በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ መሠረት በተሰጠ የፍርድ ውሳኔ ላይ የሚቀርብ የአፈጻጸም ክስ በይርጋ ቀሪ ስለሚሆንበት የሕግ አግባብ

መግቢያ

አፈጻጸም ማለት አንድ መብቱ በፍርድ ውሳኔ እንዲከበር ለፍርድ ቤት ክስ ያቀረበ ሰው የፍርድ ውሳኔ አግኝቶ በፍርዱ መሰረት ሳይፈጸምለት ሲቀር ፍርዱ የተፈረደበት ወገን እንደ ፍርዱ እንዲፈጽም የሚገደድበት የሕግ ሥርዐት ነው፡፡ ይህ ስርዐት የሚመራውም በፍትሐብሔር ሥነ- ሥርአት ሕግ ቁጥር 375 ጀምሮ በተደነገጉ ድንጋጌዎች መሰረት ሲሆን በእነዚህ የሕግ ማእቀፎች ተንተርሶ መብቱ እንዲፈጸምልት ሚጠይቅ ወገን የፍርድ ባለመብት ሲባል እንዲፈጽም የሚገደደው ደግሞ የፍርድ ባለእዳ ተብሎ ይጠራል፡፡

Continue reading
  12351 Hits

በኢትዮጵያ አሠሪና ሠራተኛ ሕግ የሥራ ስንብት ክፍያ ምንነትና የሚስተዋሉ አንዳንድ ችግሮች

 

እንደ መነሻ

የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት ለረጅም ጊዜ በተለያዩ የኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ አተሰሳሰቦች የነበረ፤ ያለ እና የሚኖር መስተጋብር ነው፡፡

ታሪኩንም በወፍ በረር መለስ አድርገን ስንመለከት ከካፒታሊስታዊ ሥርዓተ ማኅበር በፊት በነበሩት ሥርዓቶች በተለይም በባሪያ አሳዳሪ /slave-owning/ ሥርዓተ ማኅበር እና በፊውዳል /feudal system/ ሥርዓተ ማኅበር ወቅት ይሰተዋል የነበረው ሠራተኛው እንደ ጪሰኛ የሚቆጠርበት ሥርዓት ነበር፤ የሚያገኘው ጥቅምም ከአሠሪው ምግብ እና መጠለያ እንጂ መደበኛ ደምወዝ አልነበረውም፡፡

የአሠሪና ሠራተኛ ሕግ ብቅ ማለት የጀመረው በኢንዲስትሪ አብዮት ወቅት ሲሆን የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነትም ከትናንሽ የጎጆ ኢንዱስትሪ ወደ ትላላቅ ፍብሪካዎች በተሸጋገረበት ጊዜ ነበር፡፡ በአንጻሩ አሠሪዎች ደግሞ በቀላሉ ሠረተኛ ቀጥረው ያሠሩ ነበር ለምን ቢባል በወቅቱ በጣም ርካሽ የሰው ኃይል ስለነበር ነው፡፡ በወቅቱም የሠራተኛች አንገብጋቢ ጥያቄ የነበረው የተሻለ የሥራ ሁኔታ /minimum working condition/ እንዲሁም ከሠራተኛ ማኅበር አባልነት ጋር የተያያዙ መብቶች ነበሩ፡፡

Continue reading
  40809 Hits

የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ማቆም መብትና ሕገወጥ ተግባሮች ምንነት በኢትዮጵያ የሕግ ማዕቀፍ

 

