ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብሮ መኖር፤ አንድምታዎቹ እና ተግዳሮቶቹ

በተሻሻለው የኢትዮጲያ የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 1 መሰረት ህጋዊ ጋብቻ በተለያዩ ሰነ-ስረዓቶች ሊፈፀም ይችላል፡፡ እነሱም በክብር መዝገብ ሹም ፊት፣በሐይማኖት እና በባህል መሰረት የሚፈፀሙ የጋብቻ አይነቶች ናቸው፡፡ በተጨማሪም ጋብቻ ከላይ በተጠቀሱት በአንዳቸው ስነ-ስርዓቶች ቢፈፀም እንኳን ውጤቱም አንድ መሆኑን የዚሁ ህግ አንቀፅ 40 ያትታል፡፡ ህጋዊ ጋብቻ በተጋቢዎቹ ላይ ሁለት ዓይነት ውጤት ይኖረዋል፡፡ የመጀመሪያው በተጋቢዎች ግለዊ ግንኙነት ላይ የሚኖረው ውጤት ሲሆን፤ በስሩም የመከባበር ፣ የመተጋገዝና የመደጋገፍ ግዴታ ፣ ቤተሰብን በጋራ የመስተዳደር እና በጋራ አንድ ላይ የመኖር ግዴታዎችን ያቅፋል፡፡ ሁለተኛው ውጤት ደግሞ ጋብቻ በተጋቢዎች ንብረት ላይ የሚኖረው ውጤት ነው፡፡ ይህም ተጋቢዎች  ጋብቻቸውን በሚፈፅሙበት ጊዜ በግል የነበሯቸው ንብረቶች ወይም ከጋብቻ በኋላ በውርስ እና በስጦታ በየግላቸው ያገኙዋቸው ንብረቶች የግል ንበረታቸው ሆነው ሲቀሩ ከዚህ ውጪ ያሉ ንብረቶች በሙሉ የጋራ  ንብረት ይሆናሉ፡፡

Continue reading
  18871 Hits

ጠበቃ በጋብቻ ፍቺ ሂደት ስለሚኖረው የሙያ ወሰን እና የሰበር ተቃርኖ

ጋብቻ በሁሉም ባህሎችና ሃይማኖቶች ትልቅ ክብር እና ልዩ ቦታ የሚሰጠው የሃገር ምሶሶ የሆነ የቤተሰብ ተቋም የሚፈጥ ሕጋዊ ኩነት ነው፡፡ በመሆኑም ፀንቶ እንዲቆይ በመንግስት እና በህብረተሰቡ ጥበቃ ይደረግለታል፡፡ መንግስት ጋብቻ ሲመሰረት፣ በጋብቻ ውስጥ እና ሲፈርስ ግንኙነቱ የሚመራበትን ሥነ ስርዓት በህግ በመደንገግ ጥበቃ ያደርጋል፡፡ ጋብቻ በፍች እንዲፈርስ ጥያቄ በሚቀርብበት ወቅት ፍርድ ቤት ጋብቻው ፀንቶ እንዲቆይ ለማስቻል ሊከተላቸው እና ሊፈፀማቸው የሚገቡ የጥበቃ ሥነ-ሥርዓት በቤተሰብ ህግ ተደንግጓል፡፡ (አንቀፅ 76 - 82 ይመለከቷል)። 

Continue reading
  54 Hits

ጋብቻ በሚፈርስበት ወቅት የባልና ሚስት የንብረት ክፍፍል ሥነ-ሥርዓት ከሰበር ውሳኔዎች ጋር ተገናዝቦ የቀረበ

መግቢያ

ጋብቻ የተፈጸመበት ስነ-ስርዓት ማናቸውም አይነት ቢሆንም የጋብቻ መፍረስ የሚያስከትለው ውጤት ተመሳሳይ ነው፡፡ ጋብቻ ከተጋቢዎቹ አንዱ ሲሞት ወይም በፍርድ ቤት የመጥፋት ውሳኔ ሲሰጥ ወይም ጋብቻ ለመፈጸም መሟላት ያለባቸው ሁኔታዎች አንዱ በመጣሱ ምክንያት በሕግ ጋብቻው እንዲፈርስ ሲወሰን ወይም የፍቺ ውሳኔ ሲሰጥ ሊፈርስ ይችላል፡፡

Continue reading
  18870 Hits

ስለባልና ሚስት የጋራ እና የግል ንብረቶች በተመለከተ የፌዴራሉን የቤተሰብ ሕግና የተመረጡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎችን መሰረት በማድረግ የቀረበ

