ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ

መግቢያ ፡- ተበዳዮች በወንጀል ፍትሕ ሥርዓቱ የነበራቸው የተሳትፎ ሚና፡ ጥቅል ምልከታ

በኢትዮጵያ የወንጀል ተጎጂዎች በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ያላቸው ሚና ከነበረበት የማማ ደረጃ በጊዜ ሂደት ‹‹ከማማ የመውረድ›› ያህል ዝቅ እያለ መጥቷል። ሀገሪቱ በዳግም የኢጣሊያ ወረራ ተፈፅሞባት ከመያዝዋ እ.እ.አ ከ 1935 ዓ.ም በፊት በወንጀል ጉዳት ደርሶባቸው በቀጥታ ተበዳይ የሆኑ ሰዎች ወይም የተበዳይ ተወካይና ቤተዘመዶች በደል ካደረሰባቸው ሰው ፍትሕን በገዛ እጃቸው ያገኙ ነበር። ተበዳይ ጥቃት ያደረሰበትን ሰው ሲፈልግ ይበቀላል፣ ሲፈልግ በፍርድ አደባባይ ይከሳል ወይም ለደረሰበት በደል ከተበዳይ ከሳ ይቀበላል። አይ ይህን ሁሉ አልፈልግም ካለም ከሁሉም ታቅቦ ፍትሕን ከእግዚአብሔር እየጠየቀ ይኖራል። በዚህ ጊዜ ምርመራ አጣርቶ ክስ የሚመሰርት የዐቃቤ ሕግ ተቋም በሀገሪቱ አልነበረም። በግለሰቦች መሀከል የሚፈጠር አለመግባባቶችን ‹‹የወንጀል›› ጉዳይ እና የግለሰቦች የፍትሐብሔር ጉዳይ ብሎ የሚከፋፍል የሕግ ስርአት ባለመኖሩ ጥቂት በሀይማኖትና በመንግስት ላይ የሚፈፀሙ በአሁኑ ሰአት የፓለቲካ ወንጀል እየተባሉ ከሚጠሩ ወንጀሎች በስተቀር ሁሉም አለመግባባቶች ላይ ግለሰቦች በራሳቸው ከሳሽ በመሆን ጉዳያቸውን ለፍርድ ቤት ያቀርባሉ ወይም ፍትሕን በእጃቸው ያገኙ ነበር። ጉዳያቸውን ወደ ፍርድ ቤት የሚወስዱ ከሆነ ክስ የመመስረት፣ የተጀመረን ክስ የሟቋረጥ፣ ቅጣትን በመምረጥ ተበዳይ ግለሰብ ሁሉን አድራጊ ነበር። የወንጀል ይዘት ያላቸው ጉዳዮችን ከፍትሀብሔር ጉዳዮች ጋር በማጣመር የጉዳት ካሳን መጠየቅም ይቻል ነበር። በዘመኑ የወንጀል ተበዳዮች በወንጀል ጉዳይ የሉአላዊ ስልጣን ባለቤቶች ነበሩ።

Continue reading
  199 Hits

የግል አቤቱታ የማቅረብ መብት በጠቅላላው

 

