The blogger worked as a legal expert at the Ethiopian food, medicine, and healthcare administration and control authority and Ethiopian Construction Works Corporation. The blogger is currently working as a qualified and licensed lawyer.

በወንጀል ጉዳይ በዋስትና እንዲፈታ ፍርድ ቤት ያዘዘውን ሰው ፖሊስ ይግባኝ ልል ነው በማለት ግለሰቡን ያለመፍታት የህግ ስልጣን አለው?

የኢፌዲሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 19 (6) ስለተያዙ ሰዎች መብት ሲደነግግ የተያዙ ሰዎች በዋስ የመፈታት መብት እንዳላቸው ሆኖም በህግ በተደነገጉ ልዩ ሁኔታዎች ፍርድ ቤት ዋስትና ላለመቀበል ወይም በገደብ መፍታትን ጨምሮ በቂ የሆነ የዋስትና ማረጋገጫ እንዲቀርብ ለማዘዝ እንደሚችል በግልፅ ተመልክቷል፡፡

ከዚህ ህገ-መንግስታዊ ድንጋጌ መረዳት የሚቻለው የዋስትና መብት መርህ (Principle) ሲሆን በዋስ አለመፈታት ደግሞ ልዩ ሁኔታ (Exception) መሆኑን ነው፡፡ ይህንን ህገ-መንግስታዊ ድንጋጌ ለማስፈፀም ተግባር ላይ ያለው የወ/መ/ስ/ስ/ህግ ምዕራፍ 3 ላይ የዋስትና ወረቀት አስፈርሞ ስለመልቀቅ የሚል ርዕስ ያለው ሲሆን በቁጥር 63 ላይ የዋስትና ወረቀት የሚያሰጡ መሰረታዊ ፍሬነገሮችን ይዘረዝራል፡፡ እነዚህ ፍሬነገሮች ዋስትና የሚያሰጡ ሁኔታዎችን የሚያስረዱ ቢሆንም በተቃራኒው በህግ አተረጓጎም መሰረት ዋስትና የሚያስከለክሉ ሁኔታዎችንም በውስጡ አካቶ ይዟል፡፡

Continue reading
  888 Hits

በኢትዮጵያ ስላሉ ወታደራዊ ፍርድ ቤቶች አንዳንድ ጉዳዮች

 

መግቢያ

በተለያዩ የአለማችን ክፍሎች የተለያዩ የከፉ የዘር ማጥፋት ወንጀሎች (Genocide)፣ በሰው ልጆች ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች (Crimes against Humanity)፣ የጦር ወንጀሎች (War Crimes) እና የወረራ ወንጀሎች (Crime of aggression)፣ በሰላም ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች (Crime against Peace) እንዲሁም ወታደራዊ ወንጀሎች በተለያዩ ሰዎች አማካኝነት በተለያዩ የሰው ልጆች እና ተቋማት ላይ ሲፈፀሙ እንደነበር ታሪክ ይነግረናል፡፡ በአሁን ሰዓትም እነዚህ ወንጀሎች ከመሰራት አልቦዘኑም፡፡ የአንድ ሀገር የመከላከያ ሰራዊት አባል ወይም እንደአግባቡ ማንኛውም ሰው ለሚፈፅሙት የወንጀል ተግባር የሚቀርብባቸውን የወንጀል ጉዳዮች የሚመለከቱ ሀገር አቀፍ ወይም አለምዓቀፍ ወታደራዊ ፍርድ ቤቶች አሉ፡፡ እነዚህ ፍርድ ቤቶች ወታደራዊ ፍርድ ቤት (Military Court) ወይም (Court-Martial) በመባል ይታወቃሉ፡፡ እነዚህ ፍርድ ቤቶች ከመደበኛው የሲቪል ፍርድ ቤቶች የተለዩ እና ቋሚ ወይም ጊዜያዊ ሆነው-ለተወሰነ ዓላማ እና ጊዜ የሚቋቋሙ ፍርድ ቤቶች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

Continue reading
  558 Hits

የከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች ስልጣን ከአዲሱ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ አንፃር

 

በአሁን ሰዓት በሀገራችን ኢትዮጵያ ሁለት የከተማ አስተዳደሮች ማለትም የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች ይገኛሉ፡፡ እነዚህም የከተማ አስተዳደሮች ህጋዊ ጥንስሳቸው የአዲስ አበባ ከተማ ህገ-መንግስታዊ መሰረት ያለው ሲሆን የድሬዳዋ ከተማ ደግሞ የቻርተር መሰረት ያለው ነው፡፡ በዚህም መሰረት በኢፌዲሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 49 (1) መሰረት የፌዴራሉ መንግስት ርዕሰ ከተማ አዲስ አበባ ነው በማለት ለከተማው እውቅና ሰጥቷል፡፡ የህገ-መንግስቱ አንቀፅ 49 (2) የአዲስ አበባ ከተማ ራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ ስልጣን እንዳለውም ደንግጓል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የድሬዳዋ አስተዳደር ቻርተር አዋጅ ቁጥር 416/96 የድሬዳዋ ከተማን በማቋቋም እራሱን በራሱ እንደሚያስተዳድር ደንግጓል፡፡