መግቢያ

በፌዴራሉ የቤተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር 213/1992 ከአንቀጽ 2 እስከ 4 በተጠቀሱት ድንጋጌዎች  ጋብቻ በክብር መዝገብ ሹም ፊት፣ በኃይማኖት እና በባሕል ሥርዓት መሠረት ሊፈጸም ይችላል፡፡ ከእነዚህ የጋብቻ መፈጸሚያ ስርዓቶች ውስጥ በአንደኛው ስነ-ስርዓት ጋብቻ የተፈጸመ እንደሆነ በጥንዶቹ መካከል በሕግ እውቅና የተሰጠው የትዳር ግንኙነት ተመስርቷል ይባላል፡፡ ጥንዶቹ ከዚህ በላይ ከተጠቀሱት የጋብቻ መፈጸሚያ መንገዶች ውስጥ በአንዱ ጋብቻ ቢፈጽሙ የጋብቻ ውጤትን መሠረት በማድረግ በሕግ የጋራ እና የግል ንብረቶቻቸው ላይ የሚኖረው ውጤት ተመሳሳይ ነው፡፡  

Continue reading
  9832 Hits

Ilmi Maqaan Abbaa Isaa akka jijjiirramuuf kallattiidhaan gaafachuu ni danda’aa?

Ilmi Maqaan Abbaa Isaa akka jijjiirramuuf kallattiidhaan gaafachuu ni danda’aa? Xiinxala Raawwatiinsa SHH Kwt 42 fi 43 irratti taasifame.

Bu’uura Heera Mootummaa Federaalaa Kwt 36(1)(b) tiin daa’imni kamuu maqaa fi lammummaa qabaachuuf mirga qaba jechuun kaa’eera. Gama kanaan seerri maqaa namni tokko qabaachuu kan danda’u haala kamiin akka ta’e kaa’u immoo S/H/H kwt 32-46 akkasumas kwt 3358- 3360 tti jiran jalatti kaa’ameera. Bu’uuruma kanaan namni tokkoo maqaa firaa(family name),maqaa dhuunfaa tokko ykn isaa ol (first name) fi maqaa abbaa(patronymic ) qabaachuu akka qabu qajeeltoon isaa S/H/H kwt 32 jalatti kaa’ameera.

Continue reading
  4375 Hits

አዲስ ለተወለደ ህፃን ልጅ ስም የማውጣት መብት፤ የእናት ወይስ የአባት? - የሕግ ባለሙያዎች ወግ

 

መግቢያ

ከሰሞኑ በአንድ ጠበቆች፣ ዳኞች፣ ዓቃቢያነ ሕግች፣ የሕግ ምሁራን እና የሴቶች መብት አቀንቃኞች የተገኙበት የሴቶች እኩልነት እና ሰብዓዊ መብቶች በሚል ርእስ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ ተገኝቼ ሳለሁ፤ አንዲት ተሳታፊ ጠበቂት ሃሳቧን ስታጋራ ለህፃን ስያሜ የመስጠት መብት የወላጆች የጋራ መብት ነው ብላ በደፈናው ተናግራ ስትጨርስ የውይይቱ መሪ ይህን ሀሳብ በሕግ የተደነገገ መብት ነው ብላ ስትደግም ከተሳታፊዎች ጉርምምታ ሲበዛ ለምን አላጠራውም በሚል፤ ይህንን ንግግሯን የሚደግፍ የሕግ ማዕቀፍ ካለ በሚል ጥያቄ አቅርቤላት ነበር፡፡ አወያዪዋም የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ እና ሕገ-መንግሥቱ ይደነግጋል በማለት ምላሽ ስትሰጥ፤ በዚህ ነጥብ ላይ የጦፈ ክርክር ይነሳል፡፡

Continue reading
  6043 Hits

በ-ያለእድሜ ጋብቻ የሚጣሱ መብቶች

ጋብቻ ክቡር፣ ምኝታውም ቅዱስ እንደ ሆነ የሀይማኖት መጻህፍት ያስተምራሉ፡፡ ከዚህም ሌላ ጋብቻ የህብረተሰብ ተፈጥሯዊ መነሻ የሆነው ቤተሰብ የሚመሰረትበት በመሆኑ ከመንግስትና ከህብረተሰብ ያላሰለሰ የህግ ጥበቃ ይደረግለታል፡፡ ይህም ጉዳይ በበርካታ አለም አቀፋዊ፣ አህጉራዊና ብሄራዊ ህጎች እውቅና አግኝቷል፡፡

ይሁንና የጋብቻው ክቡርነትም ይሁን የምኝታው ቅዱስነት የሚረጋገጠው እንዲሁም መንግስትና ህብረተሰብ ህጋዊ ጥበቃ የሚያደርጉለትን ቤተሰብ ለመመስረት ብቁነት የሚኖረው ጋብቻው በህግ መሰረት የተፈጸመ ሲሆን ነው፡፡ ነገር ግን ከዚህ በተቃራኒው በአማራ ክልል ከሚመሰረቱ ትዳሮች መሀከል ሰማኒያ ሁለት ከመቶ የሚሆኑት ያለ እድሜ ጋብቻ የሚፈጸምባቸው ናቸው፡፡

