Permanency Rule Dilemma To Designate Grave Willful Injury Crime Of Ethiopian Criminal Code Of 2004: The Practice In Oromia Regional State

 

‘Write Your Injuries in Dust and Your Benefits in Marble’ – Benjamin Franklin.

Abstract

Though it needs statically documented data to conclude so, the practice demonstrates that bodily injury crime is one of the most frequently committed crimes. Nonetheless, there is no common worldwide standard to define what constitutes bodily injury crime and to classify bodily injury crime, particularly to grave bodily injury crime and common willful injury crime.

Continue reading
  896 Hits
Tags:

Elucidating Some Legal Insufficiency Of Prosecutors and Police Liaison For Criminal Investigation In Ethiopia: The Case Of Oromia Regional State

Abstract

22 July 1991 to 21 August 1995, and 21 August 1995 to present by Transitional Charter and Federal Democratic Republic of Ethiopia (FDRE) constitution, respectively, Ethiopia adopted a federal system and structured the regions along ethnic lines. And Oromia Regional State (ORS) is Ethiopia's most populous and largest region. 

Continue reading
  954 Hits
Tags:

The Penumbra of Wish-Washy Stands of FDRE Cassation Division on Corporate Criminal Liability Model of Ethiopia: Case Analysis

 

Introduction

This commentary analyses two self-contradictory criminal cases decision of Federal Democratic Republic of Ethiopia (FDRE)Supreme Court cassation division (hereinafter referred as the division) that have equal legal value on all subordinate courts of Federal as well as Regional States to date. The central issue of these cases was the model of corporate criminal liability in Ethiopian criminal justice system.

Continue reading
  952 Hits
Tags:

ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ

መግቢያ ፡- ተበዳዮች በወንጀል ፍትሕ ሥርዓቱ የነበራቸው የተሳትፎ ሚና፡ ጥቅል ምልከታ

በኢትዮጵያ የወንጀል ተጎጂዎች በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ያላቸው ሚና ከነበረበት የማማ ደረጃ በጊዜ ሂደት ‹‹ከማማ የመውረድ›› ያህል ዝቅ እያለ መጥቷል። ሀገሪቱ በዳግም የኢጣሊያ ወረራ ተፈፅሞባት ከመያዝዋ እ.እ.አ ከ 1935 ዓ.ም በፊት በወንጀል ጉዳት ደርሶባቸው በቀጥታ ተበዳይ የሆኑ ሰዎች ወይም የተበዳይ ተወካይና ቤተዘመዶች በደል ካደረሰባቸው ሰው ፍትሕን በገዛ እጃቸው ያገኙ ነበር። ተበዳይ ጥቃት ያደረሰበትን ሰው ሲፈልግ ይበቀላል፣ ሲፈልግ በፍርድ አደባባይ ይከሳል ወይም ለደረሰበት በደል ከተበዳይ ከሳ ይቀበላል። አይ ይህን ሁሉ አልፈልግም ካለም ከሁሉም ታቅቦ ፍትሕን ከእግዚአብሔር እየጠየቀ ይኖራል። በዚህ ጊዜ ምርመራ አጣርቶ ክስ የሚመሰርት የዐቃቤ ሕግ ተቋም በሀገሪቱ አልነበረም። በግለሰቦች መሀከል የሚፈጠር አለመግባባቶችን ‹‹የወንጀል›› ጉዳይ እና የግለሰቦች የፍትሐብሔር ጉዳይ ብሎ የሚከፋፍል የሕግ ስርአት ባለመኖሩ ጥቂት በሀይማኖትና በመንግስት ላይ የሚፈፀሙ በአሁኑ ሰአት የፓለቲካ ወንጀል እየተባሉ ከሚጠሩ ወንጀሎች በስተቀር ሁሉም አለመግባባቶች ላይ ግለሰቦች በራሳቸው ከሳሽ በመሆን ጉዳያቸውን ለፍርድ ቤት ያቀርባሉ ወይም ፍትሕን በእጃቸው ያገኙ ነበር። ጉዳያቸውን ወደ ፍርድ ቤት የሚወስዱ ከሆነ ክስ የመመስረት፣ የተጀመረን ክስ የሟቋረጥ፣ ቅጣትን በመምረጥ ተበዳይ ግለሰብ ሁሉን አድራጊ ነበር። የወንጀል ይዘት ያላቸው ጉዳዮችን ከፍትሀብሔር ጉዳዮች ጋር በማጣመር የጉዳት ካሳን መጠየቅም ይቻል ነበር። በዘመኑ የወንጀል ተበዳዮች በወንጀል ጉዳይ የሉአላዊ ስልጣን ባለቤቶች ነበሩ።