የዚህ አጭር ጽሑፍ ዓላማ የሲቪል አቪዬሽን ሠራተኞች የሥራ ማቆም አድማና የፌዴራል ፖሊስ የእስር ዕርምጃ ተከትሎ በተለያዩ ሚዲያዎች በመንግሥት በኩል በተወሰዱት ዕርምጃዎች ዙሪያ እየቀረቡ ያሉ ሕግ ነክ አስተያየቶች ውይይቶች፣ ሰሞነኛ ክርክሮችንና ተያያዥ ነጥቦች መነሻ በማድረግ በኢትዮጵያ ውስጥ የመንግሥት ሠራተኞች ሕጋዊ የሥራ ማቆም መብት የሕግ ወሰን እስከ የት ድረስ ነው? የሚለውን ጥያቄ ከሕገ መንግሥት መሠረታዊ መርሆች አንፃር በመመልከት በመብቱ አፈጻጸም ላይ የሚነሱ አንዳንድ የሕግ ጉዳዮችን በአጠቃላይ በአገሪቱ የተለያዩ የአሠሪና ሠራተኛ መብትና ግዴታዎችን አስመልክቶ በፌዴራል መንግሥት በኩል ከወጡ ሕጎች አንፃር በመጠኑ መዳሰስ ነው፡፡

የሥራ ማቆም መብት ጽንሰ ሐሳብና በሕግ የተሰጠው ጥበቃ

የሥራ ማቆም አድማ ሠራተኞች በሕግ ዕውቅና ተሰጥቶት ያለ የኅብረትና በነፃነት የመደራጀት ሰፊ የሆነው መሠረታዊ መብት አንዱና ወሳኝ ከሚባሉት ውስጥ የሚጠቀስ ነው፡፡ በዚህ ረገድ የሥራ ማቆም ዕርምጃ ሠራተኞች ለአንድ የተወሰነ ወቅት የሚሠሩትን ሥራ እንዲቋረጥ በማድረግ ለጋራ ፍላጎታቸው በአንድነት በመሆን አቋማቸውን የሚገልጹበት የመታገያ ሥልት ነው፡፡ በአጠቃላይ ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ ሁኔታ ከሥራቸው ጋር በቀጥታ በሚገናኙ ማንኛውም ጉዳዮች በተለይም ደግሞ ከተቋማዊ፣ ከማኅበራዊና ከኢኮኖሚያዊ በቀጥታ በሚያያዙ ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ጥያቄያቸውን ሕጉን ተከትለው ለሚመለከታቸው መንግሥታዊ ውሳኔ ሰጪ አካላት የሚያቀርቡበትና ድምፃቸውን ለማሰማት የሚችሉበት የመደራደሪያ ሕጋዊ ሥልቶች ነፀብራቅ እንደሆነ ከሠራዊቶች የቡድን መብቶች ታሪካዊ አመጣጥና ከዳበሩት የሕግ ፍልስፍናዎች የተጻፉ ዓለም አቀፍ የሕግ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ ይህም ሲባል መብትና ጥቅማቸውን አንድም በሚመሠርቱት የሠራተኛ ማኅበሮች በኩል ወይም በጋራ በመሆን አሠሪዎቻቸው ላይ ተፅዕኖ ለመፍጠር የሚያስችላቸው ሕጋዊ መንገድ እንደሆነ ዓለም አቀፍ የሠራተኞች መብትን ለማስጠበቅ ከወጡ ስምምነቶች መገንዘብ ይቻላል።

