የሁለት ኢትዮጵያውያን ወግ: የቀድሞውና አዲሱ ኢትዮጵያዊነት በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት ሊታረቅ ይችላል ወይ?

የዛሬ ሳምንት "የሁለት ኢትዮጵያውያን ወግ፡ የቀድሞውና አዲሱ ኢትዮጵያዊነት በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት ሊታረቅ ይችላል ወይ?" በሚል ርእስ ላይ ንግግር (public lecture) አድርጌ ነበረ። ንግግሩ እንደወረደ ነበረ፣ በኋላ አዘጋጁ የሬይ ዊተን ፎረም አጠር ያለ መግለጫ ስጠን ብለውኝ እንደምንም (የማስታውሰውን) ፃፍኩት። የሥራ ጥድፊያ ምናምን ስለነበረ በጽሑፉ አልረካሁም፣ እንዳወራሁት አልሆነም ቢሆንም ብዙ ጓደኞቼ በቦታው ባትኖሩም ለምን እንደብቃለን ብለን እነሆ ጀባ ብለናል፡፡ 

አገራችን ኢትዮጵያ ዜጎቿ (በተለይ ልሂቃኑ) ለሁለት ተከፍለው ሁለቱም የየራሳቸውን ትክክለኛ ኢትዮጵያዊነት ነው የሚሉትን ማንነት አንዱ በሌላው ላይ እና በአጠቃላይ በሕዝቡ ላይ ለመጫን እየሞከሩ ነው። አንዱ ሌላውን በማንኛውም መንገድ ለመርታት ስለሆነ ትግላቸው የመጠፋፋት ፖለቲካ ነው የያዙት። አንደኛው ወገን ከጥንት እስከ ደርግ መንግሥት ድረስ የዘለቀውን ኢትዮጵያዊነት እንደ እውነተኛ ይወስዳል። ሁለተኛው ደግሞ አሁን በተለይ ከኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት በኋላ የተፈጠረውን ኢትዮጵያዊነት እንደ እውነተኛ ይቆጥራል። አንደኛው ሁለተኛውን በታኝ፣ ከፋፋይ፣ የረጅም ዘመን አኩሪ ታሪካችንን የካደ እና ያዋረደ ነው ይለዋል። በተጨማሪም ብሔር ወይም ጎሳ ዘመናዊ ያልሆነ ጥንታዊና ለሰው በሰውነቱ እውቅና እንዲሁም ክብር የማይሰጥ ኋላቀር መገለጫ ነው ይላል። ስለዚህ ሕገ መንግሥት የግለሰብ ነፃነትን ብቻ ማስከበር ሲገባው የጋራ በተለይ የብሔር መብት ማካተቱ ያለተገባና የግል ነፃነትን ለመጨፍለቅ ያለመ ነው ብሎ ያምናል። ሁለተኛው አንደኛውን በጨቋኝነት ወይ ለጨቋኞች ሥርዓት ተቆርቋሪነት ይከሰዋል። የቀድሞው ኢትዮጵያዊነት የብሔሮችን ማንነት የካደ፣ ንብረታቸውን የዘረፈ፣ ልጆቻቸውን የገደለ፣ ግፈኛ እና በግድ የተጫነ ነው ይለዋል። ስለዚህ የአገሪቱ ችግር በዋናነት የብሔር ጭቆና በመሆኑ እሱን የሚያስወግድ በብሔሮች ነፃ ፈቃድ ላይ የተመሠረተ አዲስ ኢትዮጵያዊነት በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት ተፈጥሯል ብሎ ያውጃል። የግለሰብ ነፃነት ቢኖርም ከዛ ይልቅ የጋራ መብቶች ላይ ትኩረቱን በማድረግ የሕገ መንግሥቱን ልደት እንኳ በብሔር ብሔረሰቦች ቀን ተሰይሟል። ግለሰቦች የግድ በብሔር አማካኝነት ኢትዮጵያዊ የሚሆኑ ተደርጎ ይወሰዳል። በአጠቃላይ አንዱ ሌላውን እውነተኛ ኢትዮጵያዊ እንዳልሆነ እና ጠላት እንደሆነ ይወተውታል፣ ለማጥፋትም ተግቶ ይሠራል።

