ተገዶ የመያዝን ሕጋዊነት ለማጣራት የሚቀርብ ክስ (Habeas corpus) እና የፍትሐብሔር እንድምታው

የአካል ነጻነት መብት በኢፌዲሪ ህገ መንግስት እውቅና ከተሰጣቸው የሰብአዊ መብቶች መካከል አንዱ እና ዋነኛው መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ ይኸውም የሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 17 ድንጋጌ በግልጽ ማንም ሰው በህግ ከተደነገገው ስርአት ውጪ ሊያዝ እንዲሁም ክስ ሳይቀርብበት እና ሳይፈረድበት ሊታሰር የማይችል ስለመሆኑ ያስቀምጣል፡፡ በእርግጥ ይህ መብት በዚሁ ሕገ መንግስት መሰረት የሀገሪቱ የህግ አካል የሆኑ አለማቀፍ የሰብአዊ መብት ስምምነነት ሰነዶችም ቢሆን እውቅና ከተሰጧቸው የሰብአዊ መብቶች መካከል አንዱ ስለመሆኑ እሙን ነው፡፡ 

ይሁን እና የዚህ አጭር ጽሁፍ ዋነኛ አላማ የዚህን መብት መሰረታዊ  ነጥቦችን ወይም ወሰኑን ለማብራራት ሳይሆን አንድ የአካል ነጻነት መብቴ ተገፏል የሚል ሰው ይህ መብቱን ፍ/ቤት እንዲያስከብርለት አቤቱታ ቢያቀርብ ክርክሩ ከመደበኛው የፍታብሄር ጉዳዮች ክርክር የሚለይበትን ዋና ዋና የሥነ-ሥርዓት  ነጥቦች ለማብራራት ነው፡፡

Continue reading
  3900 Hits

የወራሽነት ማረጋገጫ፣ መቃወሚያ እና ልጅነት፡- ክፍተተ ወሕግ ወአሰራር እና መፍትሔዎቻቸው

 

ስልጣን

የርዕሰ መዲናዋን አስተዳደር ለመመስረት በቻርተር ደረጃ የወጣው አዋጅ ቁጥር 361/95 አንቀጽ 41(1) (ሸ) እና ማሻሻያው አዋጅ ቁጥር 408/96 አንቀጽ 2 የወራሽነት ማረጋገጫን ጨምሮ ሌሎች ምስክር ወረቀቶች የመስጠት የስረ ነገር ስልጣንን ለአዲስ አበባ ከተማ ፍ/ቤቶች ሰጥቷል። በዚህም መሰረት ከሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና አምስት ዓመተ ምህረት ጀምሮ እስካሁን ድረስ እነዚህ ፍ/ቤቶች እገሌ የእገሌ ወራሽ ነው፣ አንቺ የእንትና ሚስት ነበርሽ፣ አንተ ደግሞ የእገሊት አበዋራ ነበርክ …….. ወዘተ እያሉ በሕግ ዓይን ህያው ይሆን ዘንድ በሞት የፈረሰን የዓይነ ስጋ ዝምድና በወረቀት ማረጋገጫ ሲቀጥሉ ኖረዋል።

Continue reading
  4651 Hits

በኢትዮጵያ የብድር ሕግ "አበደረ" ማለት የብድሩን ገንዘብ ሰጠ ማለት ይሆን?

በዚህ በኩል ግቡ

ብድር የሰው ልጅ እና ጎደሎው ከተገናኙበት ሩቅ ዘመን ጀምሮ የነበረ ሰዋዊ ድርጊት ነው፡፡ የብድር መሰረቶቹ መቀራረብ ፣ እዝነት እና መተማመን ናቸው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ግን እነዚህ መሰረቶቹ እየተናጉ የብድርን ህልውና ሲፈታተኑት ይስተዋላል፡፡ በርካታ ሰዎችም ብድርን መሰረት ላደረጉ ክርክሮች ሲዳረጉ ይታያሉ፡፡