መግቢያ

የሥነ-ሥርዓት ሕግ ሰዎች መሠረታዊ የሆኑ የፍትሕ አቤቱታዎች ሲቀርቡ የሚመሩበትን እና መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች በሚመለከታቸው የፍትሕ አካላት የሚወስኑበትንና ተፈፃሚ ሊሆኑ የሚችሉበትን ሥርዓት የሚያሳይ ጽንሰ ሀሳብ ነው። የሥነ-ሥርዓት ሕግ መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች በምንና እንዴት ባለ አኳኋን ወደ ተግባር ሊፈፀሙ እንደሚችሉ የሚዘረዝር የሕግ ክፍል ነው። የእነዚህን መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች ይዘትና አይነት ተንትኖ የሚያቀረበው የሕግ ክፍል መሠረታዊ ሕግ (Substantive Law) ተብሎ የሚጠራ ነው። መሠረታዊ ሕግ የሰው ልጆችን መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች በግልፅ የሚደነግግ በመሆኑ ጠቀሚታው ከፍተኛ እንደሆነ ይታመናል። ይሁን እንጅ እንዚህ ዝርዝር መብቶችና ግዴታዎች በተግባር ተፈፃሚ እንዲሆኑ ካልተደረገ የመኖራቸው ጉዳይ ትርጉም የለሽ ይሆናል ማለት ነው። እነዚህ መደበኛና ልዩ መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች እንዲፈፀሙ የማድረጉ ሐላፊነት የሥነ-ሥርዓት ሕግ ቢሆንም ውጤታማ የሥነ-ሥርዓት ሕግ ከሌለ ግን መብቶችንና ግዴታዎችን የማስፈፀሙ ዓላማ እረብ የለሽ ይሆናል። ለዚህም ነው የሥነ-ሥርዓት ሕግ ከመሠረታዊው ሕግ ባላነሰ አስፈላጊና ጠቃሚ ነው የሚባለው።

በግልፅ መረዳት እንደሚቻለው ለትክክለኛ ፍትሕ አሰጣጥ የሥነ-ሥርዓት ሕግ ያለው አስተዋፆ በጣም ከፍተኛ ነው። የሥነ-ሥርዓት ሕጉን ዓላማና መንፈስ መከተል ተከትሎም ተፈፃሚ ማድረግ በራሱ ፍትሕን ማረጋገጥ ነው የሚሆነው። የፍትሕ ጉዳይ ‹‹የትም ፍጪው ዱቂቱን አምጭው›› የምንለው ነገር ሣይሆን ከመነሻው እስከ መዳረሻው ያለውን ሂደትና ሥርዓት በመከተልና በመተግበር የሚገኝ ፍርድ ስለሆነ የሥነ-ሥርዓት ሕጎችን እውቀት ማሳደግ ለትክክለኛ ፍትሕ አሰጣጥ ቁልፍ ሚና አለው።

የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥዓት የወንጀል ጉዳዩች የሚመሩበት የሚከሰሱበት የሚዳኙበት የሚቀጡበትን  ሥርዓቶች  የሚገዙ ደንቦች  ናቸው።  ይህም  ትንሽ  የማይባሉትን የመሠረታዊ ወይም የዋና መብቶች ደረጃ አግኝተው በሕገ-መንግስት እና  በዓለም-አቀፍ  ኮቬናንቶች ጥበቃና  አውቅና  ያገኙትን የተከሣሾች የሥነ-ሥርዓት መብቶች ያካትታል። 

Continue reading
  16455 Hits

Victim Oriented Measures under Ethiopian Anti-Human trafficking Law

“Violations of human rights are both a cause and a consequence of trafficking in persons.”

                                      UN human rights office of the High Commissioner, fact sheet 36

 Introduction

Traditionally, People in Ethiopia feel that living abroad is life changing and take it as a privilege. In country sides there is customarily mainstreamed saying that እልፍ ቢሉ፤እልፍ ይገኛል/ Eliff bilu elf yignagal” meaning that if somebody changes a living place she or he will get a decent life counted in thousands. That’s why many peoples in Ethiopia left their home and searching jobs abroad via illegal means and fall in the hands of satanic and barbaric traffickers in turn witnessed dozens of sufferings.

To begin with, trafficking in persons, especially women and children, is increasingly becoming an issue of global concern. It is evident that the fons et origo of human trafficking problem at the international arena at least dates back to the Paris conference on trafficking in women held in 1895.

Continue reading
  11090 Hits

እያመለጠ ያለን የጊዜ ቀጠሮ እስረኛ ተኩሶ መግደል በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ

 

