በግልግል ዳኝነት አዋጅ መሠረት የእግድ ትእዛዝ አፈጻጸም

አዋጅ ቁጥር 1237/2013 የግልግል ዳኝነትና የእርቅ አሠራር አዋጅ የሚል ርዕስ ተሰጥቶታል፡፡ የአዋጁን ሰፊ ድርሻ የሚወስደው በግልግል ዳኝነት ሂደት ላይ ስላሉ ነገሮች ድንጋጌዎችን በማውጣት ነው፡፡ ቀሪው ደግሞ ስለ ዕርቅ /conciliation/ ይናገራል፡፡ የዚህ ጽሑፍ ዓላማ በግልግል ዳኝነት ሂደት ስለሚሰጡ የዕግድ ትእዛዞች በተለይ አፈጻጸማቸውን ከአዋጁ አንጻር መመልከት ነው፡፡

  142 Hits

በውርስ ሕግ አተረጓጎም ዙሪያ በተሰጡ አንዳንድ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አስገዳጅ የሕግ ትርጎሞች ላይ የቀረበ ትችት

ይህ ጽሑፍ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከውርስ ሕጉ አጠቃላይ አወቃቀር እና አደረጃጀት ወጥተው በአንደኛው የውርስ ሕግ ክፍል የተደነገገን ድንጋጌ አግባብነት ለሌለው ሌላ የውርስ ሕግ ክፍል ተግባራዊ በማድረግ አንዳንዴም በጉዳዩ ላይ ተፈጻሚነት ያላቸዉን የውርስ ሕግ ድንጋጌዎች በመተዉ አጠቃላይ የዉል ሕግ ድንጋጌዎችን መሠረት በማድረግ ገዥ ትርጉም መስጠታቸውን እና ይህም ሕጉን የተከተለ አለመሆኑን ይከራከራል፡፡ እንዲሁም በዚህ ምክንየት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በራሱ ተቃራኒ እና ምክንየታዊ ያልሆኑ ውሳኔዎች እየተሰጡ መሆኑን በማሳየት የውርስ ሕጉ ሊተረጎም እና ተግባራዊ ሊሆን የሚችልበትን መንገድ ይጠቁማል፡፡

  2195 Hits

ፍትሕ እና ጤና

በሀገራችን የፍትሕ ሥርዓት ውስጥ ራሳቸውን በተለየ መልኩ የፍትሕ አካላት በማለት በየዓመቱ ሚያዝያ/ግንቦት ወር የፍትሕ ሣምንት የሚያከብሩ የፖሊስ፣ የማረሚያ ቤቶች አስተዳደር፣ ዐቃቤ ሕግ እና ፍ/ቤቶችን እንመለከታለን፡፡ በየዓመቱም በአዲስ አበባ ከተማችን በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ቅጥር ገቢ ድንኳን እየተተከለ ሥራዎቻቸውን በፎቶ ግራፎች፣ በጽሑፎችና በውይይት በተደገፈ ለሕዝብ በተለይም ለፍ/ቤቱ ባለጉዳዮች ያስጎበኛሉ፡፡ ነገር ግን ፍትሕ ተቋሞቻችን በመሠረታዊነት ከሚመዘኑበት የሥራዎቻቸው ቅልጥፍና፣ ውጤታማነትና ተገማችነት ባሻገር በአካል ለሚመለከታቸው ህንፃዎቻቸው፣ ግቢያቸው፣ የችሎት አዳራሾቻቸው/ክፍሎቻቸው፣ ቢሮዎቻቸው፣ መጸዳጃ ቤቶቻቸው ቢጎበኙ በተለይም ለጤና ተስማሚነታቸው ምን ይመስላሉ? የሚለው ጉዳይ ለዚህ ጽሁፍ ዐብይ መነሻ ምክንያት ነው፡፡

