በኢትዮጵያ ከሕግ አገልግሎት የሚሰበሰብ የተጨማሪ እሴት ታክስና የተርን ኦቨር ታክስ አዙሪት ጥያቄዎችና መውሰብስቦች

በኢትዮጵያ የታክስ አስተዳደር ሥርዓት ውስጥ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የተርን ኦቨር ታክስን በመጠቀም ከሕግ አገልግሎት ሽያጭ ላይ ታክስ እንደሁኔታው በፌዴራሉ እና በክልል መንግሥታት በመጣሉ በተግባርም እየተሰበሰበ ይገኛል። ይሁን እንጅ ይህ ታክስ ሕጋዊ መሠረቱን እና አግባብነቱን በተመለከተ፤ ከታክስ መሠረቱ፣ ከታክስ ምጣኔው እና ከአስተዳደር ሂደቱ ጋር ተያይዞ በርካታ አዙሪት ጥያቄዎችና መውሰብስቦች ይስተዋላሉ፡፡ የዚህ ጥናት ዓላማም አነዚህን አዙሪት ጥየቄዎችና መውሰብስቦች በዓይነታዊ የምርምር ዘዴ በማጥናት የመፍትሔ ኃሳብ መጠቆም ነው፡፡ ለዚህም ያስችል ዘንድ የተለያዩ መዛግብቶች፣ ቃለመጠይቆችና ቡድንተኮር ውይይቶች በግብዓትነት ጥቅም ላይ የዋሉ ሲሆን  ለንፅፅር ይረዳ ዘንድ የሌሎች አገራት ተሞክሮንም ለመቃኘት ተሞከሯል፡፡ በዚህም መሠረት ጥናቱ ባለሶስት አማራጭ የመፍትሔ ኃሳብ ያቀረበ ሲሆን የመጀመሪያው አሁን ከሕግ አገልግሎት በአገሪቱ እየተሰበሰበ ያለውን የሽያጭ ታክስ እንዳለ በማስቀጠል ለፍትሕ ተደራሽነትና ለሕገመንግስታዊ መብቶች መከበር ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር መወሰድ ያለባቸውን ርምጃዎች አመላክቷል፡፡

  1164 Hits

የማስረጃ ሕግ - ሕጉ እና አተገባበሩ

በሰዎች የእለት ከዕለት መስተጋብር ዉስጥ ከሚፈጠሩ ነገሮች መካከል አንዱ ቅራኔ ነዉ። ቅራኔ ሲኖር ደግሞ የመረጃ ወይም ማስረጃ ጉዳይ አብሮ ይነሳል። በተለይ ለዳኝነት አካላት ማለትም ለፍርድ ቤት፤ ለግልግል እና ለመሳሰሉት በሚቀርቡ ክርክሮች ላይ ማስረጃን ወይም መረጃን የሚመለከቱ ጉዳዮች መነሳታቸዉ አይቀሬ ናቸዉ። እዚህ ላይ የመረጃ እና ማስረጃን ልዩነት መረዳት ተገቢ ነዉ። ማስረጃ አንድን አከራካሪ ፍሬ ጉዳይ ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል የሚቀርብ ተጨባጭ ጉዳይ ሲሆን፤ መረጃ ግን አንድን ነገር ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል የሚሰጥ መግለጫ (Information) ብቻ ነዉ። ሁሉም ማስረጃ የመረጃነት ባህሪ ያለዉ ሲሆን፤ ሁሉም መረጃ ግን ማስረጃ አይደለም። ማስረጃ ለፍትሕ አካል የሚቀርብ መረጃ ሲሆን፤ ይህ መረጃም ፍሬ ነገርን የሚመለከት ነዉ። ፍሬ ነገር ማለትም በፍርድ ቤት ወይም በሌላ የዳኝነት አካል ፊት አከራካሪ ሆኖ የወጣ እና የተያዘ ጭብጥን የሚመለከት ነዉ። ማስረጃ የሚቀርበዉም ይህንን አከራካሪ ጭብጥ ወይም ፍሬ ነገር ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል ነዉ። የማስረጃ ሕግ ተፈጻሚነት የሚታየዉም በዚህ ጊዜ ነዉ።