መግቢያ

አንድ ሰው ወንጀል በመስራት በመጠርጠሩና የተጠረጠረበት ወንጀል በሕጉ ዋስትና የማያስፈቅድ በመሆኑ ወይም በዋስትና ለመውጣት አስፈላጊ የሆኑት ነገሮች እስኪከናወኑ ጊዜ ድረስ በእስር ላይ ሊቆይ ይችላል፡፡ በዚህ ጊዜ እስረኛው በሕጉ የተፈቀደለት የሰብአዊ ክብር እንክብካቤና በሕይወት ለመቆየት አስፈላጊ የሆኑ ነገሮች በሙሉ እየተሟሉለት የፍርድ ሂደቱን የመከታተል መብት አለው፡፡ እስረኛው በፍ/ቤት ወንጀለኛ ተብሎ ያልተፈረጀ ይልቁንስ በህገመንግስቱ አንቀፅ 20/3/ መሠረት ንፁህ ሆኖ የመገመት መብት ያለው በመሆኑ ተገቢው ክብርና እንክብካቤ የሚገባው ነዉ፡፡

የዚህ ጽሑፍ መነሻ በአንድ በተጠረጠሩበት ወንጀል ምክንያት የታሰሩ ሰዎች የታሰሩበት እስር ቤት በራሳቸው ባልሆነ ጥፋት በእሳት እየተቃጠለ በመሆኑ ምክንያት ከሚነደው የእሳት ቃጠሎ ራሳቸውን ለማዳን ሲሉ በሕግ ወንጀልነቱ የተደነገገ ሌላ ወንጀል ፈፅመው ቢገኙ ለምሳሌ ከታሰሩበት እስር ቤት ለማምለጥ ቢሞክሩ የእስር ቤቱ ጠባቂ ይህን የማምለጥ ድርጊት ለማቆም የሚወስደው የግድያ ተግባር በወንጀል ሕጉ መሠረት ያለውን ህጋዊነት መፈተሽ ነው፡፡

ቅጣት አልባው ወንጀል

Continue reading
  25051 Hits
Tags:

ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት መስጠት (የግዴታ ሥራ) እንደ ወንጀል ቅጣት

 

ጣልያንን ለዘጠኝ ዓመታት የመሩት የቀድሞው የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የኤሲ ሚላን እግር ኳስ ክለብ ፕሬዚዳንትና ባለቤት እንዲሁም ቢሊየነሩ ሲልቪዮ ቤርሎስኮኒ በተከሰሱበት የታክስ ማጭበርበር ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው በሚላን ከተማ የሚገኘው ፍርድ ቤት ቤርሎስኮኒ የአራት ዓመታት እስራት ቢፈረድባቸውም የእስራት ቅጣቱ በተለያዩ ምክንያቶች ቀርቶ በተቃራኒው ቤርሎስኮኒ በአረጋውያን ማቆያና መንከባከቢያ ማዕከል ውስጥ ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት እንዲሰጡ እ.ኤ.አ. በ2013 መወሰኑ ይታወቃል፡፡ በውሳኔው መሠረትም ቤርሎስኮኒ ሴሴኖ ከተማ ውስጥ በሚገኘውና ከ2000 በላይ በእድሜያቸው የገፉ፣ የአእምሮና የአካል ጉዳተኛ የሆኑ አረጋውያን በሚገኙበት ማዕከል ውስጥ ለአንድ ዓመት ያህል በሳምንት ለአራት ሠዓታት በማዕከሉ እየተገኙ አረጋውያኑን እንዲመግቡ፣ እንዲንከባከቡ፣ እንዲያንሸራሽሩ እንደ አጠቃላይም በማንኛውም መልኩ ከአረጋውያኑ ጎን እንዲሆኑ ተወስኖባቸው ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎቱን ፈፅመው አጠናቀዋል፡፡        

ታዋቂው አሜሪካዊ የሙዚቃ አቀንቃኝ ቦይ ጆርጅም በመኖሪያ ቤቱ የኮኬይን ዕፅ ይዞ መገኘትና በሀሰት የመኖሪያ ቤቴ ተዘርፏል በሚል ካቀረበው የሀሰት ጥቆማና ሪፖርት ጋር በተያያዘ እ.ኤ.አ. በ2006 በማንሀተን የወንጀል ችሎት ጥፋተኛ ከተባለ በኋላ የተወሰነበት ቅጣት ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት እንዲሰጥ ይኸውም በኒውዮርክ ከተማ ለአምስት ቀናት ያህል የከተማዋን መንገዶች እንዲያፀዳ ሲሆን ከኒውዮርክ ከተማ የፅዳት አገልግሎት ክፍል ጋር በመሆን የከተማዋን አውራ ጎዳናዎች ለአምስት ቀናት ያህል በማፅዳት ቅጣቱን ፈፅሟል፡፡