  664 Hits

የሥራ ውል ያለ ማስጠንቀቂያ የሚቋረጥባቸው መንገዶች

የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 27 ስር ያለ ማስጠንቀቂያ የስራ ውል የሚቋረጥባቸው ሁኔታዎች ተጠቅሰዋል፡፡ በዚህም ጽሁፍ በአንቀጽ 27 ስር ከተመለከተቱት ዝርዝር ሁኔታዎች የተወሰኑት በመጥቀስ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች ጋር በማገናዘብ አጭር ዳሰሳ ለማደረግ ተሞክሯል፡፡ 

  1026 Hits

ቼክና ዋስትና

በአንድ አገር የገበያ ሥርዓት ውስጥ ክፍያ የሚካሄድበት ደንብ አለ፡፡ የክፍያ ሥርዓቱም በዓይነት፣ በጥሬ ገንዘብ፣ በሰነድ ወይም በኤሌክትሮኒክስ ሊሆን ይችላል፡፡ በዓይነት ወይም በጥሬ ገንዘብ የሚደረጉ ግብይቶች በአብዛኛው ተጨማሪ ወጭ የሚጠይቁ፣ ለአያያዝ የማይመቹ እና የደህንነት ሥጋት ያለባቸው የክፍያ መፈፀሚያ ዓይነቶች ናቸው፡፡ እነዚህን ሥጋቶች ለመቅረፍ እና የክፍያ ሥርዓቱን የበለጠ ቀልጣፋ እና ውጤታማ ለማድረግ ክፍያ በቀላሉ ሊፈፀምባቸው የሚችሉ ተላላፊ የንግድ ሰነዶች ተፈጥረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የንግድ ህግ አራተኛ መፅሃፍ ሥርም ከአንቀጽ 715-895 ስለ ተላላፊ የገንዘብ ሰነዶች ዓይነት፣ አጠቃቀም እና ኃላፊነት በዝርዝር ተደንግጓል፡፡ በንግድ ህጋችን እውቅና የተሰጣቸው ተላላፊ የሆኑ የክፍያ መፈፀሚያ ሥርዓቶች አራት ናቸው፡፡

  991 Hits

Criminalization of Incitement to commit crime under international criminal law

Several individuals or groups known as parties to the crime may play a distinct role in committing international crimes. The involvement of some of them in the commission of the crime is so close, direct, and active. These persons impose greater danger to society as a whole. The participation of others in the commission of international crime may be indirect by incitement and conspiracy. It supports and legitimizes acts of violence and Persecutory measures against victims. A review of mass crimes, both from the past and the present reveals that incitement and conspiracy generally precede and accompany mass crimes such as genocide, persecution, and extermination.

  1594 Hits

Seerri dhaddacha ijibbaataatin hiikoo itti kenname yoo haqame ta’e murtiin dirqisiisaa duraan kenname seera haaraa bahe irratti raawwii qabaa? Labsii lafa baadiyyaa haaraa naannoo oromiyaa lakk. 248/2011 waliin kan xiinxalam

Akka qajeeltootti seerri murtiin dirqisiisaa irratti kenname yoo haqame dhimmoota walfakkaatoo booddee jiraniif bu’aa dirqisiisummaa kan hin qabneedha. Fakkeenyaaf labsii Seera HH fooyyeessuuf bahe lakk. 639/2001 bahe qabeenya hin sochoone baankiif ykn dhaabbilee faayinaansiitiif liqiif akka wabiitti qabsiifame ilaalchisee mana murtiitti ykn qaama waliigaltee raawwachiisu fuulduraatti mallatta’uun barbaachisaa akka hin taanee tumuun SHH kwt 1723 jalatti akka haalduree kaa’ee walakkaadhaan hambisee jira. kanaafuu murtiileen kan dura SHH kwt 1723 irratti hundaa’uun qabeenya hin sochoone qabsiisuun walqabatee murtiileen dirqisiisaa kennaman hafaa ta’u.

  1870 Hits

የማታለል ወንጀል ከእምንት ማጉደል ወንጀል በምን ይለያል? በድንጋጌዎቹ የወንጀል ክስ ለማቅረብ በመሰረታዊነት መሟላት ያለባቸው የማስረጃ አይነቶችስ ምንድናቸው?

