ጦማሪው ከሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት በ2007 ዓ.ም በሕግ በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቀ ሲሆን አሁን በፌዴራል ማናቸውም ፍርድ ቤቶች በሕግ አማካሪና በጠበቃነት በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡

ጸሐፊውን mulukenseid29@gmail.com ወይም +251917324914 ማግኘት ይችላሉ፡፡

በደርግ ዘመን አዋጅ ቁጥር 47/67 ተግባራዊ በሆነበት ወቅት ያላግባብ የተወረሱ የግለሰብ ቤቶች አሁን ላይ ለግለሰቦቹ ወይም ለሕጋዊ ወራሾቻቸው ሊመለሱ የሚችሉበት የሕግ አግባብን በተመለከተ ከሰበር ውሳኔዎች ጋር ተገናዝቦ የቀረበ

የንጉሣዊ ሥርዓት መውደቁን ተከትሎ ወደ መንግሥታዊ ሥልጣን የመጣው ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ የከተማ ቦታና ትርፍ ቤት የመንግሥት ንብረት ለማድረግ በሚል አዋጅ ቁጥር 47/1967 በማወጅ ተግባራዊ አድርጓል፡፡ ይህ አዋጅ ሊታወጅ ያቻለበት ዋነኛ መነሻ ምክንያት “በከተሞች ውስጥ የሚገኙ አብዛኛዎቹ ቦታዎችና ቤቶች በጥቂት መሳፍንት፣ መኳንንትና በከፍተኛ የመንግሥት ባለ ስልጣኖችና ከበርቴዎች በመያዛቸው እንዲሁም የሀብታም ክፍሎች ያላቸውን ከፍተኛ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ኃይል ያለ አግባብ በመጠቀም ሰው ሰራሽ የከተማ ቦታ እጥረት በመፍጠር የከተማ ቦታ ዋጋን እንዲወደድ በማድረግ በጠቅላላው የብዝበዛ ሥርዓት ጠንክሮ ለከተማው እድገትና ለብዙኃኑ የከተማ ነዋሪዎች የኑሮ መሻሻል ከፍተኛ እንቅፋት በመሆናቸው” በሚል አዋጁን መሠረት በማድረግ የከተማ ቦታና ትርፍ ቤት የመንግሥት ንብረት ሊሆን ችሏል፡፡

  11697 Hits

ከውርስ ኃብት ክፍፍል ጋር የተያያዙ አንዳንድ ነጥቦች ከፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከሰጣቸው ውሰኔዎች ጋር በማገናዘብ የቀረበ

የሟች የውርስ ኃብት ተጣርቶ ከተዘጋ በኋላ የውርስ ኃብት ባለቤትነት ወደ ሟች ወራሾች ይተላለፋል፡፡ በመሆኑም ውርስ ከተዘጋ በኋላ ወራሾች መሀከል ክፍያ እስኪፈጸም ድረስ የሟች ወራሾች በሀብቱ ላይ ያላቸው መብት ምንድነው? ክፍፍሉ ከመፈጸሙ በፊት በጋራ ወራሾች የተያዘ ንብረት በአንደኛው ወራሽ ብቻ ለሶስተኛ ወገን በሽያጭ ቢተላለፍ ፈቃዳቸውን ያልሰጡ ወራሾች መብታቸው እስከምን ድረስ ነው? ገዥውን ያለውስ መብት ምንድነው? የውርስ ሀብት ክፍፍል የሚደረግባቸው ስነ-ስርዓቶችንና ክፍፍል ከተደረገ በኋላ የሚገኙ የውርስ ኃብት የሆኑ ንብረቶች ለወራሾች ሊከፋፈሉ የሚችሉባቸው የህግ ስርዓቶችን በተመለከተ በወራሾችና ወራሽ ባልሆኑ ሶስተኛ ወገኖች መሀከል እስከ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ድረስ የደረሱ አከራካሪ ጉዳዮች አሉ፡፡ በዚህ ጽሁፍ እነዚህን ነጥቦች በተመለከተ ከፍትሐብሔር ሕጉና ከተመረጡና አስገዳጅ ከሆኑ የሰበር ውሳኔዎች አንጻር አጭር ዳሰሳ ለማድረግ እሞክራለሁ፡፡