ሆላንዳዊው የእግር ኳስ ተጫዋች የነበረውና ለአያክስ አምስተርዳም፣ ኤሲ ሚላንና ባርሴሎና እግር ኳስ ክለቦች ተጫውቶ ያሳለፈው ፓትሪክ ክላይቨርትም የ19 ዓመት ወጣት በነበረበትና ለአያክስ አምስተርዳም እግር ኳስ ክለብ በሚጫወትበት ወቅት በአምስተርዳም ከተማ ከፍጥነት ወሰን በላይ መኪና ሲያሽረክር ባደረሰው የመኪና አደጋ የቲያትር ዳይሬክተር የነበሩ የ56 ዓመት ጎልማሳ ሕይወታቸው እንዲያልፍ በማድረጉ በፍርድ ቤት ጥፋተኛ ተብሎ ዕድሜው ገና 19 ዓመት የነበረና ተስፈኛ ስፖርተኛ መሆኑ ከግምት ገብቶ የተጣለበት የሶስት ወራት የእስራት ቅጣት በሁለት ዓመት የፈተና ጊዜ እንዲገደብ፣ ለ18 ወራት መኪና ከማሽከርከር እንዲታቀብ እና ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት እንዲሰጥ ተወስኖበታል፡፡ በሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎቱም ፓትሪክ ክላይቨርት ለ240 ሰዓታት ታዳጊ ሕፃናትን በእግር ኳስ ስፖርት እንዲያሰለጥንና ለሕፃናቱ መልካም አስተዳደግ አስተዋፅኦ እንዲያደርግ ተወስኖበት ቅጣቱን መፈፀሙም ይታወቃል፡፡ ከእነዚህ ሠዎች በተጨማሪ ሌሎች ሠዎችም ለፈፀሙት የወንጀል ድርጊት ቅጣት እንሆን ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት እንዲሰጡ ሲወሰንባቸው ይታያል፡፡     

ለመሆኑ የወንጀል አጥፊዎች ላይ የሚጣሉ ቅጣቶች ምን ዓይነት ናቸው? ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት መስጠት ወይም የግዴታ ስራ ምን ዓይነት ቅጣት ነው? ዓላማውስ ምንድን ነው? በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግስ ሽፋን ተስጥቶታል ወይ? ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት መስጠት ወይም የግዴታ ስራ የሚወሰነው ምን ምን ሁኔታዎች ሲሟሉ ነው? ስንት ዓይነት የግዴታ ስራዎች አሉ? ፍርድ ቤቶችስ የግዴታ ስራን አስመልክቶ በሕግ ተለይቶ የተሰጣቸው ሥልጣን ምንድን ነው? ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት መስጠት ወይም የግዴታ ስራን አስመልክቶ የሚስተዋሉ ችግሮችና መፍትሔዎቻቸው ምንድን ናቸው? የሚሉና ተያያዥ ነጥቦችን በዚህ ፅሁፍ በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡

Continue reading
  15093 Hits

ቅጥ አልባ ቅጣቶች በኢትዮጵያ ሕጎች    

             

መግቢያ

ከጥንት ጀምሮ እስከዛሬ ወንጀል የዚች ዓለም እውነት ነው፡፡ ቃኤል አቤል መግደሉ ከተሰማበት ይህን ጽሑፍ እርሶ እያነበቡ እስካሉት ቅፅበት ድረስ ወንጀል በሰው ልጆች ላይ በሰው ልጅ በራሱ ይፈፀማል፡፡ ይህ ከሰው ልጆች ታሪክ ጋር መሳ የሆነ ታሪክ ያለው ወንጀል ወደፊትም ማቆሚያ የሚኖረው አይመስልም፡፡ የሰው ልጅ ማድረግ የቻለው  ወንጀል የሚቀንስበትን አማራጭ መዘየድ እንጂ ወንጀል አልባ ዓለም መፍጠር አይደለም፡፡ ምናልባትም ወንጀል የመቀነስ ሙከራውም ተሳክቶ እንደሆነ እንጃ፡፡