Continue reading
  1810 Hits

በወንጀል ጉዳይ በዋስትና እንዲፈታ ፍርድ ቤት ያዘዘውን ሰው ፖሊስ ይግባኝ ልል ነው በማለት ግለሰቡን ያለመፍታት የህግ ስልጣን አለው?

የኢፌዲሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 19 (6) ስለተያዙ ሰዎች መብት ሲደነግግ የተያዙ ሰዎች በዋስ የመፈታት መብት እንዳላቸው ሆኖም በህግ በተደነገጉ ልዩ ሁኔታዎች ፍርድ ቤት ዋስትና ላለመቀበል ወይም በገደብ መፍታትን ጨምሮ በቂ የሆነ የዋስትና ማረጋገጫ እንዲቀርብ ለማዘዝ እንደሚችል በግልፅ ተመልክቷል፡፡

ከዚህ ህገ-መንግስታዊ ድንጋጌ መረዳት የሚቻለው የዋስትና መብት መርህ (Principle) ሲሆን በዋስ አለመፈታት ደግሞ ልዩ ሁኔታ (Exception) መሆኑን ነው፡፡ ይህንን ህገ-መንግስታዊ ድንጋጌ ለማስፈፀም ተግባር ላይ ያለው የወ/መ/ስ/ስ/ህግ ምዕራፍ 3 ላይ የዋስትና ወረቀት አስፈርሞ ስለመልቀቅ የሚል ርዕስ ያለው ሲሆን በቁጥር 63 ላይ የዋስትና ወረቀት የሚያሰጡ መሰረታዊ ፍሬነገሮችን ይዘረዝራል፡፡ እነዚህ ፍሬነገሮች ዋስትና የሚያሰጡ ሁኔታዎችን የሚያስረዱ ቢሆንም በተቃራኒው በህግ አተረጓጎም መሰረት ዋስትና የሚያስከለክሉ ሁኔታዎችንም በውስጡ አካቶ ይዟል፡፡

Continue reading
  1967 Hits

በኢትዮጵያ ስላሉ ወታደራዊ ፍርድ ቤቶች አንዳንድ ጉዳዮች

 

መግቢያ

በተለያዩ የአለማችን ክፍሎች የተለያዩ የከፉ የዘር ማጥፋት ወንጀሎች (Genocide)፣ በሰው ልጆች ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች (Crimes against Humanity)፣ የጦር ወንጀሎች (War Crimes) እና የወረራ ወንጀሎች (Crime of aggression)፣ በሰላም ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች (Crime against Peace) እንዲሁም ወታደራዊ ወንጀሎች በተለያዩ ሰዎች አማካኝነት በተለያዩ የሰው ልጆች እና ተቋማት ላይ ሲፈፀሙ እንደነበር ታሪክ ይነግረናል፡፡ በአሁን ሰዓትም እነዚህ ወንጀሎች ከመሰራት አልቦዘኑም፡፡ የአንድ ሀገር የመከላከያ ሰራዊት አባል ወይም እንደአግባቡ ማንኛውም ሰው ለሚፈፅሙት የወንጀል ተግባር የሚቀርብባቸውን የወንጀል ጉዳዮች የሚመለከቱ ሀገር አቀፍ ወይም አለምዓቀፍ ወታደራዊ ፍርድ ቤቶች አሉ፡፡ እነዚህ ፍርድ ቤቶች ወታደራዊ ፍርድ ቤት (Military Court) ወይም (Court-Martial) በመባል ይታወቃሉ፡፡ እነዚህ ፍርድ ቤቶች ከመደበኛው የሲቪል ፍርድ ቤቶች የተለዩ እና ቋሚ ወይም ጊዜያዊ ሆነው-ለተወሰነ ዓላማ እና ጊዜ የሚቋቋሙ ፍርድ ቤቶች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

Continue reading
  1547 Hits

ማቀባበል (Facilitating Act of Bribery)

(ለጉቦኞች አይላላኩ፤ ከተላኩ ዘብጥያ ይላካሉ!)