  5519 Hits

የውል ሕግ ይርጋዎች ከተመረጡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች ጋር ተገናዝቦ የቀረበ

በዚህ ጽሁፍ በፍትሐብሔር ሕጉ ስለ ውል በተደነገገው ክፍል ስር የተጠቀሱ አጠቃላይ የይርጋ ድንጋጌዎችንና በልዩ የውል ሕግ ክፍል በተለይም የስጦታ ውል፣ የአደራ ውል፣ የሽያጭ ውል ውልን መሰረት በማድረግ የተደነገጉ የይርጋ ድንጋጌዎችንና የመያዣ ውል ቀሪ ስለሚሆንበት የሕግ አግባብ ከፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አስገዳጅ ከሆኑ የሰበር ውሳኔዎች አግባብ ዳሰሳ ለማድረግ ተሞክሯል፡፡

  4613 Hits

ስለ ይዞታ እና የቀዳሚነት ግዥ ይገባኛል የማለት መብት

በዚህ አጭር ጽሁፍ የይዞታ ትርጉም ምን እንደሆነ፣ ይዞታን መሰረት ያደረገ የሁከት ይወገድልኝ ክስ በምን አግባብ ሊቀርብ እንደሚችልና ይህ ክስ ከባለቤትነት ክርክር ጋር ያለው ልዩነት ምን እንደሆነ፣ ሁከት ይወገድልኝ የሚል ክስ ሲቀርብ ፍርድ ቤቶች የሚይዙት ጭብጥ በተመለከተ ዳሰሳ ተደርጎበታል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የቀዳሚነት ግዥ ይገባኛል የማለት መብት ትርጓሜው ምን እንደሆነና ቀዳሚ የመግዛት መብት ካለው መሀከል ባልና ሚስትን፣ ወራሾችን በተመለከተ በህጉ ሊስተናገዱ የሚችሉበት አግባብ ለማየት ተሞክሯል፡፡ በስተመጨረሻም የቅድሚያ ግዥ መብት ያለው ሰው በሚገዛበት ጊዜ ስላለው የሽያጭ ስነ-ስርዓት፣ ግድግዳና ጣራቸው በአንድ በኩል የተያያዙ ቤቶችን በተመለከተ በቅድሚያ ግዥ መብት ሊስተናገዱ የሚችሉበት የህግ አግባብና የዘመዶች በቅድሚያ የመግዛት መብትን እስመልክቶ በጽሁፍ በወፍ በረር ቅኝት ተደርጎበታል፡፡ 

  3638 Hits

ስለባልና ሚስት የጋራ እና የግል ንብረቶች በተመለከተ የፌዴራሉን የቤተሰብ ሕግና የተመረጡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎችን መሰረት በማድረግ የቀረበ

በፌዴራሉ የቤተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር 213/1992 ከአንቀጽ 2 እስከ 4 በተጠቀሱት ድንጋጌዎች  ጋብቻ በክብር መዝገብ ሹም ፊት፣ በኃይማኖት እና በባሕል ሥርዓት መሠረት ሊፈጸም ይችላል፡፡ ከእነዚህ የጋብቻ መፈጸሚያ ስርዓቶች ውስጥ በአንደኛው ስነ-ስርዓት ጋብቻ የተፈጸመ እንደሆነ በጥንዶቹ መካከል በሕግ እውቅና የተሰጠው የትዳር ግንኙነት ተመስርቷል ይባላል፡፡ ጥንዶቹ ከዚህ በላይ ከተጠቀሱት የጋብቻ መፈጸሚያ መንገዶች ውስጥ በአንዱ ጋብቻ ቢፈጽሙ የጋብቻ ውጤትን መሠረት በማድረግ በሕግ የጋራ እና የግል ንብረቶቻቸው ላይ የሚኖረው ውጤት ተመሳሳይ ነው፡፡  