ወጣም ወረደ ሁሉም ማህበረሰብ እንደ ማህበረሰቡ ታሪካዊና ማህበራዊ ዳራ ራሱን ከወንጀል ለመከላከል በዋናነት የዘየደው መላ ቅጣት ነው፡፡ የዚህ ጽሑፍ ማጠንጠኛም የወንጀል ቅጣት በኢትዮጵያ ሕግ ያለውን መልክ በመጠኑ ከጠቅላላ የቅጣት መርሆች አኳያ በመቃኘት በአሁኑ ሰዓት እርስ በእርሳቸው ተናባቢነት የሌላቸው በተመሳሳይ ጉዳይ የተለያየ ቅጣት የያዙ፣ ለቀላል ወንጀል ከባድ ቅጣት ለከባድ ወንጀል ቀላል ቅጣት የደነገጉ  በግብታዊነት እዚህም እዚያም ቅጣትን እንደ ተራ የመንገድ ጨቃ እያነሱ የሚለጥፉ ሕጎች ከወንጀል ጠቅላላ ዓላማና ግብ አኳያ በአጭሩ መፈተሸ ነው፡፡

የወንጀል ሕግ ዓላማ

Continue reading
  16758 Hits

ተከላካይ ጠበቃ ስለማግኘት መብት ጥቅል እይታ

 

መግቢያ

በአሁኑ ወቅት በስፋት ተቀባይነት ካገኙ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎች በወንጀል ተከሰው ለጠበቃ የመክፈል አቅም ለሌላቸው ሰዎች የሕግ  ድጋፍ መስጠት አንዱ ነው። በመሆኑም ተከላካይ ጠበቃ የማግኘት መብት የተከሰሱ ሰዎች ካሏቸው ሕገ-መንግስታዊ  መብቶች ቀዳሚው ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ለምን ቢሉ በዓለማቀፋዊም ይሁን በአሕጉራዊ ስምምነቶች እንዲሁም በዝርዝር ብሄራዊ ሕጎች እውቅና የተሰጣቸውና ጥበቃ የሚደረግላቸው የተከሰሱ ሰዎች መብቶች የሚከበሩበት በመሆኑ ነው።

የተከሰሱ ሰዎች ፍርድ ቤት ሲቀርቡ ሊከበሩላቸው የሚገቡ በርካታ መብቶች አሏቸው። ከእነዚህ ውስጥ በዳኝነት አካላት ፊት በእኩልነት የመታየት፣ ጥፋተኝነታቸው እስካልተረጋገጠ ድረስ ንፁህ ተደርገው የመገመት፣ ፍትሀዊ በሆነና በግልጽ ችሎት የመዳኘት፣ የተፋጠነ ፍርድ የማግኘትና ይግባኝ የማቅረብ መብቶች ይገኙበታል። በተጨማሪም ክሱን በጽሁፍ የማግኘት፣ ተከሳሾች በራሳቸው ላይ ያለመመስከር፣ የመከላከያ ምስክሮችንና ማስረጃዎቻቸውን የማቅረብ፣ ለአቃቤ ሕግ ምስክሮች መስቀለኛ ጥያቄ የማቅረብ፣ እንዲሁም በመንግሥት እጅ የሚገኙ ማስረጃዎችን የማግኘት መብቶቻቸውም ሳይጠቀሱ የማይታለፉ ናቸው።

ይሁን እንጂ እነዚህ ሁሉ በበርካታ ሕገ-መንግስታት፣ በዓለማቀፋዊና በአሕጉራዊ የሰብአዊ መብት ስምምነቶች እውቅና ያገኙ መብቶች ብዙውን ጊዜ ሲከበሩ ሳይሆን ሲጣሱ ነው የሚታየው። ይህም የሚሆነው ለእነዚህ መብቶች መከበር መሰረታዊ የሆነው የተከሰሱ ሰዎች ተከላካይ ጠበቃ የማግኘት መብት ሕጉ ላይ በተቀመጠው ልክ በተግባር እየተፈጸመ ባለመሆኑ ነው።

