ጸሐፊው በሕግ የመጀመሪያ ዲግሪ ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ያገኙ ሲሆን ከ5 አመት በላይ በተለያዩ መሥሪያ ቤቶች በሕግ ባለሙያነት እንዲሁም በኃላፊነት አገልግለዋል፡፡ ጸሐፊው አሁን ጠበቃና የሕግ አማካሪ ሲሆኑ በተጨማሪም በኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ላይ በየሳምንቱ አርብ ጠዋት የሚቀርብ "ሕጉ ምን ይላል" የተሰኘ ፕሮግራም እያሰናዱ በማቅረብ ላይ ይገኛሉ፡፡

በሕገ መንግሥት ማሻሻያ አንቀጽ 39ኝን መቀየር ይቻል ይሆን?

ሕገ መንግሥት ማሻሻል ማለት ምን ማለት ነው

ሕገ መንግሥት ማሻሻል ማለት በአጭር አነጋገር ለሕገ መንግሥት ማስተካከያ የሚደረግበት ሂደት ነው ማለት ይቻላል፡፡ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ሂደት ክለሳ (Revision) አብዮት (Revolution) ማለት አይደለም፡፡ (ቃለአብ ታደሰ) አብዛኛው ጊዜ ማሻሻያ የሕገ መንግሥቱን ቃላት፣ ሃረግ፣ ዓ.ነገር ወይንም አንቀፆችን ሊያጠቃልል ይችላል፡፡ በእነዚህ በሚሻሻሉት ፋንታ በከፊል መጨመር፣ መቀነስ ወይንም ሙሉ በሙሉ መለወጥ ሊሆን ይችላል፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ ሁሉ ለውጦች ከሕገ መንግሥቱ አጠቃላይ አላማ፣ ግብና መንፈስ ጋር በሚጣጣም መልኩ መሆን አለበት፡፡ (ቃለአብ ታደሰ፡ 2011)

  7312 Hits

የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ መቁረጥ እና ሕጋዊነቱ

ለዚህ ጽሑፍ መነሻ የሆነው ገበታ ለሃገር መርሃግብር የመንግሥት ሠራተኞች የወር ደሞዛቸውን ለገሱ የምትል ዜና በተደጋጋሚ በመስማቴ እና እውነት በዚህ የኑሮ ውድነት እነዚህ የመንግሥት ሠራተኞች ደሞዛቸውን የሚለግሱት ጎርጎራ፣ ወንጪ አሊያም ኮይሻ  ላይ ሆቴል መሰራቱ ከጊዚያዊ ችግሮቻችን ይበልጣል ብለው አምነው ወይስ በአለቆቻቸው ተፅዕኖ ሥር በመሆናቸው ተገድደው የሚለው ጥያቄ በተደጋጋሚ ውስጤ ሲመላለስ በመቆየቱ ነው፡፡ መልካም ንባብ!

  13877 Hits