የእነዚህ ኢትዮጵያዊ ማንነቶች ትልቅ ስህተት አንዱ በአንዱ ላይ አሸናፊ ለመሆን መሞከራቸው ነው። በተጨማሪ ሁለቱም ስለሕገ መንግሥት የተሳሳተ ግንዛቤ ይዘዋል። ሕገ መንግሥት የግል እና የጋራ መብቶችን አንድ ላይ ያከብራል፣ በምዕራፍ ሦስት ሳያበላልጥ እኩል ክብር ይሰጣቸዋል። በዛ ላይ ሕገ መንግሥት የሕጎች ሁሉ የበላይ ስለሆነ እራሱ ካላዘዘ በቀር በአንቀፆቹ መካከል ማበላለጥ የበላይነቱን መካድ ነው። ሌላው መብቶች የጋራ መሠረተ ሐሳብ አላቸው፣ ይኸውም የመምረጥ እና የአማራጭ ነፃነት (freedom of choice) ነው። ሁሉም ሰው እኩል ነው። ስብእናውን፣ እድሉን፣ እምነቱን፣ ከሌሎች ጋር የሚኖረውን ግንኙነት እንዲሁም ማንነቱን የመምረጥ ወይ የመወሰን ሥልጣን ወይ ነፃነት አለው። ይሄ በተለያዩ መብቶች ውስጥ ይገለፃል። ስለዚህ ብቸኛው ወሳኝ እራሱ ግለሰቡ ብቻ ነው። ሐይማኖት ይኑረው አይኑረው፣ ካለው የትኛው ይሁን የሚለውን የሚወስነው ግለሰቡ ነው። ይህ የሐይማኖት ነፃነት ነው። ይናገር ወይ ዝም ይበል መወሰን የመናገር ነፃነቱ ነው። ስለዚህም ማንነቱን መወሰን፣ በብሔር ይሁን በሌላ መገለጫ ይሁን ብሎ መወሰን የግለሰቡ ነፃነት ነው። የብሔር ማንነት ከመረጠ ግን እሱ ሊከበር የሚችለው በጋራ ተመሳሳይ ማንነት ካላቸው ጋር ነው። ምክንያቱም በዛ ውስጥ ያሉት መብቶች የባህል፣ የቋንቋና ራስን በራስ የማስተዳደር ስለሆኑ ነው። የግል መብቶች፣ ለምሳሌ የመዘዋወር እና በፈለጉበት የመኖር መብት በመላ አገሪቱ ሲከበር የጋራ መብት የሆነው የብሔር ማንነት መብት ግን ብሔሩ በሰፈረበት አካባቢ የተወሰነ ነው። ግን መጀመሪያ ላይ የመወሰን ነፃነቱ ግለሰባዊነቱ የተከበረ ነው፣ ምሳሌ ሐይማኖት ይኑረኝ አይኑረኝ ወይም ምንነቱን ብጠየቅ ያለመመለስ መብት እንዳለኝ ሁሉ ለብሔር ወይ ሌላ ማንነትም ተመሳሳይ ነው። ስለዚህ መንግሥት በየመሥሪያ ቤቱ የሚጠቀማቸው ፎርሞች በግለሰቦች ሲሞሉ ሐይማኖት እና ብሔር የሚሉ ቦታዎች የግድ መሆን አይችሉም። ለግለሰቡ ምርጫ የተተዉ ናቸው። ሲፈልግ ብሔር የለኝም፣ ወይ አለኝ ካለ ብሄሩን፣ ካሰኘው ኢትዮጵያዊ፣ አሊያም ዝም ማለት መብቱ ነው። ይሄን የሚቃረን አንድም አንቀፅ ወይ እንድምታ በሕገ መንግሥቱ የለም። የመዘዋወር ነፃነት እና የመምረጥ ነፃነትን ያለ ምንም የብሔር ቅድመሁኔታ ተፈፃሚ የሚሆኑ መብቶች (የብሔር መብት ገደብ) ናቸው፣ የእኩልነት መብት ለሁሉም መብቶች እንደሚሠራም መረዳት ያስፈልጋል።

