቶች ናቸው፡፡ እነዚህን ሥጋቶች ለመቅረፍ እና የክፍያ ሥርዓቱን የበለጠ ቀልጣፋ እና ውጤታማ ለማድረግ ክፍያ በቀላሉ ሊፈፀምባቸው የሚችሉ ተላላፊ የንግድ ሰነዶች ተፈጥረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የንግድ ህግ አራተኛ መፅሃፍ ሥርም ከአንቀጽ 715-895 ስለ ተላላፊ የገንዘብ ሰነዶች ዓይነት፣ አጠቃቀም እና ኃላፊነት በዝርዝር ተደንግጓል፡፡ በንግድ ህጋችን እውቅና የተሰጣቸው ተላላፊ የሆኑ የክፍያ መፈፀሚያ ሥርዓቶች አራት ናቸው፡፡

  3173 Hits