 የዓለም አቀፉን የሠራተኞች መብት በሕግ ጥበቃ ለማሰጠት ከወጡት የተለያዩ ስምምነቶች እንዲሁም አገሮች አባል የሆኑበት የበላይ ጠባቂ የሆነው ተቋም (International Labor Organization (ILO)) አማካይነት በየጊዜው ስለሠራተኞች በነፃነት የመደራጀትና የሠራተኛ ማኅበራት የመመሥረት መብት (Right to Organize & Collective Bargaining Convention (1948/51)) & Freedom of Association & Protection of the Right to Organize Convention) (1948/51)) አስመልክቶ በዝርዝር ከፀደቁት የሕግ ሰነዶች እያንዳንዱ አገሮች በውስጥ የሕግ ማዕቅፎቻቸው ተጨባጭ ሁኔታዎቻቸውን መሠረት በማድረግ ለመብቱ አፈጻጸምና አተገባበር ልዩ ሕጎች በማውጣት ሕጋዊ ጥበቃና ምቹ ሁኔታዎችን እንዲፈጥሩ ግዴታዎችን ያስቀምጣሉ፡፡   በተለይም ኢትዮጵያ አባል የሆነችበትና በ1987 ዓ.ም. በፀደቀው የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት ምዕራፍ 3 አካል የሆነው የተባበሩት መንግሥታት የኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ባህላዊ መብቶችን ለመደንገግ የወጣው የቃል ኪዳን ሰምምነት (International Convenant on Economic, Social, and Cultural Rights (ICESCR)) የሠራተኞች አጠቃላይ መብቶችን በሚመለከት ልዩ ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ ከመሆኑም በተጨማሪ በቃል ኪዳን ስምምነት ሰነዱ አንቀጽ 8 ውስጥ የሥራ ማቆም ዕርምጃ የመውሰድ መብት የየአገሮቹን ገዥ ሕጎች ተከትሎ በሁሉም መስክ የሚገኙ ሠራተኞች ገደብ ሊጣልባቸው ከሚችሉት ከመከላከያ ሠራዊት፣ ከፖሊስና ከመንግሥት የአስተዳደር ሠራተኞች በስተቀር መብቱ ሳይሸራረፍና ያለአድልኦ በእኩልነት ሊከበር እንደሚገባው ዋስትና ይሰጣል፡፡ ሆኖም አባል አገሮች በውስጥ ባላቸው ተጨባጭ ሁኔታዎች አንፃር በማገናዘብ በሕጎቻቸው ላይ የተወሰኑ ገደቦች እንዲሁም የሥራ ማቆም ዕርምጃ ፈጽሞ ማድረግ የማይቻልባቸውን ዘርፎች በሚመለከት በዝርዝር ሕግ መከልከል እንደሚችሉ ነገር ግን የሠራተኞች የጋራ መብት ፍፁምነት የሌለው ቢሆንም፣ እንኳን ገደብም ሆነ ክልከላ ለማድረግ የሚቻለው ቢያንስ ቢያንስ ግልጽ የሆኑትን ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያገኙ ሕጋዊ መሥፈርቶችንና አሠራሮች ጋር ተጣጥሞና መሠረታዊ የሆነውን የመብቱን ዓላማ በማይቃረን መልኩ ሊሆን እንደሚገባ ያስረዳሉ፡፡

Continue reading
  10999 Hits

አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 እና አንዳንድ ጉዳዮች

 

ከዚህ ቀደም በሀገራችን ኢትዮጵያ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይን የሚገዙ ሕጎች እንደነበሩ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ በ1955 ዓ.ም የወጣው የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 210/1955፣ በ1968 ዓ.ም የወጣው የሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 64/1968፣ የሠራተኛ ጉዳይ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 85/1968፣ ስለአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ የወጣው አዋጅ ቁጥር 42/1985 እና አዋጅ ቁጥር 377/1996 የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

ከየካቲት 18 ቀን 1996 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ በግሉ ዘርፍ ያለውን የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነትና መስተጋብር እንደ ዋነኛ ምሰሶ በመሆን ሲያስተዳድር የነበረው ሕግ አዋጅ ቁጥር 377/1996 እና የዚህ አዋጅ ማሻሻያ ሕጎቹ አዋጅ ቁጥር 466/1997 እና አዋጅ ቁጥር 494/1998 ነበሩ፡፡ እነዚህ ሕጎች ከ14 አመታት በላይ በሥራ ላይ የዋሉ በመሆናቸው አሁን ካለው የማህበረሰብ እድገት ጋር የተጣጣሙ ባለመሆናቸው የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቀን ሰኔ 27 ቀን 2011 ዓ.ም ባደረገው 4ኛ አመት የሥራ ዘመን 48ኛ መደበኛ ስብሰባው የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ረቅቅ አዋጅን መርምሮ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡

ይህም ሕግ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ዓ.ም ሆኖ ነሐሴ 30 ቀን 2011 ዓ.ም በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ በሥራ ላይ ውሏል፡፡ ይህ አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ምን ምን ሀሳቦችን አካቶ ነው የተሻሻለው? ለሠራተኛው ምን ዓይነት ሕጋዊ ጥቅምና መብቶችን አካቷል? እንዲሁም የአሠሪ ግዴታና መብት ምን ይመስላል? የሚሉትን ጉዳዮች እና አዲሱን አዋጅ ከተሻረው የአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ቁጥር 377/96 በማነፃፀር በወፍ በረር (Bird’s Eye View) እንደሚከተለው እንመለከታለን፡፡

አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ከዚህ ቀደም የነበረውን አዋጅ ከነ ማሻሻያዎቹ በመሻር እና የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጄንሲ አዋጅ ቁጥር 632/2001ን በአዲሱ አዋጅ ውስጥ በማካተት ነው በሥራ ላይ የዋለው፡፡

Continue reading
  74982 Hits

በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት - የሠራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ፕሮቶኮል አንድምታ

 

ዓለማችን ላይ የፈረንጆቹ 2020 የተወሳሰቡ ችግሮችን ይዞባት መጥቷል፡፡ ከቻይና ውሃን በትንሹ ተነስቶ በወራት ውስጥ ዓለምን ካዳረሰው የኮሮና ቫይረስ የሚስተካከል ችግር ግን ይመጣል ብሎ የገመተ አልነበረም፡፡ ይህ ቫይረስ በቀጥታ በሰው ልጆች ጤና እና ህይዎት ላይ እያሰከተለ ከሚገኘው ኪሳራ እና ውድመት በሚስተካከል ደረጃ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችንም እያስከተለ ይገኛል፡፡ ከአሜሪካ ስቶክ ማርኬት እስከ ኢትዮጵያ አየር መንገድ፤ ከአውሮፓዊያኑ የንግድ ልውውጦች እስከ ኢትዮጵያ የአበባ ንግድ፤ ከካናድ የጥራጣሬ ግብይት እስከ አዲስ አበባ የአትክልት ተራ ንግድ ድረስ ብዙ መመስቃቀሎችን እያስከተለ ይገኛል፡፡ በዚህ መመሰቃቀል ውስጥ ብዙ አካላት ተጎጂ የሚሆኑ ቢሆንም በተለያዩ ሁኔታዎች ላይ ተቀጥረው እንደሚሰሩ ሰራተኞች ግን የችግሩ ቀጥተኛ ገፈት ቀማሽ አይገኝም፡፡ በተለይ ከአሜሪካ የቅጥር ገባያ እየሰማን እንዳለነው ብዙ ድርጅቶች ሰራተኞቻቸውን እየቀነሱ እያጋጠማቸው ያለውን የገንዘብ እጥረት በማቃለል ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህ በሀገሪቱ የሚገኘውን የሥራ አጥ ቁጥር ወደ ስላሳ በመቶ እያደረሰው ይገኛል፡፡ ይህ ችግር ወደ ኢትዮጵያ መከሰቱ የማይቀር ነው፡፡ ብዙ የግል ድርጅቶች ስራቸውን ሙሉ ለሙሉ እያቆሙ በሚገኝበት በዚህ ጊዜ የሠራተኛን የደሞዝ ወጪ ያለምንም ችግር የመሸፈን አቅም ይኖራቸዋል ተብሎ አይጠበቅም፡፡    

ይሄን ችግር ከግምት ውሰጥ በማስገባት የሠራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በዚህ ሳምንት መጋቢት /2012 ዓ/ም ከአሠሪዎችና ሠራተኛ ማህበራት ጋር በመነጋገር አሠሪዎች በዚህ ወቅት ለሰራተኞቻቸው ወጥ የሆነ ምላሽ እንዲሰጡ የሚያስችል የኮቪድ 19 የሥራ ቦታ ምላሽ (workplace Response) የተመለከተ ፕሮቶኮል (ፕሮቶኮል ወይም ፕሮቶኮሉ) አውጥቷል፡፡ የዚህ ፕሮቶኮል መነሻ የዓለም ስራ ድርጅት (አይ.ኤል.ኦ) በተፈጥሮ እና በሰው ሰራሽ አደጋዎች ሳቢያ ሀገራት እና የስራው ዓለም ሲጠቃ የቀውስ አስተዳደር ምላሽን በተመከተ በተቀመጠው ጋይድ ላይን መሰረት መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ ይህ አጭር ዳሰሳ ፕሮቶኮሉ በአሠሪዎች እና በሰራተኞች ላይ የሚጥለውን መብትና ግዴታ ከማየት ባለፈ የፕሮቶኮሉን ህጋዊ አንድምታ እና መሰል ጉዳዮችን አይዳስስም፡፡

  1. ፕሮቶኮሉ ዓላማ

የፕሮቶኮሉ አሠሪዎች ያላቸውን ህልውና ለማስቀጠል የሠራተኛ የደሞዝ ወጭን በመቀነስ የሚወስዷቸውን እርምጃዎች እና ሰራተኞች ደግሞ በዚህ ወቅት ሊደርስባቸው የሚችለውን ከፍተኛ የሆነ ማህበራዊ ቀውስ ከግምት ውስጥ በማስገባት የአሠሪውን ህልውና እና የሰራተኞችን ማህበራዊ ዋስትና በማመጣጠን ወጥ ምላሽን ለመስጠት ያለመ ነው፡፡ በፕሮቶኮሉ ላይ እንደተጠቀሰው የቫይረሱን ወረርሽን ባስተማማኝ መልኩ ለመከላከል እና ወረርሽኙ ቢከሰት ጉዳትን ለመቀነስ እንዲሁም ወረርሽኙ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ፤ በድርጅቶች ቀጣይነትና ህልውና እና በሠራተኞች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ የሚፈጠረውን አሉታዊ ተፅዕኖ መቀነስ ነው፡፡

  1. የአሠሪ ግዴታዎች

ወረርሽኙን የመከላከያ እርምጃዎችን መውሰድ

Continue reading
  7010 Hits

Examining Workers Rights, Occupational Safety Measures and Benefits amid Covid-19 Under Ethiopian Labour Law

 

Introduction

The outbreak of CODIV-19 has caused employment crisis worldwide as the virus is claiming thousands of lives and sickening a millions. The virus is causing global economic, social, health, and economic disruptions. The International Labour Organization has an estimate that up to 25 million jobs could be lost worldwide. In addition to the possible unemployment crisis, the safety and health of workers are at risk. Following the declaration of the virus as a Public Emergence of  International Concern  and pandemic by World Health Organization, countries are taking different measures including partial or full lockdown. Ethiopia is not an exception to this crisis, and the same measures are being taken by the government.

During crisis, Labor Law responds with safety and health measures, benefits and rights for workers. However, CODIV-19 pandemic has brought new challenges to some static provisions of the labor law, including the ILO protocols and guidelines. The Ethiopian labor proclamation has also suffered from some lacuna to combat the CODIV-19 pandemic having static provisions in normal cases. Hence, the discussion as to new challenges posed by the new pandemic to the Ethiopian labor law, the adequacy of existing legal responses available, the safety and health measures needs to be taken, and the workers' rights and benefits related with this outbreak is imperative and timely.

The Issue

Continue reading
  5420 Hits

የኮቪድ 19 ወረርሸኝና የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ

 

በዓለማችን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽን እየተስፋፋ በመምጣቱ ከአሜሪካ እስከ አፍሪካ፣ ከአውሮፓ እስከ እሲያ ከአውስትራሊያ እስከ ደቡብ አሜሪካ መንግስታት፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ ግዙፍ የንግድ ድርጅቶች አነስተኞቹን ጨምሮ እንቅስቃሴያቸው እየተናጋ፤ ህልውናቸው ፈተና ውስጥ እየገባ ነው፡፡ ይህ ወረርሽን ማብቂያው እና መወገጃው በግልጽ ያልታወቀ እና ሊተነበይም ያልቻለ በመሆኑ በተለይም የግል የንግድ ድርጅቶች ቀጥረው የሚያሰሯቸው ሠራተኞች ላይ ሊወስዱ ስለሚችሉት እርምጃ እርግጠኛ አይደሉም፡፡ በሀገራችን ኢትዮጵያም የቫይረሱ መግባት ከተረጋገጠበት ጊዜ አንስቶ መንግስት ትምህርት ቤቶችን  እንዲዘጉ አድርጓል፡፡ በመቀጠልም ፍርድ ቤቶች በከፊል እንዲሁም የመንግስት ተቋማት በፈረቃ የሚሰሩበትን ሁኔታ አመቻችቷል፡፡ በሌሎች የንግድ ድርጅቶች ላይ በመንግስት ደረጃ የተሰጠ ትዕዛዝ ባይኖርም የንግድ እንቅስቃሴ በመቀዝቀዙ እንዲሁም ግለሰቦች በተቻላቸው አቅም ከቤት እንዳይወጡ እየተመከረ በመሆኑ ሥራ በአግባቡ እየተሰራ እና ድርጅቶች በፊት ያገኙ የነበረውን ገቢ እያስቀጠሉ ነው ለማለት አዳጋች ነው፡፡

በመሆኑም የግል የንግድ ተቋማት በተለይ በእንደዚህ አይነት አስገዳጅ የሆነ ሥራን ማሰራት፣ ገቢንም መሰብሰብ በማይቻልበት ወቅት ምን አይነት ሕጋዊ እርምጃዎችን መውሰድ ይችላሉ? በሕጉ ላይ የተቀመጡ አማራጮች ምንድን ናቸው? አማራጮቹን ለመጠቀምስ የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችስ ምን ምን ናቸው? የሚሉትን ነጥቦች ከአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 (አዋጁ) ድንጋጌዎች አንጻር በመቃኘት አሠሪዎች በሠራተኞቻቸው ላይ አላስፈላጊ እርምጃ እንዳይወስዱ፤ ሠራተኞችም የሥራ ዋስትናቸው እስከምን ድረስ ሊሆን እንደሚችል ተገንዝበው የራሳቸውን መብት እንዲያስከብሩ እና አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ በማሰብ ይህን ጽሑፍ ተዘጋጅቷል፡፡

 

ከአቅም በላይ የሆኑ ከሥራ ውል የሚመነጩ መብትና ግዴታዎች እንዲታገዱ ሊያደርጉ የሚችሉ ሁኔታዎች፡-

Continue reading
  4539 Hits

የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ መቁረጥ እና ሕጋዊነቱ

 

ለዚህ ጽሑፍ መነሻ የሆነው ገበታ ለሃገር መርሃግብር የመንግሥት ሠራተኞች የወር ደሞዛቸውን ለገሱ የምትል ዜና በተደጋጋሚ በመስማቴ እና እውነት በዚህ የኑሮ ውድነት እነዚህ የመንግሥት ሠራተኞች ደሞዛቸውን የሚለግሱት ጎርጎራ፣ ወንጪ አሊያም ኮይሻ  ላይ ሆቴል መሰራቱ ከጊዚያዊ ችግሮቻችን ይበልጣል ብለው አምነው ወይስ በአለቆቻቸው ተፅዕኖ ሥር በመሆናቸው ተገድደው የሚለው ጥያቄ በተደጋጋሚ ውስጤ ሲመላለስ በመቆየቱ ነው፡፡ መልካም ንባብ!

ለጠቅላይ ሚኒስትራችን ምስጋና ይግባቸውና አይነ-ግቡ የሆኑ የቱሪስት መዳረሻዎችን ከቤተ-መንግሥታቸው ጀምረው እየገነቡልን ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ስራዎች የሃገርን ገፅታ ከመገንባት ጀምሮ ታሪክን ጠብቆ በማቆየት በቱሪዝም እንደሃገር የሚገኘው ገቢ ከፍተኛ እንዲሆን በማድረግ ረገድ ትልቅ ተስፋ የተጣለባቸው መሆናቸው በስፋት ይጠቀሳል ይሁን እንጂ በተቃራኒው ቅንጦት ነው፣ በዚህ ሰዓት ሰላም እና በልቶ ማደር እንጂ ቅንጡ ሆቴል የሚፈልግ ኢትዮጵያዊ ከቁጥር አይገባም ስለሆነም ያለጊዜው የመጣ ፕሮጀክት ነው በማለት የሚተቹትም አልጠፉም፡፡

ቤተመንግሥትን ከማስዋብ የተጀመረው ፕሮጀክት አሁን አድማሱን አስፍቶ ሃገራዊ ቅርፅን በመላበስ በሶስት ክልሎች ማለትም አማራ፣ ኦሮሚያ እና ደቡብ ያሉ የመስህብ ስፍራዎችን ወደማልማት ተሸጋግሯል፡፡ ለዚህም እውን መሆን ገበታ ለሃገር በሚል በገቢ ማሰባሰቢያ መልክ የ10,000,000 ብር እና 5,000,000 ብር የሚከፈልበት እራት ግብዣ በጠቅላያችን ተሰናድቷል፡፡ በዚህ አላበቃም በኢትዮ ቴሌኮም አማካኝነት ዜጋው ልቡ በፈቀደ መጠን ገንዘብ እንዲለግስ አጭር የጽሑፍ መልዕክት ተዘጋጅቷል፤ የባንክ አካውንትም በተለያዩ ሚዲያዎች ይፋ በማድረግ ገቢ ማሰባሰብ ስራው ቀጥሏል፡፡ ይሁን እንጂ ፕሮጀክቱ ይፋ ሲደረግ ያልተገለፀ ነገር ግን በተግባር እየሆነ ያለ አንድ እውነት አለ፡፡ ይህም የመንግሥት ሠራተኛው ለፕሮጀክቱ የወር ደሞዙን እንዲሰጥ ማድረግ፡፡ የእንትን ሚኒስቴር ሠራተኞች እና አመራሮች ለገበታ ለሃገር የወር ደሞዛቸውን ለገሱ የሚል ዜና በየዕለቱ እየሰማን ነው፡፡ ለመሆኑ የሠራተኛ ደመወዝ የሚቆረጠው እንዴት ነው?፣ አንድ የስራ ሃላፊ ስለፈለገ ወይም መስሪያቤቱ አመራሮች ተወያይተው ስላፀደቆ የሠራተኛን ደመወዝ መቁረጥ ይቻላል እንዲቆረጥብን አንፈልግም የሚሉ ሠራተኞች ሲኖሩ እንዴት ይደረጋል?፣ የሚሉ ጥያቄዎች በዚህ ጽሑፍ መልስ ለመስጠት ይሞከራል፡፡

 

Continue reading
  10169 Hits

The Minimum Wage System in Ethiopia: a Comparative Analysis

 


Abstract

A minimum wage is the lowest wage that employers may legally pay to workers. The purpose of minimum wages is to protect workers against unduly low pay and they are essentially labour market interventions used by governments either as instruments of political macroeconomics or as social tools. Governments introducing minimum wage policy and legislations basically aim to protect low-income workers through the introduction of minimum wages based on country specific factors. In case of Ethiopia the new labour proclamation which is entered into force in 5th September, 2019 for the first time provide establishment of minimum wage board that will periodically revise minimum wages based on different factors. Since the new minimum wage board in Ethiopia is a new conception it is not perfect in addressing all issues and problems that exist in the implementation of the purpose intended by the government. So this article has employed different sources and explores the minimum wage system in Ethiopia special focusing on new labour proclamations by consulting other countries better experience in tackling those unseen problem and for having strong minimum wage system in the country.

 

Continue reading
  4865 Hits

Creating Economic opportunities for refugees: Why refugees in Ethiopia are refusing their right to work and integration?

 

1. The right to work of refugees

 The right to work is one of the fundamental human rights recognized by different human rights instruments. The 1948 Universal Declaration of Human Rights (UDHR) under its Article 23 declared the right to work as a fundamental human right.

For refugees, the right to work is vital for reducing vulnerability, enhancing resilience, securing dignity, and integration. The 1951 Refugee Convention and its 1967 Protocol relating to the Status of Refugees recognize the right to work of refugees including their Right to housing, education, welfare assistance and social security, Freedom of movement, ID documents and travel documents.

To implement the right to work of refugees there are Legal conditions required by refugee law and other national laws. The variety of legal conditions related to the right to work and other legal restrictions on the right to work such as work permits, restricted business sectors, an encampment of refugees, and restrictions on freedom of movement.

Continue reading
  3771 Hits