ከእነዚህ በርካታ ብድር ነክ ክርክሮች አንዱ በውሉ ላይ ተበዳሪ ተብለው የተሰየሙ ሰዎች የብድሩን ገንዘብ አልተቀበልኩም በማለት የሚያነሱት ክርክር ነው፡፡ ተበዳሪው በውሉ ላይ ተበድሬአለሁ ብሎ የፈረመ ቢሆንም ውሉ ፍ/ቤት ሲመጣ ግን ተበድሬአለሁ ብዬ ፈርሜአለሁ ግን የብድሩን ገንዘብ አልተቀበልኩም ማለት ይከራከራል፡፡

Continue reading
  2505 Hits

The legality of Levying Income Tax on Illegal Amounts Received by a Taxpayer ---- Personal Reflection

Income tax is essentially a tax levied on a person’s income from various sources. It is a direct tax in the sense that it is demanded from the very persons who, it is intended or desired, should pay it. Hence, every person either a natural person or a corporate entity should have to pay income tax on the respective income they derived.  Nevertheless, Income-driven by a taxpayer may not always be holy. Some incomes earned illegally can be mixed with the lawfully acquired income of the taxpayer. For instance, a shop selling contraband products with lawful once, a hotel collecting payment from prostitutes… etc. At the end of the day, if not understated, such incomes will be reported to tax authorities.

Continue reading
  1833 Hits

ከውርስ ኃብት ክፍፍል ጋር የተያያዙ አንዳንድ ነጥቦች ከፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከሰጣቸው ውሰኔዎች ጋር በማገናዘብ የቀረበ

የሟች የውርስ ኃብት ተጣርቶ ከተዘጋ በኋላ የውርስ ኃብት ባለቤትነት ወደ ሟች ወራሾች ይተላለፋል፡፡ በመሆኑም ውርስ ከተዘጋ በኋላ ወራሾች መሀከል ክፍያ እስኪፈ...

Continue reading
  8751 Hits
Tags:

የማዕድን ሥራዎች ፈቃድ የተሰጠው ሰው እና በኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆነ ንዑስ-ሥራ ተቋራጭ የግብር ግዴታ

መግቢያ

ማንኛውም ገቢ የሚያገኝ ሰው በፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 979/2008 እና በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 መሰረት ግብር የመክፈል ኃላፊነት አለበት፡፡[1] በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም የኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆነ በቋሚነት የሚሰራ ድርጅት፤ በኢትዮጵያ ነዋሪ ላልሆነ ሰው የትርፍ ድርሻ፣ የንዑስ ሥራ ተቋራጭ፣ የወለድ፣ የሮያሊቲ፣ የሥራ አመራር፣ የቴክኒካል፣ የመድን አረቦን፣ ወደ ውጭ አገር የሚላክ ትርፍ፣ እንዲሁም የሌሎች ገቢዎች ክፍያ ሲፈጽሙ ከጠቅላላ ክፍያው ላይ በግብር ሕጉ መጣኔ መሰረት ግብር ቀንሰው መያዝ እንዳለባቸው ተደንግጓል፡፡[2] በተመሳሳይ በኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም በኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆነ በቋሚነት የሚሰራ ድርጅት ከመቀጠር ከሚገኝ ገቢ፣ ከትርፍ ድርሻ ወይም ካልተከፋፈለ ትርፍ፣ ከወለድ፣ ከሮያሊቲ፣ እና ከሌላ በአገር ውስጥ ከሚፈጸም ክፍያ ላይ በግብር ሕጉ መጣኔ መሰረት ግብር ቀንሰው መያዝ አለባቸው፡፡[3]

Continue reading
  3263 Hits

አዲስ ለተወለደ ህፃን ልጅ ስም የማውጣት መብት፤ የእናት ወይስ የአባት? - የሕግ ባለሙያዎች ወግ

 