  14821 Hits

የሽያጭ ውልን የተመለከቱ አንዳንድ ነጥቦች ከሰበር ውሳኔ ጋር ተገናዝቦ የቀረበ

መግቢያ

በዚህ ጽሑፍ የሽያጭ ውል ምንነት፣ የማይንቀሳቀስ ንብረት የገዛ ሰው ስላለው መብትና ገዥው ስለሚኖርበት ግዴታ፣ የሽያጭ ውልን መሰረት አድርገው የሚቀርቡ ክርክሮች ይዘታቸው እና  የይርጋ ገደባቸው ምን እንደሚመስል እንዲሁም የማይንቀሳቀስ ንብረት የገዛ ሰው ንብረቱን ሊለቅ የሚችልባቸው የሕግ አግባብ ምን ምን እንደሆኑ ከፍትሐብሔር ሕግ እና ከሰበር ውሳኔዎች አንጻር ዳሰሳ ለማድረግ ተሞክሯል፡፡   

  11343 Hits

ጋብቻ በሚፈርስበት ወቅት የባልና ሚስት የንብረት ክፍፍል ሥነ-ሥርዓት ከሰበር ውሳኔዎች ጋር ተገናዝቦ የቀረበ

መግቢያ

ጋብቻ የተፈጸመበት ስነ-ስርዓት ማናቸውም አይነት ቢሆንም የጋብቻ መፍረስ የሚያስከትለው ውጤት ተመሳሳይ ነው፡፡ ጋብቻ ከተጋቢዎቹ አንዱ ሲሞት ወይም በፍርድ ቤት የመጥፋት ውሳኔ ሲሰጥ ወይም ጋብቻ ለመፈጸም መሟላት ያለባቸው ሁኔታዎች አንዱ በመጣሱ ምክንያት በሕግ ጋብቻው እንዲፈርስ ሲወሰን ወይም የፍቺ ውሳኔ ሲሰጥ ሊፈርስ ይችላል፡፡

  22819 Hits

ስለ ኑዛዜ ከውርስ ሕግና ከሰበር ውሳኔዎች ጋር ተገናዝቦ የቀረበ

የኢትዮጵያ የውርስ ሕግ ኑዛዜ ማለት ምን ማለት እንደሆነ የሰጠው ትርጉም ባይኖርም አንድ ኑዛዜ ህጋዊ ውጤት እንዲኖረው ማሟላት የሚገባቸውን መስፈርቶች ምን ምን እንደሆኑ በዝርዝር የሚያስቀምጡ የሕግ ድንጋጌዎችን ከፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 857 እስከ 908 ተደንግጎ እናገኘዋለን፡፡ በዚህ ጽሁፍ ኑዛዜ በምን አግባብ ቢደረግ በሕግ ዘንድ ውጤት ይኖረዋል፤በውርስ ሕጋችን ላይ የተቀመጡት የኑዛዜ አደራረግ ስርዓቶች አስገዳጅነታቸው እስከምን ድርስ እንደሆነና ኑዛዜ በፍርድ ቤት ቢጸድቅ ሊያስገኝ የሚችለው ውጤትና ባለመጽደቁ የሚያመጣው ተጽእኖ ምን እንደሆነ ከውርስ ሕግ እና አስገጋጅ ከሆኑ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ውሳኔዎች አንጻር  በአጭሩ ዳሰሳ ለማድርግ ተሞክሯል፡፡ 

  11377 Hits

Legal updates on federal court establishment proclamation, proclamation number 1234/2021

Introduction

The Federal Court Proclamation no 25/96 its amendment, which has been in force for many years, is repealed and replaced by the federal courts' Proclamation number 1234/2021.  When we look at the existing proclamation, the new law introduced new elements. In these short notes, we will briefly explore the new features of the proclamation and the reason behind the improvements of the proclamation to its current content.

  12143 Hits
Tags:

Brief summary major reforms introduced by Movable Property Security Rights Proclamation, No.1147/2019

 

Introduction

Before the enactment of movable property security right proclamation, Ethiopian movable security right law is ultimately unsatisfactory because it is fragmented, and contained in four different pieces of legislation: The Civil and Commercial Codes, the Business Mortgage Proclamation, the Proclamation to Provide for a Warehouse Receipts System (Warehouse Receipts Proclamation), and the Capital Goods Leasing Business Proclamation. Under this system, security rights in many movable assets are not registered.

  9623 Hits