በዚህ አረዳድ ከሄድን አሁን በሥራ ላይ ባለው ሕገ መንግሥት ሁለቱ ኢትዮጵያውያን ሊስማሙ ወይ ሊታረቁ ይችላሉ። ዋናው የሚያስወግዱት ማስገደድን ነው። በግለሰብ ወይ በሕዝብ ላይ አመለካከቱን ለመጫን መሞከር ነው የኢትዮጵያዊያን ትልቁ ችግር። ባየነው መሠረት ደግሞ የነፃነት ተፃራሪ ማስገደድ ነው፣ በማንኛውም መልኩ ሰውን ማስገደድ ክልክልም ነው። የፈለግነውን ኢትዮጵያዊ ማንነት ይዘን መቀጠል መብታችን ነው። የቀድሞው ታሪካችንን በግልፅ እየተወያየን፣ በሚያኮራው እየኮራን፣ በሚያሳፍረው እያፈርን፣ ከአሁኑ ማንነታችን የተነጠለ ሳይሆን አንድ ወጥ ታሪክ በተለያየ ምእራፍ እንደሆነ መገንዘብ ተገቢ ነው።

ይህ አረዳድ በኢትዮጵያ ማንኛውም ዜጋ በአመለካከቱ ወይም በማንነቱ ምክንያት እንዳይገለል፣ ታሪክን ለማረም ሌላ ታሪካዊ ስህተት እንዳይደገም ይረዳል። ሌላው እስካሁን ሕገ መንግሥትን የገዥው ፓርቲ አድርጎ በመውሰድ ፓርቲው የሚሰራው ሥራ (ስህተት) የሕገ መንግስቱ እንደሆነ ማሰብ የለብንም። በተመሳሳይ ገዥው ፓርቲ ሲፈልግ የራሱ ብቻ አድርጎ ሲያቀርበውም ስህተት በመሆኑ ልንከላከል ይገባል። ሕገ መንግሥት አንዴ ተፅፎ በሥራ ላይ ከዋለ በኋላ ትርጉሙ የሁላችንም ነው፣ ነገር ግን ሥልጣን ያለውርጓሚ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ነው። በቤኒሻንጉል ክልል ምርጫ ጋር ተያይዞ የቀረበለትን የመመረጥ መብት ጉዳይ 1995 ዓ.ም ምክር ቤቱ ሲወስን የሰጠው ማብራሪያ ይህን የኔን አረዳድ ያጠናከረልኝ ነበረ። ስለዚህ በሕገ መንግሥቱ ላይ ተመርኩዤ ያለጥርጥር ይህን ማለት እችላለሁ: ኢትዮጵያዊ እህቴ ወይ ወንድሜ መሆኑ ብሔር ወይም ሌላ ማንነት ስላለው ወይ ስለሌለው አይቀየርም።

  7331 Hits

ወደኋላ ሄዶ ተግባራዊ የሚያደርጉ የታክስና ጉምሩክ ሕግ ድንጋጌዎች ሕገ መንግሥታዊነት

 

 

   . ወደኋላ ሄዶ ተግባራዊ የሚያደርጉ የታክስና ጉምሩክ ሕግ ድንጋጌዎች ሕገ መንግሥታዊነት 

የታክስና የጉምሩክ ሕጎች ስንል ምን ማለታችን ነው? ከሕገ መንግሥቱ ጋር ያላቸው ዝምድናስ ምን ይመስላል ?

በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/08 አንቀጽ 2(36) መሠረት የታክስ ሕግ ማለት የጉምሩክ ሕግን ሳይጨምር የታክስ አስተዳደር አዋጅ፣ የፌደራል የገቢ ግብር አዋጅ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ፣ የኤክሳይስ ታክስ አዋጅ፣ የቴምብርና የተርን ኦቨር ታክስ አዋጅ፣ ታክስ/ቀረጥ/ክፍያ ለመጣል የሚወጣ ሕግ እንድሁም እነዚህን አዋጆች መሠረት በማድረግ የሚወጡ ደንብና መመሪያዎችን ያካትታል፡፡ የጉምሩክ ሕግ ማለት ደግሞ በጉምሩክ አዋጅ ቁጥር 859/06 አንቀጽ 2(39) መሠረት የጉምሩክ አዋጁን፣ አዋጁን ተከትለው የሚወጡ የጉምሩክ ደንብና መመሪያዎችን እንድሁም የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን /የአሁኑ ገቢዎች ሚኒሰቴር/ የሚያስፈፀማቸውን ሌሎች ሕጎች ያካትታል፡፡

Continue reading
  9394 Hits

ተከሳሽ በሌለበት የወንጀል ክስ ስለመስማት (Trial in absentia)