ማንኛውም የከተማ አስተዳደር እራሱን በራሱ ሲያስተዳድር በህግ አግባብ የተቋቋሙ ሶስቱ የመንግስት አካላት ማለትም ህግ አውጪ፣ ህግ አስፈፃሚና ህግ ተርጓሚ አካላት ይኖራቸዋል፡፡ በዚህም አግባብ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቻርተር አዋጅ ቁጥር 361/95 እንዲሁም የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በቻርተር አዋጅ ቁጥር 416/96 መሰረት የራሳቸውን የከተማ ፍርድ ቤቶች አቋቋመው በስራ ላይ ይገኛሉ፡፡ የከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች ማለት የአዲስ አበባና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች ማለት እንደሆነ አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀፅ 2 (10) በግልፅ አመላክቷል፡፡

እነዚህ የከተማ ፍርድ ቤቶች የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 በስራ ላይ ሲውል ስልጣንና ሀላፊነታቸውን በማሻሻል ብቅ ብሏል፡፡ እነዚህ የከተማ ፍርድ ቤቶች ምን አይነት አዲስ ስልጣን ተጨመረላቸው?፣ በፍትሐብሄር እና በወንጀል ጉዳዮች ስልጣናቸው እስከምን ድረስ ነው? እና በተጨመረላቸው ስልጣን ምክንያት የስራ ጫና ሊኖር ስለሚችል ምን አይነት ዝግጅት ማድረግና በህዝብና በተገልጋዩ ማህበረሰብ አመኔታ ያላቸው ፍርድ ቤቶች ለመሆን ምን ማድረግ ይጠበቅባቸዋል የሚሉትን እንደሚከተለው በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡ መልካም ንባብ፡፡

 

Continue reading
  8666 Hits

የፍርድ ቤቶች የእግድ ትእዛዝ ተፈፃሚነት እስከየት ድረስ ነው?

 

 

ለአንድ ሀገር ሰላም፣ ዲሞክራሲ፣ የሕግ የበላይነትና ፍትሕ መረጋገጥ እንዲሁም ሰብዓዊ መብቶች መከበር በሕግ አግባብ የተቋቋሙ ገለልተኛ፣ ነፃ፣ ተጠያቂነት ያለባቸው እና በሕዝብ ዘንድ አመኔታን ያተረፉ ፍርድ ቤቶች ሚና የጎላ እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡ ያለሕግ እና ያለፍርድ ቤቶች ሰላም፣ ዲሞክራሲ፣ የሕግ የበላይነትና ፍትሕ በአንድ ሀገር ውስጥ ይኖራል ብሎ መገመት አይቻልም፡፡

እነዚህ ፍርድ ቤቶች አሁን ባለው የሀገራችን ሕገ-መንግሥት ነፃ ሆነው መቋቋማቸውን እና በሀገሪቱ ውስጥ በፌዴራልም ሆነ በክልል ግዛቶች ሥር ብቸኛው የዳኝነት አካል እንደሆኑ ሕገ-መንግሥታዊ ማረጋገጫ አግኝተዋል፡፡ በዚህም አግባብ ሥራቸውን እያከናወኑ ይገኛሉ፡፡

በሰዎችም መካከል አለመግባባት ሲፈጠር በሰላማዊ መንገድ በስምምነት፣ በድርድር ወይም በሽምግልና ወይም በእርቅ ለመፍታት ካልቻሉ ሥልጣን ወዳላቸው መደበኛ ወይም ሕጋዊ እውቅና ወደተሰጣቸው ፍርድ ቤቶች እንደሚሔዱ ይታወቃል፡፡

Continue reading
  9453 Hits

ስለወለድ እና የወለድ ወለድ አስተሳሰብ ደንቦች በጨረፍታ

 

 

  1. መግቢያ

ሰዎች ንብረታቸውን የሚመለከቱ ጉዳዮችን በተመለከተ አንድን ግዴታ ለማቋቋም ወይም ለመለወጥ ወይም ለማስቀረት ባላቸው ተወዳዳሪ ግንኙነት በሁለት ወይም በብዙ ሰዎች መካከል ስምምነት ሲፈፅሙ ውል እንዳደረጉ ከኢትዮጵያ የፍትሐብሄር ህግ ቁጥር 1675 መረዳት ይቻላል፡፡ አንድ ውል ከተደረገ በኋላ በአንደኛው ወይም በሁለቱም ተዋዋይ ወገኖች ላይ ግዴታን ይጥላል፡፡ ይህንን ግዴታ በተባለው ጊዜ አለመፈፀም ወይም ጊዜ ካልተቀመጠ ደግሞ ማዘግየት የሚያስከትለውን ኪሳራ በተመለከተ ተዋዋይ ወገኖች ገደብ ወይም ቅጣት ወይም አንድ የተወሰነ ወለድ ግዴታውን ያልፈፀመ ተዋዋይ ወገን ውሉን ላከበረው ወገን እንዲከፍል ሲዋዋሉ መመልከት ወይም በፍርድ ቤቶች ሲወሰን ማየት የተለመደ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ወለድና የወለድ ወለድ (Interest on interest or compound interest) አስተሳሰብ ደንቦችን በተመለከተ እና ተያያዥ ጉዳዮችን የኢትዩጵያ ህጎች ላይ ተመስርተን በጨረፍታ እንደሚከተለው እንዳስሳለን፡፡