  2835 Hits

Criminal Reinstatement in Ethiopia: Exploring the Factors Behind its Limited Application

Introduction

Criminal reinstatement (simply reinstatement) also known as “Expungement” or “Expunction” in the common law legal system is a legal process that allows individuals with criminal records to have their convictions removed from public records. This means that the records are destroyed; making them inaccessible to organizations that may conduct background checks. Reinstatement is a concept included in our criminal code and criminal procedure code, but the law and its details are hardly known in our society. As a result, it is not widely used. This paper explores the concept of reinstatement, its difference from pardon, the eligibility criteria, the process involved, its relevance in helping individuals reestablish their lives following a conviction, and the impact it has on individuals and society as a whole. It also highlights the gaps in the current practice of criminal reinstatement and concludes with recommendations for improvements. 

  1114 Hits

የሕግ አረቃቀቅ ሥርዓት በኢትዮጵያ

ሕግ ማርቀቅ አንዱ እና ዋነኛው የሕግ ሙያ ዘርፍ ነው፡፡ ሕግ ማውጣት የሚያስፈልግበት ዋና ዓላማ የመንግስትን ፖሊሲ ለማስፈፀም ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ሕግ የፖሊሲ ማስፈፀሚያ ተደርጎም ይወሰዳል፡፡ የሕግ አረቃቅ ላይ ሊወሰድ የሚገባው ጥንቃቄ እና የአረቃቅ ሂደቱ ሕጉ ከፀደቀ በኋላ የሚኖረው አተገባበር ላይ ቀጥተኛ የሆነ ተፅእኖ ያለው መሆኑ ይታወቃል፡፡ የሕግ አረቃቀቅ በኢትዮጵያ ወጥነት የሚጎድለው፤ ትኩረት የሚሻ እና በሕግ አግባብ ሊመራ የሚገባ ዘርፍ ነው፡፡አሁን ላይ ይህ ዘርፍ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚመራበት አንድ ወጥ የሆነ የሕግ ማዕቀፍ የሌለውም ዘርፍ ነው፡፡ ዘርፉ በዚህ አግባብ የሚመራበት የሕግ ማዕቀፍ አለማግኘቱ በሕጎች አረቃቀቅ ጥረት፤ ወጥነት፤ መናበብ፤ እና አፈፃፀም ላይ የራሱ የሆነን አሉታዊ ተፅእኖ እንዳሳደረ ይታመናል፡፡

  821 Hits

በሌላ ሰው ይዞታ ላይ ቤት የሰራ ሰው መብት - አንዳንድ ነጥቦች 

ሲፈጠር የአንድ ቤተሰብ የነበረው መሬት ቤተሰቡ በቢሊዮን ሲራባ አንድ ኢንች አልጨመረም። በመንኮራኩር ሰማይ ቢታሰስ በሮኬት ጠፈር ቢሰነጠቅ በምድር ላይ እንዳለው ያለ መሬት እስካሁን አልተገኘም። በምድር ያለው መሬትም በተለያዩ ምክንያቶች ጠቀሜታው እየቀነሰ፣ ለምነቱ እየጠፋና እየጠበበ ይገኛል። መሬት በገጠርም ሆነ በከተማ ዋነኛ የመብት ምንጭ እና የሁሉም ምጣኔ ሀብታዊ፣ ማሕበራዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች መሰረት ነው። እያለቀ የሄደውን መሬት እየጨመረ ላለው ሕዝብ በሚዛን ለማከፋፈል በተለያዩ ሀገራት በተለያዩ ጊዜያት ልዩ ልዩ ፍልስፍናዎች ሲፈለሰፉ፣ ርዕይዎተ ዓለም ሲሆኑ፣ ወደፖሊሲ ሲቀየሩና ሕግ እየሆኑ ሲተገበሩ ቆይተዋል። እየተተገበሩም ይገኛሉ። ይሁን እንጂ በዚህ ዘመን ለሁሉም ዜጎች መሬት መስጠት የሚያስችል ምንም ዓይነት ፍልስፍና አልተገኘም። 

  3329 Hits

አካለመጠን ባልደረሱ ወጣት የወንጀል ሕግ ተላላፊዎች ላይ የኢትዮጵያ የሕግ ማዕቀፍ - የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓትና የወንጀል ሕጉን መነሻ በማድረግ