1.  ተከሳሽ በሌለበት የወንጀል ክስ ስለመስማት (Trial in absentia) ፅንሰ ሃሳብ

ተከሳሽ በሌለበት የወንጀል ክስ መስማት (Trial in absentia) ማለት ተከሳሹ በወንጀል ክሱ በፍርድ ቤት ጉዳዩ በመታየት ላይ የሚገኝ ቢሆንም ተከሳሹ ግን በአካል በፍርድ ቤት ሳይገኝ ጉዳዩ በሌለበት በመታየት ላይ የሚገኝ ማለት ነው፡፡ ይህ አይነቱ የህግ ስረዓት በተለያዩ ሃገሮች የሚተገበር ሲሆን በእኛም ሃገር በወንጀል ሥነሥርዓት ህጉ እና በመገናኛ ብዙሃን የመረጃ ነፃነት አዋጅ ቁጥር 590/2000 ላይ በልዩ ሁኔታ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ ተከሳሽ በሌለበት የወንጀል ክስ መስማት ተገቢነቱ መታየት ያለበት ከወንጀል ህጉ አላማ፤ ከፍትህ እና ከሰብዓዊ መብት አንፃር ነው፡፡

2.  ተከሳሽ በሌለበት የወንጀል ክስ መስማት ያለው ጠቀሜታ እና ጉዳት

የወንጀል ክስ በሚሰማበት ወቅት የተከሳሽ በፍ/ቤት መገኘት ብዙ አይነት ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡ በፍ/ቤት በመገኘትም ተከሳሽ ሙሉ መብቶቹ እንዲከበሩ እና ማንኛውም አይነት የተከሳሽ መብቶች እንዳይታለፍ ማድረግ ይችላል፡፡ በዚህም ሳያበቃ በወንጀል ፍትህ አስተዳደሩ ላይ እውነታውን ከማውጣጣት አንፃር ፋይዳ አለው፡፡ ተከሳሽ በሌለበት የሚታይ ጉዳይ የአንድ ወገንን ማስረጃ ብቻ የሚመዘንበት በመሆኑ ጥፋተኛ የመባል እድልን የሚያሰፋ በመሆኑ ያለጥፋት የሚቀጡ ሰዎችን ሊያበዛ ይችላል፡፡

በሌላ መልኩ ደግሞ ተከሳሽ በሌለበት የወንጀል ክስ መስማት ተከሳሽን በመጠበቅ ሊጠፋ የሚችለውን ጊዜ በመቀነስ አፋጣኝ የፍትህ ስርዓት እንዲኖር ያደርጋል፡፡ ተከሳሽን በመጠበቅ ሊጠፋ ይችል የነበረውን የማስረጃ መሳሳት ይቀንሳል፡፡

Continue reading
  10604 Hits

አንዳንድ ጉዳዮች ስለ ሕገ-መንግሥት እና ፍርድ (ትርጉም)

 

 

 

መንደርደሪያ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የስራ ዘመን ከማለቁ በፊት ምርጫን ማከናወን እንደማይችል፤ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ካሳወቀ ጊዜ ጀምሮ፤ የጉዳዩ ሕገ መንግሥታዊ ገፅታዎች በተለያዩ መድረኮች ውይይት እየተደረገባቸው ነው። አራት አማራጭ መፍትሄዎች የቀረቡለት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ በጉዳዩ ላይ የሕገ መንግሥት ትርጉም፤ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት ጠይቋል። የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ፤ ጥያቄውን ተቀብሎ፤ የሕገ መንግሥት ምሁሮች አስተያየታቸውን በፅሁፍ እንዲያቀርቡ ጋብዟል። በቃልም እንዲያስረዱና ጥያቄዎችን እንዲያቀርቡ ጋብዟል።

የቀረበውን ግብዣ መሰረት በማድረግ አሰተያየት ለማቅረብ ውስኜ ነበር። በተለያዩ ምክንያቶች ሳላደርገው ቀርቻለሁ። አንደኛ፤ ግብዣው ለሕገ መንግሥት ምሁራኖች የቀረበ ጥሪ ነበር። ሁለተኛ፤ ጉባኤው የቀረበለትን አሰተያየት የመመልከት ግዴታ እንደሌለበት አስታውቋል። ሶስተኛ፤ በጊዜ እጥረት፤ በዛው ሳምንት የመጀመሪያ ልጄ ስለተወለደና በዚሁ ትኩረቴ ተይዞ የቆየ ስለነበረ። እንዲያም ሆኖ ግን በተለያዩ አጋጣሚዎች አንዳንድ አስተያየቶችን በማህበራዊ ሜዲያ ሳቀርብ ነበር። እነዚህን አስተያየቶቼን እንደሚከትለው አደራጅቼ አቅርቤያለሁ።