  1. ትርጓሜ

ወለድ የሚለውን ፅንሰ ሀሳብ ስንመለከተው አንድ ገንዘብ ያበደረ ሰው ተበዳሪው ብድሩን በመጠቀሙ ላበዳሪው ወገን በበኩሉ የሚከፍለው ወይም አንድ የባንክ ደንበኛ ያለውን ገንዘብ በአንድ ባንክ ገንዘብ ተቀማጭ ሲያደርግ በመቶኛ የሚታሰብ ገንዘብን የሚመለከት ወይም ተበዳሪ የወሰደውን ገንዘብ ወይም እቃ በወቅቱ ባለመመለሱ የተነሳ የሚከፈል የገንዘብ ካሳ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ወለድ ለገንዘብ ብድር ብቻ የሚከፈል ሳይሆን አንድ ግዴታን ባለመፈፀም ወይም በማዘግየት እና ይሄ ፍሬ ነገር ሲረጋገጥ የሚከፈል ጭምር ነው፡፡ በተጨማሪም ወለድ በስምምነት ወይም ያለስምምነት ማለትም በህግ አግባብ ሲወሰን ሊከፈል የሚችል ገንዘብ ነው፡፡ ለዚህ ፅሁፍ ዓላማ ሲባል በመቶኛ የሚታሰበውን ገንዘብን በሚመለከት ብቻ ያለውን እናያለን፡፡

የወለድ ወለድ ማለት በሚከፈል ወለድ ላይ በስምምነቱ ወይም በህግ መሰረት ወለዱን በወቅቱ ያልከፈለ ወገን በወለዱ ላይ የሚከፍለው ተጨማሪ የወለድ ወለድ እንደመቀጫ ያለ ገንዘብ ማለት ነው፡፡

Continue reading
  19021 Hits
Tags:

አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 እና አንዳንድ ጉዳዮች

 

ከዚህ ቀደም በሀገራችን ኢትዮጵያ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይን የሚገዙ ሕጎች እንደነበሩ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ በ1955 ዓ.ም የወጣው የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 210/1955፣ በ1968 ዓ.ም የወጣው የሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 64/1968፣ የሠራተኛ ጉዳይ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 85/1968፣ ስለአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ የወጣው አዋጅ ቁጥር 42/1985 እና አዋጅ ቁጥር 377/1996 የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

ከየካቲት 18 ቀን 1996 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ በግሉ ዘርፍ ያለውን የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነትና መስተጋብር እንደ ዋነኛ ምሰሶ በመሆን ሲያስተዳድር የነበረው ሕግ አዋጅ ቁጥር 377/1996 እና የዚህ አዋጅ ማሻሻያ ሕጎቹ አዋጅ ቁጥር 466/1997 እና አዋጅ ቁጥር 494/1998 ነበሩ፡፡ እነዚህ ሕጎች ከ14 አመታት በላይ በሥራ ላይ የዋሉ በመሆናቸው አሁን ካለው የማህበረሰብ እድገት ጋር የተጣጣሙ ባለመሆናቸው የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቀን ሰኔ 27 ቀን 2011 ዓ.ም ባደረገው 4ኛ አመት የሥራ ዘመን 48ኛ መደበኛ ስብሰባው የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ረቅቅ አዋጅን መርምሮ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡

ይህም ሕግ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ዓ.ም ሆኖ ነሐሴ 30 ቀን 2011 ዓ.ም በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ በሥራ ላይ ውሏል፡፡ ይህ አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ምን ምን ሀሳቦችን አካቶ ነው የተሻሻለው? ለሠራተኛው ምን ዓይነት ሕጋዊ ጥቅምና መብቶችን አካቷል? እንዲሁም የአሠሪ ግዴታና መብት ምን ይመስላል? የሚሉትን ጉዳዮች እና አዲሱን አዋጅ ከተሻረው የአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ቁጥር 377/96 በማነፃፀር በወፍ በረር (Bird’s Eye View) እንደሚከተለው እንመለከታለን፡፡

አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ከዚህ ቀደም የነበረውን አዋጅ ከነ ማሻሻያዎቹ በመሻር እና የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጄንሲ አዋጅ ቁጥር 632/2001ን በአዲሱ አዋጅ ውስጥ በማካተት ነው በሥራ ላይ የዋለው፡፡

Continue reading
  74978 Hits