መግቢያ

ከሰሞኑ በአንድ ጠበቆች፣ ዳኞች፣ ዓቃቢያነ ሕግች፣ የሕግ ምሁራን እና የሴቶች መብት አቀንቃኞች የተገኙበት የሴቶች እኩልነት እና ሰብዓዊ መብቶች በሚል ርእስ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ ተገኝቼ ሳለሁ፤ አንዲት ተሳታፊ ጠበቂት ሃሳቧን ስታጋራ ለህፃን ስያሜ የመስጠት መብት የወላጆች የጋራ መብት ነው ብላ በደፈናው ተናግራ ስትጨርስ የውይይቱ መሪ ይህን ሀሳብ በሕግ የተደነገገ መብት ነው ብላ ስትደግም ከተሳታፊዎች ጉርምምታ ሲበዛ ለምን አላጠራውም በሚል፤ ይህንን ንግግሯን የሚደግፍ የሕግ ማዕቀፍ ካለ በሚል ጥያቄ አቅርቤላት ነበር፡፡ አወያዪዋም የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ እና ሕገ-መንግሥቱ ይደነግጋል በማለት ምላሽ ስትሰጥ፤ በዚህ ነጥብ ላይ የጦፈ ክርክር ይነሳል፡፡

Continue reading
  4032 Hits

የሽያጭ ውልን የተመለከቱ አንዳንድ ነጥቦች ከሰበር ውሳኔ ጋር ተገናዝቦ የቀረበ

 

መግቢያ

በዚህ ጽሑፍ የሽያጭ ውል ምንነት፣ የማይንቀሳቀስ ንብረት የገዛ ሰው ስላለው መብትና ገዥው ስለሚኖርበት ግዴታ፣ የሽያጭ ውልን መሰረት አድርገው የሚቀርቡ ክርክሮች ይዘታቸው እና  የይርጋ ገደባቸው ምን እንደሚመስል እንዲሁም የማይንቀሳቀስ ንብረት የገዛ ሰው ንብረቱን ሊለቅ የሚችልባቸው የሕግ አግባብ ምን ምን እንደሆኑ ከፍትሐብሔር ሕግ እና ከሰበር ውሳኔዎች አንጻር ዳሰሳ ለማድረግ ተሞክሯል፡፡   

Continue reading
  6930 Hits

የሕግ የበላይነትን የሚያናጋው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ (የቤት ኪራይ ማእቀብና የሕግ ጥሰቶቹ)

 

መግቢያ

የአዲስ አባባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ቀደም ሲል አውጥቶት የነበረውና የተከራየን ሰው ማስወጣት (በርግጥ ደንቡ ይህን ድርጊት አልከለከለም) እና የኪራይ ዋጋን መጨመር ለማገድ የወጣውን የደንብ ቁጥር 122/13 ማራዘሙን በድጋሜ አስታዉቋል፡፡ ይህ ደንብ የቤት አከራዮች ያከራዬት ቤት ላይ ዋጋ እንዳንይጨምሩ ክልከላ ይጥላል፡፡ በዚህ አጭር ጽሑፍ የደንቡን ህጋዊነት ለሕግ የበላይነት ያለውን መጥፎ ተምስሌትነት በርግጥ ሊፈታ ያሰበውን ችግር ለመፍታት ያለውን ፋይዳ በአጭር ባጭሩ ለመዳሰስ ይሞክራል፡፡ አንባቢያንን ለተራዘመ እና አሰልቺ የንባብ ሂደቶች ላለመዳረግ ጉዳዩን በቀጥታና በጭሩ ለመዳሰስም ተሞክሯል፡፡

Continue reading
  8187 Hits

Snapshot Note on the Determination of Residency under Ethiopian Income Tax Law - part one

 

Introduction

Income taxation is fundamentally territorial. Due to the existence of multiple sovereign states' interests in the tax collected over economic activities, the legal framework for taxation is also complex. The doctrine of state sovereignty provides the conceptual foundations for the legal framework within which States can exercise their taxing power over economic activity. In the terms of public international law, sovereignty demarcates the State’s tax jurisdiction.

Continue reading
  3414 Hits