ከላይ የተገለጸው አሀዝ ከፍተኛነት ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነ ሲሆን ጽሁፉ ያለ እድሜ ጋብቻን ምንነት፣ የሰብአዊ መብት ስምምነቶች ስለ ያለ እድሜ ጋብቻ ያላቸውን አቋምና ያለ እድሜ ጋብቻን ለማስቆም የሚያጋጥሙ ችግሮችን በአጭሩ ይዳስሳል፡፡ በመቀጠልም በያለ እድሜ ጋብቻ የሚጣሱ መብቶችንና ያለ እድሜ ጋብቻ መፈጸም የሚያስከትለውን የህግ ተጠያቂነት በዝርዝር ይመለከታል፡፡

ያለ እድሜ ጋብቻ ምንነትና የሰብአዊ መብት ስምምነቶች አቋም

ኢትዮጵያ ውስጥ ከ140 በላይ የሚሆኑ ጐጂ ልማዳዊ ድርጊቶች ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህ አንዱና ዋናው ደግሞ ያለ እድሜ ጋብቻ ነው፡፡ በዚህ ያለ እድሜ ጋብቻ የአማራ ክልል በሀገር ደረጃ ቀዳሚውን ስፍራ የያዘ ሲሆን ይሄው ድርጊት ከገጠሩ የክልሉ ክፍሎች አልፎ በከተሞች አካባቢም ይፈጸማል፡፡

Continue reading
  20270 Hits
Tags:

የጋብቻ እና ፍቺ ሕጋዊ ውጤቶች ከተሸሻለው የቤተሰብ ሕግ አንፃር

 

መግቢያ

የሰው ልጆች በዚህ ምድር ላይ መኖር የጀመሩትና ማህበራዊ መስተጋብር እንድ ህብረተሰብ ክፍል ብሎም እንደ ሀገር መኖር የጀመሩበት ጊዜ እና ቦታ ላይ የታሪክ ሊቃውንት በእርግጥ ይሄ ጊዜና ቦታ ባይሉንም ረጅም ዘመናትን እንዳስቆጠሩ ይገልፃሉ፡፡ የአንድ ሀገር ወይም ማህበረሰብ መሠረት የሆነው ቤተሰብ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ይህ የሕብረተሰብ መሠረት የሆነው ቤተሰብ የሚመሰረተው በተለያየ መልኩ ቢሆንም ዋናው ግን የህብረተሰቡ አካል የሆኑት ሰዎ (ወንድ እና ሴት) በሚፈጸሙት ጋብቻ ነው፡፡ ቤተሰብ የህበረተሰቡ ዋና መሶሶ በመሆኑ ትልቅ ቦታና ከበሬታ የሚሰጠው ነው፡፡ ይህ ትልቅ ቦታና ከበሬታ የሚሰጠው የህብረተሰቡ መሠረት የሆነ ተቋም እንደ ተቋም ከመቋቋሙ አንስቶ እስከ መጨረሻው ጊዜው ድረስ በሕግና እና ስርዓት መመራት ይኖርበታል፡፡ የቤተሰብ መመስርቻ የሆነው ጋብቻ በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ኖሮት እንዲዘልቅ ህብረተሰቡ ባወጣው ሕግ መሠረት መመሥረት ይኖርበታል፡፡ እንዲሁም በቆይታው ጊዜ የሚፈጠሩትን ግንኝነቶችና ውጤቶች እንዲሁም በሕግ መሠረት ከለላ ሊኖራቸው ይገባል፡፡ ለምሳሌ ያህል የልጅ አስተዳደግና አስተዳደር፣ በትዳር ውስጥ ስለሚፈጠሩ ንብረቶች፣ ከትዳር በፊት የነበሩ ንብረቶች፣ በባልና ሚስት መሀል ስለሚኖረው ግለሰባዊ ግንኙነቶች፣ በዚህ ትዳር ውስጥ ሆኖ ማድረግ ስለተከለከሉ ነገሮች እና ወዘተ የመሳሰሉት በሕግ መሠረት መደንገግ ይኖርባቸዋል፡፡

ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ይህን የህብረተሰብ ምሰሶ የሆነውን ትዳር (ቤተሰብ) ሊያፈርሱት ይችላሉ፡፡ ይህ በሕግ መሠረት የተቋቋመው ተቋም በሕግ መሠረት ሕጋዊ በሆነ መልኩ ነው መፍረስ ያለበት፡፡ ፍቺ በሕጉ መሠረት በመፈጸም ትዳር ሲፈርስ የራሱ የሆነ ሕጋዊ ውጤት ይኖረዋል፡፡ የልጆች ቀለብ በትዳር ውስጥ የፈሩ ንብረቶች አከፋፈል ወዘተ በሕግ መሠረት መሆን ይኖርበታል፡፡