በወንጀል የሚጠረጠሩ ሰዎችን በፍርድ ቤት በመክሰስ ለማስቀጣት በቂና አሳማኝ በሆነ መልኩ ማስረጃ አቅርቦ ማስረዳት በዐ/ህግ በኩል ይጠበቃል፡፡ የተለያየ አይነት ማስረጃን የመመዘን መርህ በወንጀል ክስ ለመክሰስና ጥፋተኛ ለማለት በስራ ላይ የሚውል ቢሆንም በጥቅሉ ሶስት አይነት የማስረጃ አመዛዘን መርህ በስፋት ይታያል፡፡

  4250 Hits
Tags:

ዳኛ የወል ዳኛ

“በሕግ አምላክ” ካለ ሀገሬው ውልክፍ የለም፡፡ ሕግ የማኅበረሰብ የውል ገመዱ ነው፡፡ ሕግ የአንድ ሃገር ባህል፣ ልማድ፣ የኑሮ ዘይቤ ካስማና ባላ ነው፡፡ ሕግ ያለ ሰው፣ ሰው ያለ ሕግ ምሉዕነት የለውም፡፡ ሕግ ፈራጅ ነው በዳዩን ይቀጣል፤ ተበዳዩን ይክሳል፡፡ ሕግ አድራጊ ፈጣሪ ነው ይሾማል፤ ይሽራል፡፡ ሕግ ለጋስም ንፉግም ነው ይሰጣል፤ ይነሳል፡፡ ሕግ የእግር ብረት ሆኖ እግር ከወረች ያስራል፤ ሕግ ቁልፍ ሆኖ ይፈታል፡፡ ሕግ መንገድ ነው ያገናኛል፤ ያለያያል፡፡ሕግ ወረትን አያዉቅም፤ሕግ ዘላቂነትን የሚያልም የሩቅ ተጓዥ ነዉ፡፡ ሕግ አዉጪዎች ካልባለጉ ሕግ አይባልግም፡፡ ሕግ እንደ ፈጣሪ አይደለም፤ መረን የሚለቀዉ ሲመቸን የምናከብረዉ ሳይመቸን የምንጥሰዉ አድርግን ያወጣነዉ ቀን ነዉ፡፡

  1651 Hits
Tags:

ፍቺ ከፍርድ ቤት ውጭ - የሰበር ሰሚ ችሎት እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔዎች አጭር ዳሰሳ

ለዚህ ጽሑፍ መነሻ የሆነው ጸሐፊው በሥራ ምክንያት በሚያያቸው መዝገቦች ስር ሲገጥሙት የነበሩ ክርክሮች እንዲሁም በተለያዩ አጋጣሚዎች ከሥራ ባልደረቦቹ ጋር ጋብቻ ከፍርድ ቤት ውሳኔ ውጭ በሁኔታዎች ስለሚፈርስበት አግባብ ያደረጋቸው ውይይቶች ሲሆኑ በዋነኛነት ግን የቅርብ ምክንያቱ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በጉዳዩ ላይ የሰጠው ውሳኔ ነው። በፌደራሉ የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 75 ሥር እንደተመለከተው ጋብቻ የሚፈርስባቸው ብቸኛ ሦስት ምክንያቶች ሞት ወይም የመጥፋት ውሳኔ፤ ጋብቻ ለመፈጸም መሟላት ካለባቸው ሁኔታዎች አንዱ በመጣሱ ምክንያት ጋብቻው እንዲፈርስ ሲወሰን እንዲሁም ፍቺ መሆናቸው የተመለከተ ሲሆን በአንቀጽ 117 ሥር እንደተመለከተው ደግሞ ጋብቻን በፍቺ ለማፍረስ ሥልጣን የተሰጠው ለፍርድ ቤቶች ብቻ ነው። 

  3627 Hits