ይህ ጽሑፍ በቀጥታ የተወሰደው በፍትሐብሔር ሥነ-ሥርዓት ሕግ የመጀመሪያ ደረጃ መቃዎሚያዎች ከሚለው ተሻሽሎ ከታተመው መጽሐፍ ላይ ነው። ሆኖም ለዚህ የበየነ-መረብ ጽሑፍ ለንባብ እንዲመች በግርጌ ተቀምጠው የነበሩት ማጣቀሻዎች በፅሑፉ ውስጥ እንዲከተቱ ተደርጓል።
በዚህ መጽሐፍ ውስጥ የኢትዮጵያ የንግድ ሕግ አዋጅ ቁጥር 166/1952 ከ50 ዓመታት በላይ ያገለገለ ቢሆንም በከፊል በአዋጅ ቁጥር 1243/2013 የተሸሻለ/የተተካ/ ቢሆንም የድሮው የንግድ ሕግ አዋጅ ቁጥር 166/1952 ውስጥ መጽሐፍ 3 (ሦስት) ማለትም ከአንቀጽ 561 እስከ 714 እና መጽሐፍ 4 (አራት) ማለትም ከአንቀጽ 715 እስከ 967 ያሉ ድንጋገጌዎች ያልተሻሩ ለመሆኑ በአዲሱ የኢትዮጵያ የንግድ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 በመግቢያው አንቀጽ 3(3) ላይ በግልፅ ተደንግጓል። ስለዚህ የንግድ ሕግ ይርጋዎች በአዲሱ ሕግ እና በድሮው ሕግ ያልተሻሩ ድንጋጌዎችን ከሰበር አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ጋር በመጽሐፉ በጥልቀት ተዳሷል።