የይግባኝ የዳኝነት ክፍያ አግባብነትን በተመለከተ

ግምቱ ተለይቶ የሚታወቅ የፍትሐ ብሔር ክርክር ጉዳይ በመያዝ በፍርድ ቤት ክስ የሚመሰርት ወይም የተከሳሽ ከሳሽነት ክስ የሚያቀርብ ማንኛውም ተከራካሪ በፍትሐብሔር ሥነሥርዓት ሕግ ቁጥር 215/1 እና ስለ ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ገንዘብ አከፋፈል በ1945 ዓ/ም በተደነገገው ደንብ መሠረት የዳኝነት ክፍያ ይከፍላል። በዚህ ክሱን በከፈተበት ፍርድ ቤት በተሰጠው ውሳኔ ቅር የተሰኘ ተከራካሪ ደግሞ የይግባኝ አቤቱታውን ይግባኝ ለመስማት ሥልጣን ወዳለው ፍርድ ቤት ያቀርባል። ይህ የይግባኝ አቤቱታ እንዲሰማለት ደግሞ በሥር ፍርድ ቤት የከፈለውን የዳኝነት ክፍያ 50% መክፈል ይጠበቅበታል። የዚህ አጭር ማስታወሻ ዓላማም የዚህ የይግባኝ የዳኝነት ክፍያ አግባብ የማይሆንበትን ኹኔታ መጠየቅ ነው።  

  9272 Hits

አመክሮ፤ መብት፣ ሸቀጥ ወይስ ችሮታ?

ፕሬዝደንቱ የስልጣን ጊዜአቸውን ጨርሰው ከሥልጣን ሊወርዱ የወራት ወይም የቀናት ዕድሜ ነው የቀራቸው። ከሥልጣን ከመውረዳቸው በፊት ግን ለወደፊት ሕይወታቸው ገንዘብ ለመሰብሰብ የሚያስችላቸው አንድ አጋጣሚ ከፊታቸው ተደቅኗል። ይህ በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር የሚያስገኝ አጋጣሚ አሁን ባላቸው የፕሬዝዳንትነት ስልጣን ሊያደርጉት የሚችሉት ነገር ነው። ይህ አጋጣሚ “ፕሬዝደንታዊ ይቅርታ” (Presidential pardon) ነው። እስረኛው ይህንን ይቅርታ አግኝቶ ከእስር ከተፈታ የሚከፍለው ገንዘብ እጅግ ብዙ በመሆኑ በሥልጣን ደላላዎች (Power brokers) አማካኝነት ገንዘቡን ተቀብሎ የይቅርታ ሰነዶቹ ላይ ፈረመ።

  10448 Hits

What Do We Need To Be Reminded Of?

“The great American word is freedom, and in particular freedom of thought, speech and assembly.” Robert M. Hutchins

All freedoms are a single freedom- one and indivisible, although people consider one freedom as more important than the others. The above quote from Robert Hutchins is the sole spirit of the First Amendment to the American constitution. This First Amendment lumps together the freedom of religion, of speech and the press, of assembly, and of petition.

  9342 Hits