Continue reading
  14422 Hits

ስለ “የታሰሩ ሰዎች መብቶች” አንዳንድ ነጥቦች

 

በማያ ጋዜጣ ሐምሌ የታተመ በሰሞኑ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የችሎት ውሎዎች በፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ እና በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የጋራ የወንጀል ሕጉን የማስፈጸም ተግባር ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ የተለያዩ መንግስታዊ መሥሪያ ቤቶች ዳይሬክተሮችን ጨምሮ በሙስና ወንጀል ተጠርጣሪነት ተይዘው የጊዜ ቀጠሮ እየተጠየቀባቸው የሚገኙት እስከ ሣምንቱ አጋማሽ ድረስ ቁራቸው 45 የደረሱ ተጠርጣሪዎች በእሥር ላይ የሚገኙ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ የሕግ እርምጃው ቀጣይነት ያለው መሆኑንም በመንግስት መገናኛ ብዙሃን በኢቢሲ መግለጫ ተነግሯል፡፡ የተጠርጣሪዎችን በእሥር ላይ መዋል ተከትሎ በመንግስትም ሆነ በግል መገናኛ ብዙሃን ተጠርጣሪዎቹ ፈጽመውታል ተብሎ ስለተጠረጠሩበት ወንጀል ዝርዝር የገንዘቡን መጠን ጨምሮ በስፋት ሲዘገብ እየተመለከትንና በጋዜጦች እያነበብን ነው፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዎቹን በሕግ መሠረት በቁጥጥር ሥር አውሎ፣ ክስ አቅርቦ ጥፋተኝነታቸው በማስረጃ የተረጋገጠባቸውን በህጉ መሠረት እንዲቀጡ ማድረግ መሰረታዊ የህግ ዓላማ እንዲሁም አንደኛው የሕግ አስፈጻሚዎች ሥልጣንና ተግባር ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በእሥር ላይ የሚገኙት ተጠርጣሪ እሥረኞችን ሕገመንግሥታዊ መብቶችን የማክበሩ ጉዳይም ከተጠያቂነቱና የወንጀል ህጉን ከማስፈጸሙ እኩል ጎን ለጎን ትኩረትን የሚሻ ነው፡፡ የሰዎች መብቶችና ግዴታዎች ሁል ጊዜ ጎን ለጎን በትይዩ የሚፈጸሙ መሆናቸው መሠረታዊ የህግ መርህ ነው፡፡ 


ከላይ የተጠቀሱትን ተጠርጣሪዎችን ጨምሮ ካሁን በፊት በሙስናም ሆነ በሌሎች ወንጀሎች ተጠርጥረው በእሥር ቤት/ በማረሚያ ቤት በሚገኙ ተከሳሾች የፍርድ ቤት ችሎት ውሎዎች የታሰሩ ሰዎችን መብቶች በተመለከተ የሚነሱ ዘርፈ ብዙ የመብት ጥያቄዎች፣ የመብት ጥሰት አቤቱታዎችና ክርክሮች ተደጋግመው ሲነሱ ይስተዋላል፡፡ የዛሬው የጽሁፋችን ርእስና ጭብጥ ሆኖ የተመረጠው ይህንኑ የእስረኞችን መብት ጉዳይ የሚመለከት ነው፡፡ በኢፌዲሪ ሕገመንግስት ከአንቀጽ 13 እስከ 44 ስለ ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ከተደነገጉት መካከል በአንቀጽ 21 ሥር በጥበቃ ሥር ያሉና በፍርድ የታሰሩ ሰዎች መብት ከሰብአዊ መብቶች መካከል አንደኛው ሕገመንግስታዊ መብት መሆኑን ተደንግጓል፡፡ 
የሕገመንግስቱ አንቀጽ 21 ሁለት ንዑሳን ድንጋጌዎች እንደሚከተለው ይነበባሉ፡- 
(1) በጥበቃ ሥር ያሉና በፍርድ የታሰሩ ሰዎች ሰብዓዊ ክብራቸውን በሚጠብቁ ሁኔታዎች የመያዝ መብት አላቸው፡፡