በዚህ ጽሑፍ ውስጥም የጋብቻና ፍቺ ሕጋዊ ውጤቶቻቸው ከቀለብ መስጠት፣ ንብረት ግንኙነት (Pecuniary effect) እና ግላዊ የተጋቢዎቹ ግንኙነት (personal effect) ላይ በማተኮር በአሁኑ ሰዓት በፌዴራል መንግስት ደረጃ የወጣውን የተሻሻለውን የቤተሰብ ሕግ ዙሪያ ያለውን የሕግ ማዕቀፍ እና አተገገባበሩ ላይ ትኩረት በማድረግ የሚዳሰስ ይሆናል፡፡

Continue reading
  63772 Hits

በገጠር መሬት የመጠቀም መብትን በዋስትና ማስያዝና አርሶ አደሩ

 

 

አባትነትን DNA በትክክል ማወቅ ይቻላል?

ስለ ኪሜራ ምን ያውቃሉ?

 ሰላም እንዴት ናችሁ በማለት እስኪ ሙያችን በተመለከተ አንድ ቁምነገር ላንሳ፡፡

Continue reading
  18346 Hits

የቤተሰብ ሕጉ አንቀጽ 107/2/ ከሌሎች የቤተሰብ ሕጉ ድንጋጌዎች እና ከሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 36 ጋር ያለው ተቃርኖ

መግቢያ

እናትነት እውነት አባትነት ግን እምነት ነው የሚለው አባባል ተደጋግሞ የሚሰማው አባትነትን ማረጋገጥ ፈታኝ የሆኑ ማህበራዊ ባይሎጂካዊና ሕጋዊ ውስብስብነት ያለው ፈታኝ ጉዳይ በመሆኑ ነው፡፡ አባት ለልጁ ግዴታዎችን  አሉበት፤ አባት ከልጁ የሚጠይቀው መብት አለው፡፡ ልጅ ለአባቱ የሚጠይቀው ግዴታዎች ያሉበትን ያህል ከአባቱም የሚጠይቀው መብት አለው፡፡ እኚህ በመሀላቸው መብትም ግዴታም ያስተሳሰራቸው ሁለት ሰዎች ታዲያ በርግጥም አባትና ልጅ ናቸው? የሚለው ጥያቄ ፈታኝ ነው፡፡ ለዚህ ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከባድ ስለመሆኑ አባትነትንና ልጅነትን ስለማወቅ በሕጉ የተቀመጡ ድንጋጌዎች ለጥያቄው ምላሽ በሚሰጡበት አካሔድ መረዳት ይቻላል፡፡ ይህ ጽሑፍም የሚያጠነጥነው ከጋብቻና እንደባልና ሚስት አብሮ ከመኖር ግንኙነት ውጭ በአንድ አጋጣሚ ግብረ ሥጋ ግንኙነት ምክንያት የተወለደን ልጅ በተመለከተ ሆኖ በእንደዚህ ዓይነት ግንኙነት የተወለደ ልጅ በርግጥ በሕግ አይን አባት አለው? ካለውስ ሕጉ በዚህ ረገድ ግልጽና ወጥ ነው? የቤተሰብ ሕጉ አንቀጽ 107/2/ በርግጥስ ፋይዳው ምንድን ነው? የሚሉ ጉዳዮችን ለውይይት መነሻ እንዲሆን ያህል ለመዳሰስ ይሞክራል፡፡

አባትነትን እና ልጅነትን ስለማረጋገጥ

በቤተሰብ ሕጉ አቀራረጽ መሠረት ልጆች በሦስት ይከፈላሉ፤ እነዚሁም በጋብቻ ውስጥ የተወለዱ፤ እንደ ባልና ሚስት አብረው ከሚኖሩ ሰዎች የተወለዱ ልጆች እና ከሌላ ዓይነት ማለትም ከመጀመሪያዎቹ ከሁለቱ ውጭ በሆነ  ሌላ ግንኙነት የተወለዱ ልጆች ናቸው፡፡

የመጀመሪያዎቹ ሁለት ግንኙነቶች በሕግ ፊት ዕውቅና የተሰጣቸውና በሕጉም ተገቢውን ጥበቃ የሚደረግላቸው ሲሆን የመጨረሻው ይነት ሌላ ግንኙነት ግን በሕግ ፊት ውጤት  የማያስተካከል በዚህም ምክንያት በሕግ ጥበቃ የማይደረግለት ተራ ግንኙነት ነው፡፡

Continue reading
  17779 Hits
Tags: