በኢትዮጵያ የሲቪክ ምህዳር መብቶች ጥበቃ እና የሚስተዋሉ አንዳንድ ችግሮች

 

 

 

“The importance of ensuring the broadest possible civic space in every country cannot be overstated…The protection of the civic space, and the empowerment of human rights defenders, needs to become a key priority for every principled global, regional and national actor."

Continue reading
  9069 Hits

በኢትዮጵያ በኢንተርኔት ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብት እና ገደቡ

መግቢያ

ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብት ለዲሞክራሲያዊ ማህብረሰብ መፈጠር የመሰረት ድንጋይ ነው፡፡ ይህ መብት በጣም ረጅም ጊዜ ያስቆጥረ የሰው ልጅ መብት ሲሆን በዘመናት መካከል በፈላጭቆራጭ ነገስታት እና መሪዎች ጫና ተደርጎበታል፡፡ ለአብነት ያህልም በጥንታዊ ባቢሎናዊያን የልዩነት ሃሳብ (being dissenter) መያዝ ወደ እቶን እሳት ያስጨምር እንደነበር ከመጽሃፈ ዳንኤል  ምዕራፍ 3 ንባብ መረዳት እንችላለን፡፡

ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብት የፍልስፍና መሰረቱ ከጥንት ግሪካዊያን ስልጣኔ ጋር አብሮ ይነሳል፡፡ በተለየም የዴሞክራሲ ታሪካዊ ከተማ በሆነችው አቴንስ የመናገር ነጻነት ዋጋ ህይዎትን እስከወዲያኛው ሊያስነጥቅ የሚችል ነገር ነበር፡፡ በዚህ ረገድ የሶቀራጥስ የፍርድ ችሎት ለዘመናት እንደ የመናገር ነጻነት ጥሰት ተደርጎ በድርሳናት ይወሳል፡፡ (አርሊን ሳክሶንሃውስ፡2006፡102)

በአውሮፓዊያን የዕውቀት ስልጣኔ (enlightenment period) ጫፍ በነካበት ወቅት የመናገር ነጻነት አምባገነን መንግስታትን በሃሳብ ለመሞገት የሚስችል መሳሪያ ነበር፡፡ ለምሳሌ:- ባሮን ሞንተስኩ የተባለ የፈረንሳይ ፈላስፋ የመንግስት ስልጣን ሕግ አውጪ፣ ሕግ አስፍፃሚ እና ሕግ ተርጓሚ ተብሎ መከፈል እንዳለበት በጹሁፍ እና በቃል በማስተማሩ የማታ ማታ ሃሳቡ ተቀባይነት ሊያገኝ ችሏል፡፡ በኋላም እኤአ ከ 1789_1799 ዓ.ም በነበረው የፈረንሳይ አቢዮት የመናገር መብት የሰው ልጆች ትልቁ ነጻነት እንደነበር ታሪክ መዝግቦታል፡፡ በታላቋ ብሪታኒያ እና አሜሪካም የመናገር ነጻነት የሊብራል የፖለቲካ አስተሳሰብ እና ዴሞክራሲ እንዲያብብ በማስቻል ረገድ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል፡፡ በተለይም እነዚህ አገራት ጆን ሚልተን፣ ጆን ስቱዋርት ሚልን ጨምሮ ጀምስ ማዲሰንን የመሰሉ ሃሳብን በነጻነት የመናገር መብት ተሟጋቾችን አፍርተዋል፡፡

ልክ እንደ ዘመነ ሶክራጥስ ሁሉ ዛሬም ሃሳብን በነጻ መግለጽ እንደ ጅማል ካሾጊ ህይዎትን እስክ ወዲያኛው ሊያስከፍል ይችላል፡፡ በአምባገነኖች ግፊት አገር እስጥሎ ስደተኛ ያደርጋል፤ ለእስር ብሎም ለተለያዩ እንግልቶች ይዳርጋል፡፡

ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብት ሲባል ግለሰቦች ሃሳባችውን መግለጽ፣ መረጃ ማግኘት፣ መጠየቅ እንዲሁም ለሌሎች የማካፈል መብትን ጨምሮ በፈለጉት መንገድ ማለትም በጽሁፍ፣ በንግግር፣ በምልክት፤ በኢንተርኔት ወይም በሌላ መንገድ በመጠቀም መልዕክት የማስተላልፍ መብት ነው፡፡

Continue reading
  12017 Hits

The Ethio-Eritrea Rapprochement - a Catalyst to Hone Human Rights Profile?

The human rights profile of Ethiopia and Eritrea have been infamous. Both countries have criticised by the leading UN human rights bodies, regional and NGOs. Now, these countries are making history by torn down the wall of resentment built after bloody boarder war. Would this new chapter of rapprochement enable them to revamp their human rights profile?

Before examining the role of rapprochement for the improvement of human rights, it is worth to glance a laconic view of major events held in the past few years. Ethiopia and Eritrea have been rancorous rivals in the political economy of the Horn of Africa. (See here, here, and here).Even one accuses the other for sheltering rebels and assisting armed groups, and they were also engaging in proxy-war held in Somalia in 2006. Initially, two countries went to battlefield for an iota piece of land called Badme though the casus belli was mainly economic and other political factors. The conflict between two brotherly States reached its peak in the year 1998-2000, in turn, costed both of them inter alia, it claimed the lives of more than 70,000 people, displaced civilians, pummeled their economy, brought serious violation of international humanitarian law and waned the human rights situations.

This blog post did not delve into the cause-effect analysis the rapprochements nor specific case studies of human rights  rather it aimed at discussing few musings on the role of the rapprochement for the betterment of human rights in both States.

      Picture credit: Eritrean MoI

Continue reading
  8119 Hits

ከሠራተኞች መብት አንጻር ትኩረት የሚሹ የግንባታ ደህንነት አንዳንድ ነጥቦች

 

ለመስፋፋትና፡ ለመመቻቸት፤

ተድላና፡ ደስታ፡ ምቾት፡ ለማግኘት፤

እንረዳው በጣም፡ መነሻ እርካባችን፤

ሠራተኞች ናቸው፡ መቆናጠጫችን፡፡

Continue reading
  14107 Hits

የኮንስትራክሽን ዋስትና ምንነትና በተግባር የሚስተዋሉ የሕግ ክፍተቶች - ክፍል 2

በክፍል 1 ላይ ጸሐፊው ስለ አጠቃላይ የዋስትና የሕግ ማዕቀፍ በአጭሩ ለማቅረብ ሞክሯል፡፡ በዚህ ክፍል ደግሞ ስለ ኮንስትራክሽን ዋስትና ምንነት፣ ዓይነቶች እንዲሁም በተግባር የሚታዩ ክፍተቶች ይዳስሳል፡፡

 

1. የኮንስትራክሽን ዋስትና (Construction security)

 

በኮንስትራክሽን ውል አፈጻጸም ወቅት በርካታ የዋስትና ዓይነቶች ሲተገበሩ ይታያል፡፡ ከቅድመ ግንባታ ጀምሮ በግንባታ ወቅት አንዳንዴም ከግንባታ በኋላ ለሚከሰቱ ችግሮች ዋስትና ጥቅም ላይ ሲውል ይሰተዋላል፡፡ በተለይም የህንጻ አሰሪዎች (Clients) ግንባታው በፈለጉት ጊዜና ዕቅድ መሰረት እንዲካናወንላቸው ካላቸው ጽኑ ፍላጎት የተነሳ ውሉ እንዲፈጸምላቸው አሰፈላጊ ከለላ እንዲኖራቸው ይሻሉ፡፡

በኢትዮጵያም አብዛኛው የኮንስትራክሽን ውሎች መንግስት አሰሪ በመሆን የሚቀርብባቸው ናቸው፡፡ ለማሳያ ያህል የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ግንባታ፣ የኢንዲስትሪ ፓርኮች ግንባታ፣ የባቡር ዝርጋታ፣ የመንገድ ግንባታዎች ወዘተ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ በተለምዶው የመንግስት ኪስ እርጥብ (solvent) ነው ቢባልም በውል አስተዳደር ወቅት በተለያዩ ምክንያቶች የክፍያ መዘግየት ይስተዋላል፡፡ በዚህ ጊዜም ሥራ ተቋራጩ ልክ እንደ አሰሪው ሁሉ ግዴታ አለተፈጸመልኝም ብሎ ጥያቄ ማቅረብ ይችላል፡፡ በመርህ ደረጃ አሰሪ ሆኖ የቀረበው የመንግስት መስሪያ ቤት ውል ባለመፈጸሙ ምክንያት ሥራ ተቋራጩ ውል አልተፈጸም በሚል መከራከሪያ ሊያቀርብ እንደማይችል ከፍትሐብሔር ሕጉ አንቀጽ 3177 ድንጋጌ እና ከተለመደው የላቲን አባባል፡- ‘Exceptio non adimpleti contractus’ (ግዴታ አለተፈጸመልኝምን እንደ መከራከሪያ አለማቅረብ) መረዳት ይቻላል፡፡

Continue reading
  20001 Hits

የኮንስትራክሽን ዋስትና ምንነትና በተግባር የሚስተዋሉ የሕግ ክፍተቶች - ክፍል 1

መግቢያ

ይህ ጹሑፍ በ6ኛው የኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ኢንቨስትመንት ፎረም ላይ “የኮንስትራክሽን ዋስትና ሕጎች እና የገንዘብ ተቋማት አሰራር” በሚል አውደ ጥናት ላይ ለውይይት የቀረበ ነው፡፡

ዋስትና በውል አፈጻጸም ወቅት እንደተጨማሪ ግዴታ የሚቆጠር በሕግ ፊት ሊጸና የሚችል (juridical act) ተግባር ነው፡፡ በአለፉት ጥቂት ዓመታት ብቻ በአለማችን ከኢኮኖሚያዊ እድገት ጋር ታያይዞ ዋስትና (security) የመጠቀም ልማድ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጧል፡፡

ሆኖም ግን እኤአ ከ2007 ዓ.ም በኋላ ከዓለም ኢኮኖሚ መዳከም ጋር ተያይዞ የዋስትና ጥቅም በአግባቡ የታየበት ብሎም አሰፈላጊነቱም ጭምር ጥያቄ ምልክት ውስጥ የገባበት ጊዜም አይዘነጋም፡፡

ዋስትና መልኩ ይለያይ እንጂ በተግባር አገልግሎት ላይ መዋል የጀመረው እእኤ ከ2750ዓ.ዓ ገደማ ጀምሮ ነበር፡፡ በወቅቱም ዋስትናው ጥሬ ገንዘብ እንደመያዣነት በማቅረብ ነበር፡፡ በተለይ ስለ ሰው ዋስትና (surety) ሕግጋት እና መርሆዎች በተመለከተ ጥናታዊ ሮማዊያን እኤአ በ150ዓ.ም ገደማ ያዘጋጁት ተጠቃሽ ነው፡፡ (ጄፈሪ በርተን፡2000፡9) ከዚያም የሦስተኛ ወገን ዋስትና ወደ ማቅረብ የተሄደበትም ጊዜ ነበር፡፡ ዘመናዊ የፋይናንስ ተቋማት ማደግን ተክትሎ በዋናነት ለዓለምአቀፍ የሽያጭ ግብይቶች ክሬዲ (letters of credit) እየተስፋፋ የመጣበትን ሁኔታ እናገኛልን፡፡

Continue reading
  15612 Hits

ድጋፍ የተሳነው እና እየተዘነጋ የመጣው የኮንስትራክሽን ውሎች አማራጭ የግጭት አፈታት

 “In business as in life, you don’t get what you deserve, you get what you negotiate.”

Dr.Chester L. Karrass

መግቢያ

ግጭት የሰው ልጅ ወደ ምድር ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ  የነበረ፣ ያለ እንዲሁም በእልት ተዕለት የማህበራዊ መስተጋብር ውስጥ ሊከሰት የሚችል አለመግባባት ወይም ልዩነት ነው፡፡ ይህም አለመግባባት በጊዜና በሚገባ ካልተፈታ፣ በማህበረሰብ ውስጥ ከፍተኛ ስጋትና አለመረጋጋት ሊፈጥር ይችላል፡፡ ይህንንም ተግዳሮት ለማስቀረት በማሰብ አብዛኛውን ጊዜ የመንግስት ባህላዊ ተግባር (traditional functions of government) በመባል የሚታወቀው ማለትም ቋሚ የሕግና ፍትሕ ሥርዓት በመገንባት ለሚነሱ ቁርሾዎች መላ ሊያገኙበት የሚችልበትን ሥርዓት መዘርጋት ነው፡፡ ይህም ሊሆን የሚችልበት አንዱ መንገድ መደበኛ ፍርድ ቤቶችን ወይም አማራጭ የግጭት መፍቻ መንገዶችን በየደረጃው በማቋቋምና ለሚነሱ ግጭቶች በጊዜ መፍትሄ በመስጠት ሊሆን ይችላል፡፡

በዓለምአቀፍም ሆነ በአገር ወስጥ የሕግ ሥርዓት አስተማማኝና በቂ የግጭት አፈታት ሥርዓት መኖር በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ይህም መሆኑ በህብረተሰቡ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ኑሮ ውስጥ ሰላምና መረጋጋት ከማምጣቱ ባሻገር ተጠባቂ የሕግ ሥርዓት (Predictable legal system) እንዲኖረን ያደርጋል፡፡

የግጭት አፈታት ሲባልም በግራ ቀኝ በኩል የሚመጣ ማነኛውም ግጭት ወይም አለመግባባት ለመፍታት የሚተገበር ሥነ-ስርዓት ሲሆን ይህም በመደበኛው የፍርድ ሂደት ወይም በአማራጭ የግጭት አፈታት (alternative dispute resolution) መንገድ ሊከናወን ይችላል፡፡

Continue reading
  12608 Hits

አስገዳጁ የኮንስትራክሽን ኢንሹራንስ የሕንጻ መደርመስን ይከላከለው ይሆን?

መግቢያ

ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነው ጉዳይ ልክ የዛሬ አመት ገደማ በአዲስ አበባ ቦሌ ክ/ከተማ ልዩ ስሙ ሰሚት በሚባል ስፍራ የተደረመሰውን ህንጻ እና እሱን ተከትሎ የከተማ አስተዳደሩ ባወጣው ደብዳቤ (circular) መሰረት አስገዳጅ የኮንስትራክሽን ኢንሹራንስ በድጋሜ እንዲኖር መደረጉን በማስመልከት ነው፡፡

እንደሚታወቀው ኢንሹራንስ (መድን) የሚለው ቃል ሲነሳ ምንግዜም ቢሆን ሊዘነጋ የማይችለውጉዳይ የአደጋ (risk) መኖር ነው፡፡ የአደጋ መከሰት ለመድን ቅድመ ሁኔታ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡

ስለ መድን ታሪክ በአጭሩ ለመናገር ስነሳ አባይን በጭልፋ ኢንዲሉ! በጥቅቱ ጠቆም ለማድረግ ያህል የሚከተለውን ዐረፍተ ነገር እጽፋለሁ፡፡ በአለማችን ጥንታዊ የሚባለው መድንበ3ሺህ ዓ.ዓ ቻይናዊያን የጀመሩት ሲሆኑ በወቅቱም ነጋዲያን በሸቀጦቻቸው ላይ በአንድ ማጓጓዢያ እቃ መጫን እና መጠቀም የሚደርሰውን አደጋ ብሎም የሚመጡ የጎርፋ እና መሰል አደጋወችን ለመከላከል በርካታ የማጓጓዣ አማራጮች በወሰዱ ማግስት ነበር፡፡ ከዚያም በሜሶፖታሚያ (ሳምራዊያን) ስልጣኔ ወቅት እየተስፋፋ መመጣቱ በድርሳናት ላይ ሰፍሯል፡፡ በተለይም እኤአ በ1750 ዓ.ዓ በሰፈረው የንጉስ ሐሙራቢ ሕግ እንደተመለከተው ነጋድያን በባህር በሚነግዱበት ወቅት እቃውን በጥሩ ሁኔታ እንዲደርስ አስቀድመው በብድር ያስጭናሉ፤እቃውም በጥሩ ሁኔታ ከደረሰ ለአበዳሪው ተጨማሪ ገንዘብ ጭምር እንደሚከፍል ይናገራል፡፡ ዳሩ ግን ይህ ሳይሆን ቀርቶ ዕቃው ቢጠፋ ወይም ቢዘረፍ የአበዳሪው ዋስትና ሙሉ ኃላፊነት ነው፡፡ (ቫውግሃን፡1997፡3) ከዚያም በኋላ በሜዲትራንያን ባህር የሚደረጉ የንግድ እንቅስቃሴወች ከነጋዲያን አስቀድሞ በተሰበሰበ አረቦን/Premium/ ለሚደርሱ የባህር ላይ ንግድ አደጋወች ማካካሻ ተደርገው ሲሰራባቸው ቆይቷል፡፡

በመካከለኛው ዘመንም በጥናታዊቷ የጣሊያን ዋጀንዋ ከተማ እኤአ በ1347 የመጀመሪያው ዘመናዊ የመድን ውል በሥራ ላይ ዋለ፡፡ ከዚህም የተነሳ መድን ከሌሎች ዓይነት የፍትሃብሄር ድርጊቶች ለመለየት ተሞክሯል፡፡ (ፍራንክሊን፡2001፡274)

ስለ መድን ውል በጠቅላላው ሲታሰብ ከትልቀቱ እና ስፋቱ የተነሳ በርካታ ተግዳሮቶች እንደሚኖሩ የታመነ ነው፡፡ በኢትዮጵያ መድን ሕግ እና ውሎች ዙሪያ በርካታ አሳሳቢ ችግሮች አሉ ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ እንኳንስ በሁለቱም ማለትም በሕግ እና በውሎች ዙሪያ ቀርቶ ከውሎች ውስጥ ጥቂቶችን በሚገባ ተመርጠው በአግባቡ ቢፈተሹ ብዙ አሳሳቢ ችግሮች እንደሚገኙባቸው የሚያከራክር አይደለም፡፡ (ዘካሪያስ ቀንዓ፡1998፡1)

Continue reading
  12749 Hits

በኮንስትራክሽን ውሎች አፈጻጸም ወቅት የመሀንዲሱ ሚና እና የጥቅም ግጭት

መግቢያ

እንደሚታወቀው በኮንስትራክሽን ውሎች አፈጻጸም ወቅት መሀንዲሱ የሚጫወተው ሚና እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡ አንዳንዴም መሀንዲሱ በውኑ የመሀንዲስ አድራጎት የማይመስሉ ተግባራትን ሲያከናውን ይሰተዋላል፡፡ ይህም ነገሩ አጀብ! ቢያሰኝም እውነታው ግን ከዚህ የራቀ አይደለም፡፡

እርግጥ ነው መሀንዲሱ ብዙ አልፎ አልፎም እርስ በእርሳቸው የሚጣረሱ ተግባራትን የሚያከናውንበት ጊዜ አለ፡፡ ለአብነት ያህልም፡-የግንባታው ዲዛይነር፣ የአሰሪው ወኪል (employer’s agent)፣ አማካሪ (supervisor)፣ የሥራ ርክክብ አረጋጋጭ (certifier)፣ ብሎም አንዳንዴ አራጊ ፈጣሪ ገላጋይ ዳኛ ወይም ከፊል አስታራቂ (adjudicator or quasi-arbitrator) ሊሆን ይችላል፡፡

በነገራችን ላይ የመሀንዲሱ ሚና ከላይ በጠቀስናቸው ተግባራት ላይ ብቻ የተወሰነ አይደለም፡፡ በግንባታ ውሉ አፈጻጸም ወቅት አስቀድሞ ለፕሮጀክቱ አፈጻጸም የሚሆኑ ሥራዎን በራሱ አነሻሽነት (proactive works) ወይም ፕሮጀክቱ ወደ ሥራ ከገባ በኋላ ለውሉ አፈጻጸም የሚሆኑ ተግባራት እና ሥራዎችን በአሰሪው ወይም ሥራ ተቋራጩ ትእዛዝ (reactive works) እንዲሁም በውሉ በግልጽ ተለይተው ባይሰጡትም ለፕሮጀክት አፈጻጸም አንድ መደበኛ መሀንዲስ ሊሰራቸው የሚችሉ ሥራወችን ሊያከናውን ይችላል፡፡

አንዳንዴም ባለሃብቶች የመገንባት ሃሳቡ ኑሯቸው ወደ ስራው ሊገቡ ሲሉ ዘርፈ ብዙ የቴክኒክ ችግሮች፣ የምርታማነት እና ንግድ ጉዳዮች እንዲሁም የሕግ መወሳሰብ ባለማወቃቸው ብሎም ከግምት ባለማስገባታቸው የተነሳ እክል ሊገጥማቸው ይችላል፡፡ በሲቪል ምህንድስናው ዘርፍም ይህንን የባለሃብቱን ሃሳብ እና ስጋት ወደ እውነት ለመተግበር አማካሪ መሀንዲሱ ወይም መሀንዲሱየተባለውን ጉዳይ ሊፈጽምለት ይችላል፡፡

ነገሩ እንዲህ ነው! መሀንዲሱም ሆነ አማካሪ መሀንዲሱ በውል የተጣለባቸውን ሥራወች ሲሰሩ ግልጽ የሆነ የጥቅም ግጭት (manifest conflict of interest) ሊከሰት ይችላል፡፡ እነዚህ የጥቅም ግጭቶችም በሥራው ላይ ከተፈጥሮ ሕግ እና ርትዕ(natural law and equity) አንጻር የፍትሃዊነት ጥያቄ ስለሚያስነሳ በጥልቀት እና በአንክሮ መታየት ያለበት ጉዳይ ነው፡፡

Continue reading
  16501 Hits

በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ፈቃድ አስጣጥ በአንድ መስኮት አገልግሎት መሆን መልካም አጋጣሚዎች እና ፈተናው

መግቢያ

ኢንቨስትመንት ቃሉ እንግሊዝኛ ሲሆን አሁን አሁን ግን በአማርኛ ሥነ ጽሑፍም በጣም እየተለመደ በመምጣቱ የአማርኛውን አቻ ቃል ማለትም “ምዋዕለ-ንዋይ” የሚለው መጠሪያ እስከሚዘነጋ ድረስ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን በየእለቱ ይነገራል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት አዋጅ ቁ.769/2005 ሳይቀር መዋዕለ ንዋይ ከማለት ይልቅ ኢንቨስትመንት የሚለውን ቃል ሙሉ በሙል ተጠቅሟል፤ ስለዚህ በዚህ ረገድ አንባቢውን ግራ ላለማጋባት ሲባል ጸሐፊው ኢንቨስትመንት የሚለውን ቃል ለመጠቀም ተገዷል፡፡ የዚህ ጹሑፍ ዓለማ ለምን ምዋዕለ-ንዋይ የሚለው ቃል ኢንቨስትመንት እየተባለ ተጠራ የሚለው ጉዳይ ባይሆንም አገር በቀል መጠሪያዎችን መጠቀም እንድንለምድና እንድናዳብር አስተያየት ለመጠቆም ነው፡፡

የአንድ ሃገር ለውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ተፈለጊ እና ሳቢ የሚያደርጋት የዘረጋችው ሃገራዊ ምቹ የኢንቨስትመንት ፖሊሲ ነው፡፡ ሆኖም ግን ምቹ የሕግ እና የፖሊሲ ማዕቀፍ መኖሩ ብቻ ፍሰቱን እንዲጨምር ላያደርግ ይችላል፡፡ ለምን ቢባል በተግባር የወጡት ፖሊሲዎች እና ሕጎች በአስፈጻሚው አካል ዘንድ የመተግበራቸው ሁኔታ ስለሚያጠያይቅ ጭምር ነው፡፡ እነዚህ አስተዳደራዊ ሥነ ሥርዓቶች ነጻ የኢንቨስትመንት ፈቃድ በሰጡ አገራት ጭምር ከፍተኛ ስጋት ያጭራሉ፡፡ በብዙ ሃገራትም በርካታ ኢንቬስተሮች የሚያቀርቡት ስሞታ እና እሮሮ በተለይም አሰልቺ ከሆኑ አሰራሮች (hectic bureaucracy) መኖር ጋር ይያያዛል፡፡

እርግጥ ነው ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ጥሩ የሕዝብ ግንኙነት  ወይም የገበያ ጥናት ባለሙያዎች መኖራቸው መልካም ተግባር ነው፡፡ በተለየም ቢዝነስ ተኮር የሕዝብ ዲፕሎማሲ በዚህ ረገድ ተጠቃሽ ተግባር ነው፡፡ ታዲያ በዚህ የማስተዋዋቅ ተግባር የተመሰጡ የውጭ ኢንቬስተሮች የተባለችውን አገር ሄዶ ሁኔታውን ለማየት ከመቼው ጊዜ ልባቸው ይነሳል፡፡ በዚህ ጊዜ ታዲያ የሚሄዱበት አገር አስተዳደራዊ ችግር በስፋት የሚታይበት ከሆነ ኢንቬስተሩ አስቀድሞ ስለሁኔታው ሊወስን ይችላል፡፡ ለአብነት ያህልም ኢንቬስተሩ/ሯ ወደ ተባለው አገር ለማምራት ቪዛ ተይቀው በጣም አሰልቺ ነገር ቢገጥማቸው ከራስ ተሞክሮ ውሳኔ ሊዎስኑ ይችላሉ፡፡ (ፍራንክ ሳደር፡እኤአ 2003፡2)

የተባለውን እሰቸጋሪ ውጣ ውረድ አልፈውም ወደ አገር ቤት ሲገቡ ከሌሎች ቀደምት ኢንቨስተሮች ተሞክሮ በመውሰድ ሊያውጡ የሚችሉትን ወጪ፣ መዘግየት፣ የመንግስት ምላሽ እና ለችግሮች የሚሰጠውን መልስ ከግምት በማስገባት አስቀድመው ትረፍና ኪሳራ (cost-benefit analysis) በመስራት የተባለው አስተዳደራዊ ችግር ይኖራል ብለው ካመኑ ልክ እንደ ሌሎች ተጎጂ ላለመሆን ባመጣቸው እግር ወደ መጡበት አገር ይመለሳሉ፡፡

ሌላው ጉዳይ ፈቃድ ሰጭው አካል የቀረበለትን ማመልከቻ ቶሎ መልስ ካልሰጠበት፣ ግለጸኝነት የሚጎድለው ከሆነ እና በጣም ሰፊ የሆነ ፈቅደ ስልጣን (discretionary power) ሚስተዋል ከሆነ ለሌላ ብልሹ አሰራር ማለትም ጉዳይን በቶሎ ከፍሎ ማስፈጸም (practice of “speed payments”) ተግባር አምርቶ ኢንቨስተሮች ፈቃድ ለማግ ኘት ሲሉ መደለያ እና ማግባቢያ ገንዘብ ለነቀዙ ባለስልጣናት ወይም ወኪሎች እንዲከፍሉ ሊገደዱ ይችላል፡፡

Continue reading
  19412 Hits