(2) ከትዳር ጓደኞቻቸው፣ ከቅርብ ዘመዶቻቸው፣ ከጓደኞቻቸው፣ ከሃይማኖት አማካሪዎቻቸው፣ ከሐኪሞቻቸው እና ከሕግ አማካሪዎቻቸው ጋር ለመገናኘትና እንዲጎበኟቸውም ዕድል የማግኘት መብት አላቸው፡፡

ለመሆኑ የታሰሩ ሰዎች ምን መብት አላቸው? መብቶቻቸውስ በየትኞቹ የሀገራችን ህግጋት ጥበቃ ተደርጎላቸዋል? የመብት ጥበቃውስ ከማን ነው? ጠባቂውስ ማን ነው? የት፣ መቼና እንዴትስ ይጠበቃል? ጽሁፉ እንዚህንና ተያያዥ ጭብጦችን ይዳስሳል፡፡

Continue reading
  12267 Hits

ስለቀዳሚ ምርመራ (Preliminary Inquiry) ፍርድ ቤት ተልዕኮ፣ ሥልጣን እና ተግባር

 

መግቢያ

በዘመናዊ አሠራር የወንጀል ጉዳይን እንዲከታተል የተቋቋመ እያንዳንዱ መሥሪያ ቤት ለፍርድ ሊቀርቡ የሚገባቸውን ጉዳዩች አይነትና ብዛት ለመለየት የሚያስችለው ሥነ ሥርዓት ይቀይስለታል፡፡ ይህ እንዲሆን የሚያሰፈለገውም በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ነው፡፡ አንደኛ አንድ ሰው ወንጀል ሰርተሃል ተብሎ በሚከሰሰበትና ለፍርድ በሚቀርብበት ጊዜ ብዙ ችግር ሊገጥመው እንደሚችል የታወቀ ነው፡፡ በወንጀል ተግባር ተከሶ ለፍርድ የሚቀርብ ሰው የሚደርስበት የማሕበራዊና የኢኮኖሚያዊ ቀውስ በጣም ከፍተኛ ነው፡፡ ስለዚህ የዚህ አይነቱ ከባድ ጉዳት ሊደርስ የሚገባው በእርግጥ ወንጀል በሰሩና ወንጀል ለመስራታቸውም የማያጠራጠር ማስረጃ በቀረበባቸው ሰዎች ላይ መሆን አለበት፡፡ አንድን ሰው ወንጀል ሰርተሃል ብሎ መክሰስና በማሕበራዊ ኑሮ ውስጥ ያለውን ክብር ዝቅ ማድረግ ቀላል ነው፡፡ ክሱን በማስረጃ ማረጋገጥና ተከሣሹን ጥፋተኛ ማስደረግ ግን በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ ስለዚህ በማስረጃ ሊረጋገጡ የማይችሉ ወንጀሎች በተቻለ መጠን በአጭሩ መቋጫ እንዲያገኙ ማድረግ የመንግሥት ሃላፊነት ነው፡፡