Continue reading
  7531 Hits

የክልሎች (የትግራይ ክልል) ምርጫ ሕገ-መንግሥታዊነትና ራስን በራስ የማስተዳደር ብሎም የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት

 

መግቢያ

ለዚህ ጽሑፍ መነሻ የሆነኝ 6ተኛውን ሀገር አቀፍ ምርጫ የፌደራል መንግሥቱ ማራዘሙን ተከትሎ የትግራይ ክልላዊ ብሔራዊ መንግሥት ምርጫውን በክልሉ ለማካሔድ በመወሰን የምርጫ ቦርድ በማቋቋም ምርጫውን ለማድረግ አስፈላጊ ናቸው ያላቸውን ዝግጅት በማድረጉ ሲሆን የትግራይ ክልል መንግሥት ምርጫውን ማድረግ ይችላል አይችልም? ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቁጥጥር ውጭ የሆነና ራሱን የቻለ ምርጫ ቦርድ ማቋቋም ይችላል አይችልም? ምርጫውስ ከተካሄድ ሊኖረው የሚችለው ውጤት ምን ድን ነው? የሚሉትንና ተያያዥነት ያላቸውን ጥያቄዎች ለመመለስ እንዲሁም የትግራይ ክልል ምርጫውን ማድረግ መቻሉ ጋር የምርጫውን በክልል ደረጃ መደረጉን የሚደግፉ ፖለቲከኞችና አስተያየት ሰጭዎች ራስን በራስ ከማስተዳደርና የራስን እድል በራስ ከመወሰን ሕገ መንግሥታዊ መብት ጋር ስለሚያያይዙት ከነዚህ መብቶች ጋር ምርጫ ማድረግ እንዴት ሊታይ ይገባል? የሚለውን ከፌደራሉ ሕገ መንግሥት እና ከምርጫ አዋጆች (አ/ቁ. 1133/2011 እና አ/ቁ. 1162/2011) አኳያ ለማብራራትና ሃሳብ ለማቅረብ በሚል የተዘጋጅ አጭር ጽሑፍ (Article) ነው፡፡ በዚህ ጽሑፍ ላይ ማንኛውም አስተያየት ሰጭ ለሚሰጠው አስተያየት ጸሐፊው ለማስተናገድና ሃሳብ ለመለዋወጥ ዝግጁ መሆኔን ከወዲሁ ማሳወቅ እፈልጋለሁ፡፡ መልካም ንባብ፡፡

 

1. የትግራይ ክልል ምርጫ ምንነትና ዓይነት

Continue reading
  4093 Hits

በፌዴሬሽን እና በትግራይ ክልላዊ መንግሥት ም/ቤቶች የተሰጡ ውሳኔዎች ሕገ-መንግሥታዊነት

 

በዓለማችን እና በሀገራችን የተከሰተውን የኮቪድ-19 ኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ተከትሎ በሀገራችን የፌደራል መንግሥትና የትግራይ ክልላዊ መንግሥት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጆች መታወጃቸው ተከትሎ የሀገራዊ ምርጫን መራዘምና ክልላዊ ምርጫ በትግራይ መከናወኑን ከሕገ-መንግሥቱ ድንጋጌዎች አኳያ እንደሚከተለው አስቀምጣለሁ፡፡

በቅድሚያ ጥቂት በሆነችው ትልቅ ኢ-ሕገመንግሥታዊ ውሳኔን በመግለጽ ልጀምር፡፡ በሕገ-መንግሥታችን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሊደነገግ የሚገባው በሁለት ምክንያቶች ማለትም፡-

1ኛ/ በሰው ሰራሽ አደጋ (የውጪ ወረራ ሲከሰት እና ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን አደጋ ላይ የሚጥል ሁኔታ ሲከሰት)