በ1995 የወጣው የኢፌዲሪ ህገ-መንግስት ለተጠረጠሩና ለተከሰሱ ሰዎች በርካታ የሕግ ጥበቃዎችን ያደርጋል። እነዚህ ጥበቃዎች በዋናነት በሕግ ፊት በእኩል የመታየት፣ በሕግ አግባብ የመዳኘት፣ አላግባብ ቤታቸውና አካላቸው ከመበርበር የመጠበቅ፣ ከሕግ አግባብ ውጭ ያለመያዝ፣ በጠበቃ የመወከል፣ ንፁህ ሆኖ የመገመት፣ የፍርድ ሂደታቸው በግልፅ ችሎት ፈጣን በሆነ መልኩ እንዲካሄድ የማድረግ፣ የሚቀርብባቸውን ማስረጃ የመመልከትና መስቀለኛ ጥያቄ የመጠየቅ፣ ኢሰብአዊ ከሆነና ጭካኔ ከተሞላበት ቅጣት የመጠበቅ እና በአንድ ወንጀል ሁለት ጊዜ ያለመቀጣት መብት ናቸው። እነዚህ መብቶች በአብዛኛው እድሜያቸው ከ18 አመት በላይ በሆኑ ወይም ለአካለመጠን በደረሱ ወጣቶች ላይ የሚተገበሩ ሲሆን አካለመጠን ባልደረሱ ሰዎች ላይ ሁኔታው የተለየ ሆኖ ይገኛል። በወንጀል ለተጠረጠሩና ለተከሰሱ አዋቂ ሰዎች በሕግ የተቀመጡ ጥበቃዎች አካለመጠን ላልደረሱ ሰዎች ሲከለከሉ ወይም በዝምታ ሲታለፉ ይስተዋላል።

  5323 Hits

በደርግ ዘመን አዋጅ ቁጥር 47/67 ተግባራዊ በሆነበት ወቅት ያላግባብ የተወረሱ የግለሰብ ቤቶች አሁን ላይ ለግለሰቦቹ ወይም ለሕጋዊ ወራሾቻቸው ሊመለሱ የሚችሉበት የሕግ አግባብን በተመለከተ ከሰበር ውሳኔዎች ጋር ተገናዝቦ የቀረበ

የንጉሣዊ ሥርዓት መውደቁን ተከትሎ ወደ መንግሥታዊ ሥልጣን የመጣው ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ የከተማ ቦታና ትርፍ ቤት የመንግሥት ንብረት ለማድረግ በሚል አዋጅ ቁጥር 47/1967 በማወጅ ተግባራዊ አድርጓል፡፡ ይህ አዋጅ ሊታወጅ ያቻለበት ዋነኛ መነሻ ምክንያት “በከተሞች ውስጥ የሚገኙ አብዛኛዎቹ ቦታዎችና ቤቶች በጥቂት መሳፍንት፣ መኳንንትና በከፍተኛ የመንግሥት ባለ ስልጣኖችና ከበርቴዎች በመያዛቸው እንዲሁም የሀብታም ክፍሎች ያላቸውን ከፍተኛ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ኃይል ያለ አግባብ በመጠቀም ሰው ሰራሽ የከተማ ቦታ እጥረት በመፍጠር የከተማ ቦታ ዋጋን እንዲወደድ በማድረግ በጠቅላላው የብዝበዛ ሥርዓት ጠንክሮ ለከተማው እድገትና ለብዙኃኑ የከተማ ነዋሪዎች የኑሮ መሻሻል ከፍተኛ እንቅፋት በመሆናቸው” በሚል አዋጁን መሠረት በማድረግ የከተማ ቦታና ትርፍ ቤት የመንግሥት ንብረት ሊሆን ችሏል፡፡

  10770 Hits

ከውርስ ኃብት ክፍፍል ጋር የተያያዙ አንዳንድ ነጥቦች ከፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከሰጣቸው ውሰኔዎች ጋር በማገናዘብ የቀረበ