ሁለተኛ የወንጀልን ጉዳይ በፍጥነት ውሣኔ ማሰጠት ሲገባ በልማድ እንደሚታየው ግን ይህን ማድረግ እንዲህ ቀላል ሆኖ አልተገኘም፡፡ በማንኛውም አገር እንደሚታየው የወንጀል ሥራ በየአቅጣጫው እየጨመረ በመሄድ ላይ የሚገኝ ቢሆንም እንኳን ሁሉንም ወንጀል አድራጌዎች ወዲያውኑ ወደ ፍርድ ቤት ለማቅረብና ለማስቀጣት አይቻልም፡፡ ከወንጀሎቹ ብዛት አንፃር ሲታይ ደካማወቹ ጉዳዩች በአጭሩ የሚቋጩበት ዘዴ መኖር አለበት፡፡ ከማስረጃ አኳያ ጠንካራዎቹን እና ደካማዎቹን ጉዳዩች የምናጣራበት ዘዴ ቀዳሚ ምርመራ በመባል ይታወቃል፡፡ ይህ ጠንካራዎቹን እና ደካማዎቹን ጉዳዩች የማበጠሩና የመለየቱ ተግባር እንደየ አገሩ የሕግ ሥርዓት ለዐቃቤ ሕግ ወይም ለመርማሪ ዳኛ (investigating Judge) ወይም የሕግ ሙያ ለሌላቸው እማኝ ዳኞች (Grand juries) ሊሰጥ ይችላል፡፡ ከፖሊስ የምርመራ መዝገብ የደረሰው ዐቃቤ ሕግ ጉዳዩ በቀዳሚ ምርመራ አድረጌ ፍርድ ቤት መጣራት የሚገባው ሆኖ ካገኘው ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን እንዲያጣራ ሊያዝ ይችላል፡፡ ዐቃቤ ሕግ ጉዳዩ ለቀዳሚ ምርመራ አድራጊ ፍርድ ቤት እንዲቀርብ ትዕዛዝ የሚሰጠው ምን ምን ሁኔታዎች ተሟልተው ሲገኙ ነው? ጉዳዩ ለቀዳሚ ምርመራ አድራጊ ፍርድ ቤት ሣያቀርብ በቀጥታ ክሱን በዳኝነት ለማየት ሥልጣን ላለው ፍርድ ቤት ቢያቀርብ ሊመጣ የሚችለው ውጤት ምንድን ነውየቀዳሚ ምርመራ አድራጊ ፍርድ ቤት ሥልጣን ተግባርና ዓላማ ምንድን ነው?

ከላይ ለቀረቡት ጥያቄዎች አጥጋቢ ምላሽ ለማገኘት ቀዳሚ ምርመራን (ቀዳሚ ምርመራ (Preliminary Inquiry) በሌሎች ሐገራት Preliminary Hearing, Preliminary Examination ወይም Examining Trial በመባል ይጠራል) አስመልክቶ በሌሎች ሐገራት ያለውን የሕግ ማዕቀፍ ይዘትና አሠራር በቅድሚያ መመልከት አስፈላጊ ነው፡፡

Continue reading
  12642 Hits

"በሕግ አግባብ"ያለአግባብ ስለመታሰር

 

ካሳ አልባ የፍትሕ ሥርዓቱ ተጎጂዎች

እንዲያው አያድርገውና በወንጀል ተጠርጥረው ጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆብዎ አስቸጋሪውን የወንጀል ምርመራ ተቋቁመው ካለፉ በኋላ በዓቃቤ ሕግ ተከሰው የዋስትና መብትዎን ተከልክለው ክራሞትዎ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሆነ እንበል፤ በሕግ ጥላ ሥር፡፡

የፍርድ ቤት ቀጠሮዎት በደረሰ ጊዜ እጅዎ በካቴና ተጠፍንጎ ወይም ከሌላ እስረኛ ጋር ተቆራኝቶ ጠመንጃ በወደሩ ፖሊሶች በአይነ ቁራኛ እየተጠበቁ ለወራት ወይም ለዓመታት ነጻነትዎ ተነፍጎ የፍርድ ሂደቱን ሲከታተሉና ሲሟገቱ ከባጁ በኋላ በመጨረሻ ጉዳይዎትን ይመለከት የነበረው ዳኛ የችሎቱን ጠረጴዛ በመዶሻው ግው! በማድረግ ‹‹ከተከሰሱበት ወንጀል በነፃ ተሰናብተዋል ቅንጣት ያህል ጥፋት የለብዎትም›› ብሎ ቢያሰናብትዎ ምን ይሰማዎታል???

እርግጥ ነው፣ ተሟግተው በማሸነፍዎና ንጹህነትዎን በማስመስከርዎ አልያም የእሥር ህይዎትዎ በማክተሙና ፀሐይቱን ያለ አንዳች ከልካይና ተቆጣጣሪ እንዳሻዎ ሊሞቋት በመብቃትዎ ደስታ እና እፎይታ እንደሚሰማዎ አያጠራጠርም፡፡

Continue reading
  11505 Hits