2ኛ/ በተፈጥሮ አደጋ (ጎርፍ፣ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ የህዝብ ጤንነትን አደጋ ላይ የሚጥቅ ሁኔታ ሲከሰት) ስለመሆኑ የፌደራሉ ሕገ-መንግሥት አ.ቁ 93(1) የሚደነግግ ሲሆን በ2ኛው የተፈጥሮ አዳጋ ሲከሰት የፌደራል መንግሥቱ ብቻ ሳይሆን ክልላዊ መንግሥቶች አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የማውጣት ሥልጣን ይኄው የሕግ መንግሥት አንቀጽ 93(1)(ለ) መብትን ይሰጣቸዋል፡፡ በመሆኑም የሀገራችን የበላይ ሕግ የሆነው አካል ለሁለቱም መንግሥታት እኩል ሥልጣን በሰጠው ጉዳይ ላይ የአንደኛው ከአንደኛው የሚበልጥበት ወይም አንደኛው በአንደኛው ላይ የበላይ የሚሆንበት ሁናቴ የለም፡፡ ነገር ግን የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት መጋቢት 30 ቀን 2012 ዓ.ም የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ተከትሎ ያወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በክልሎች ከሚወጡ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጆች ሁሉ የበላይ ስለመሆኑ መደንገጉ ኢ-ሕገ መንግሥታዊ ነው፡፡

Continue reading
  3679 Hits

በሕገ መንግሥት ማሻሻያ አንቀጽ 39ኝን መቀየር ይቻል ይሆን?

 

ሕገ መንግሥት ማሻሻል ማለት ምን ማለት ነው

ሕገ መንግሥት ማሻሻል ማለት በአጭር አነጋገር ለሕገ መንግሥት ማስተካከያ የሚደረግበት ሂደት ነው ማለት ይቻላል፡፡ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ሂደት ክለሳ (Revision) አብዮት (Revolution) ማለት አይደለም፡፡ (ቃለአብ ታደሰ)

አብዛኛው ጊዜ ማሻሻያ የሕገ መንግሥቱን ቃላት፣ ሃረግ፣ ዓ.ነገር ወይንም አንቀፆችን ሊያጠቃልል ይችላል፡፡ በእነዚህ በሚሻሻሉት ፋንታ በከፊል መጨመር፣ መቀነስ ወይንም ሙሉ በሙሉ መለወጥ ሊሆን ይችላል፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ ሁሉ ለውጦች ከሕገ መንግሥቱ አጠቃላይ አላማ፣ ግብና መንፈስ ጋር በሚጣጣም መልኩ መሆን አለበት፡፡ (ቃለአብ ታደሰ፡ 2011)

የኢፊዲሪ ሕገ መንግሥት የሚሻሻልበት ሥርዓት

የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ሃሳብን እንዴት ማመንጨት ይቻላል?

Continue reading
  4232 Hits

የሕገ-መንግሥት ፍርድ ቤት፡ የብሔርና ብሔረሰቦች ሉዓላዊነት መቃብር

 

 

በሀገራችን ህዝባዊ አመጽን ተከትሎ በሰኔ 2010 ዓ.ም ብትረ መንግሥቱን የሚዘውረው የብልጽግና ፓርቲ ለአመጹ ምክንያት የሆኑትን የዲሞክራሲ ጥያቄዎች ለመመለስ የተቋም ግንባታ እና የህግ ለውጦችን እያደረገ ነው፡፡

በተጨማሪም ገዢው የብልጽግና ፓርቲ ከኦሮሚያ እና አማራ ብሔር ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በመሆን በቅርቡ በተፈራረሙት የመግባቢያ ሰነድ ሕገ-መንግሥቱን በጋራ እንዲሻሻል ለማድረግ የሚሰሩ ስለመሆኑ ተፈራርመዋል፡፡ ይሁን እንጂ እንዲሚሻሻሉ በጋራ የተስማሙባቸው የሕገ-መንግሥት የአንቀጾች ዝርዝር ላይ ስምምነት ላይ አልደረሱም(ወይም ለህዝብ ሊገልጹት አልፈለጉም)፡፡ ነገር ግን በመግባቢያው ሰነድ ላይ ከፈረሙት አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ከጥቂት የሕገ-መንግሥት ምሁራን እንዲሻሻል ጥያቄ የሚቀርብበት አንዱ ድንጋጌ የሕገ-መንግሥት አንቀጽ 62(1) የሆነውና “ሕገ-መንግሥትን የመተርጓም” እና በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ የመስጠት የፌዴሬሽን ምክር ቤት ስልጣንን ከምክር ቤቱ ተወስዶ የሕገ-መንግሥት ጉዳይን የሚያይና የሚወስን የሕገ-መንግሥት ፍ/ቤት እንዲቋቋም በማለት ባህር አቋርጠው የምዕራቡንና የምስራቁም ልምድ በማስረጃነት በመጥቀስ በሀገራችንም ይህ ተግባራዊ እንዲሆን እየሞገቱ ይገኛሉ፡፡