የሟች የውርስ ኃብት ተጣርቶ ከተዘጋ በኋላ የውርስ ኃብት ባለቤትነት ወደ ሟች ወራሾች ይተላለፋል፡፡ በመሆኑም ውርስ ከተዘጋ በኋላ ወራሾች መሀከል ክፍያ እስኪፈጸም ድረስ የሟች ወራሾች በሀብቱ ላይ ያላቸው መብት ምንድነው? ክፍፍሉ ከመፈጸሙ በፊት በጋራ ወራሾች የተያዘ ንብረት በአንደኛው ወራሽ ብቻ ለሶስተኛ ወገን በሽያጭ ቢተላለፍ ፈቃዳቸውን ያልሰጡ ወራሾች መብታቸው እስከምን ድረስ ነው? ገዥውን ያለውስ መብት ምንድነው? የውርስ ሀብት ክፍፍል የሚደረግባቸው ስነ-ስርዓቶችንና ክፍፍል ከተደረገ በኋላ የሚገኙ የውርስ ኃብት የሆኑ ንብረቶች ለወራሾች ሊከፋፈሉ የሚችሉባቸው የህግ ስርዓቶችን በተመለከተ በወራሾችና ወራሽ ባልሆኑ ሶስተኛ ወገኖች መሀከል እስከ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ድረስ የደረሱ አከራካሪ ጉዳዮች አሉ፡፡ በዚህ ጽሁፍ እነዚህን ነጥቦች በተመለከተ ከፍትሐብሔር ሕጉና ከተመረጡና አስገዳጅ ከሆኑ የሰበር ውሳኔዎች አንጻር አጭር ዳሰሳ ለማድረግ እሞክራለሁ፡፡

  4609 Hits

ጠበቃ በጋብቻ ፍቺ ሂደት ስለሚኖረው የሙያ ወሰን እና የሰበር ተቃርኖ

ጋብቻ በሁሉም ባህሎችና ሃይማኖቶች ትልቅ ክብር እና ልዩ ቦታ የሚሰጠው የሃገር ምሶሶ የሆነ የቤተሰብ ተቋም የሚፈጥ ሕጋዊ ኩነት ነው፡፡ በመሆኑም ፀንቶ እንዲቆይ በመንግስት እና በህብረተሰቡ ጥበቃ ይደረግለታል፡፡ መንግስት ጋብቻ ሲመሰረት፣ በጋብቻ ውስጥ እና ሲፈርስ ግንኙነቱ የሚመራበትን ሥነ ስርዓት በህግ በመደንገግ ጥበቃ ያደርጋል፡፡ ጋብቻ በፍች እንዲፈርስ ጥያቄ በሚቀርብበት ወቅት ፍርድ ቤት ጋብቻው ፀንቶ እንዲቆይ ለማስቻል ሊከተላቸው እና ሊፈፀማቸው የሚገቡ የጥበቃ ሥነ-ሥርዓት በቤተሰብ ህግ ተደንግጓል፡፡ (አንቀፅ 76 - 82 ይመለከቷል)። 

  2621 Hits

የከተማ መሬት ሕግ በአዲስ አበባ - ክፍል አንድ - የሚል የሕግ መጽሐፌን በማሳተም ለአንባቢያን አቅርቢያለሁ

በመዲናችን የመሬት ሕግ ላይ ትኩረት ያደረገውና ”የከተማ መሬት ሕግ በአዲስ አበባ” የሚል አርዕስት ያለው መጽሐፍ ስለ መሬት ሕግ ጠቅላላ ጽንሰ ሃሳባዊ ጉዳዮችን ጨምሮ ስለ እስከዛሬው የአገራችን የመሬት ስሪት ሁኔታ፣ ከዚሁ ጋር ተያያዥነት ስላላቸው የመዲናችን ዋና ዋና ጉዳዮች ለምሳሌ የመዲናችንን የቆዳ ስፋት፣ የወሰን አከላለል እና ሕጋዊ አቋም የሚያብራሩ እንዲሁም ከመዲናችን ምስረታ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ያለውን የመሬት ስሪት ሁኔታ የሚያስረዱ ነጥቦችን አሁን ለንባብ በበቃው የመጀመሪያው ክፍል ይዟል፡፡

ስለሆነም ይህንኑ የምርምር መጽሐፌን እንድታነቡልኝ ስል በአክብሮት እጋብዛለሁ፡፡

  1757 Hits