Continue reading
  3147 Hits

Analysis of the unique feature of the SNNPR constitution with the FDRE constitution


 Introduction

Save the constitutions of Oromia and Tigray, the remaining seven sub-national constitutions were adopted after the promulgation of the federal constitution. Accordingly, the first SNNPR constitution was adopted in 1995 as per the authorization it gets from Art 50(5) and Art 52(2) (b) of the federal constitution. This constitution was active until it was finally replaced by the revised SNPPR constitution of 2001. As it holds true for other regional constitutions, the revision was the need to constitutional zed principles of separation of power, accountability and transparency in government acts, to organize the structure and administration of state in a way that can facilitate local government, and to create a situation that eases socio-economic development in the region. At the same time, it should also be noted that there are scholars who argue that the reason for the revision of sub-national constitutions is the internal problem of EPRDF. Whatever the case, starting from the inception of a federal system in Ethiopia SNNPR adopted only two constitutions.

This article tries to analyse the unique features of the SNNPR revised constitution and compares this with the FDRE Constitution.

 

1. Unique features of SNNPR revised constitution

Continue reading
  3154 Hits

የኢፌድሪ ሕገ-መንግሥትን በሕገ-መንግሥታዊ መንገድ ለማሻሻል ብቸኛው መንገድ፡- የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ተግባራዊ ማድረግ

 

 

1. መግቢያ

ሕገ መንግሥት በባሕርይው ጠቅላላ ድንጋጌዎችን የሚይዝ በመሆኑ፤ ሕገ መንግሥትን ከተለዋወጭ የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ እና ማኅበራዊ ሁኔታዎች ጋር ለመጣጣም እና ዘላቂነት ኖሮት ገዚ ሆኖ እንዲኖር ያስችል ዘንድ ማሻሻልን ይጠይቃል፡፡ ለዚህም ሲባል የተፃፉ ሕገ-መንግሥት ያላቸው ሀገራት በሕገ መንግሥታቸው ውስጥ ማሻሻያ ሥርዓቶችን ወይም ማስተካከያ የሚደረግበት ሂደት የሚደነግጉ አንቀጾችን አካተው ይይዛሉ፡፡ በ1987 ዓ.ም የወጣው የኢፌድሪ ሕገ መንግሥትም እንዴት እንደሚሻሻል የማሻሻያ ሥርዓቶቹን በአንቀጽ 104 እና 105 ስር ተደነግጎ ቢገኝም እስካሁን ድረስ ሥርዓቶቹን ተከትሎ ማሻሻያ ሳይደረግበት ቆይቷል።  

የኢትዮጵያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ደኤታ አቶ ሬድዋን ሁሴን ታህሳስ 9 2014 ዓ.ም ለቱርኩ አናዶል ኤጀንሲ በሰጡት ቃለ ምልልስ ላይ በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት ውስጥ ለረጅም ጊዜ ሲያጨቃጭቁ የቆዩ ጉዳዪች ላይ ምክክር ማድረግና ለሕዝበ ውሳኔ በማቅረብ ሕገ መንግሥቱን ማሻሻልን ጨምሮ ሁሉን አካታች ሀገራዊ የምምክር መድረክ ለማካሄድ መታቀዱን ተናግረዋል።  በተመሳሳይ መልኩ የሀገሪቷ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አብይ አህመድም የሕገ-መንግሥት ማሻሻያ አጀንዳ ላይ ምክክር እንደሚደረግ በቅርቡ መግለጻቸው ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረትም አገራዊ መግባባት ለመፍጠር ያስችላል ተብሎ የታመነበት የኢትዮጵያ አገራዊ ምክር ኮሚሽን መቋቋሚ አዋጅ በቅርቡ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መፅደቁ ይታወሳል፡፡ ነግር ግን የኢፌድሪ ሕገ-መንግሥት ማሻሻያ ሥርዓቶች እጅግ ውስብስና ጥብቅ (very stringent and rigid) ስለመሆናቸው የዘርፉ ምሁራን ያስረዳሉ፡፡

Continue reading
  2201 Hits