ይህ አጭር ጽሑፍ በማወቅም ባለማወቅም የወንጀል አድራጊዎች ተልእኮ የሚያስፈጽሙ ሰዎች እንዲጠነቀቁ ለማስቻል በግርድፉ የቀረበ ነው፤ ጥልቀት ያለው ትንተና እንዳይጠብቁ። ጽሑፉ ሰዎች የቆሸሸ ገንዘብ የሚያቀባብሉበት እጃቸው፣ እንዲሁም የጉቦኞች የገንዘብ መላላኪያ የሚያደርጉት የባንክ ሂሳብ ቁጥራቸው አደገኛ መዘዝ ይዞባቸው እንዳይመጣ ሊጠነቀቁ ይገባል የሚል መልእክት ለማስተላለፍ፣ ምናልባትም ለማስጠንቀቅ የቀረበ የሕጉ አጭር መግለጫ ነው። ለሕግ ሙያተኞች ፈጽሞ ጥቅም የለውም ማለት ባይቻልም ዓይነተኛ ጥቅሙ ግን ከሙያው ዓለም ውጪ ላለው ለተራው ማኅበረሰብ ነው። ጽሑፉ ስለማቀባበል የሙስና ወንጀል ውስን የግንዛቤ ማስጨበጫ ነጥቦችን በመያዝ ተዘጋጅቷል። ሕግን አለማወቅ ከተጠያቂነት አያድንምና ይነበብ።

Continue reading
  2279 Hits

ለተዋጣለት ወንጀል ምርመራ የሚጠቅሙ ቀዳሚ ነገሮች

የተዋጣለት የወንጀል ምርመራ ሥራ ለወንጀል ፍትሕ ሥርዓት መስፈን ቁልፍ የሆነ ሚና እንደሚጫወት በርካታ በወንጀል ምርመራ ሥራ ላይ የታተኮሩ መጽሐፍት የሚገልጹት ጉዳይ መሆኑን እንረዳለን፡፡ በወንጀል ምርመራ ወቀት የተፈጸመ ወንጀልን ለማግኘት እና ጥፋተኛውን ለይቶ ለማውጣት ከሚጠቅሙ ቀዳሚ ነገሮች መካከል የሚከተሉትን መጥቀስ ይቻላል፡፡

Continue reading
  22527 Hits
Tags:

ዳኞች፣ ዐቃቤ ሕጎች፣ ጠበቆች እና ፖሊሶች ሊዘነጓቸው የማይገቡ የወንጀል ሥነ ሥርዓት ሕግ መርህዎች

መንግሥት የሃገርን ሰላምና ደህንነት የመጠበቅ እና የማስጠበቅ እንዲሁም የሕዝቦቹን እና የነዋሪዎቹን መሠረታዊ የግለሰብና የቡድን ነፃነት መብት እና ጥቅም የማክበርና የማረጋገጥ ግንባር ቀደም ኃላፊነትና ሚና አለበት፡፡ ይህንን ኃላፊነቱን ለመወጣት ከሚያከናውናቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት መካከል በግልጽ በሚመራ ሥርዓት የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ማዕቀፍን መዘርጋትና ማቋቋም አንዱና ዋነኛው ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ማዕቀፍን ከሚያቋቁሙ ምሰሶዎች መካከል የወንጀል ሕግ፣ የወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕግ እና የማስረጃ ሕግ በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ፡፡

Continue reading
  24075 Hits

መጥላት ላለብን የጥላቻ ንግግር የተጨማሪ ሕግ አስፈላጊነት

 

ኢትዮጵያውን የሚሳተፉባቸውን የማኅበራዊ ሚዲያዎች ለሚጠቀምና ሌሎች ተጠቃሚዎች የሚጽፏቸውን ወይንም የሚጭኗቸውን ጽሑፎች፣ ምሥሎችና ድምፆች ለሚከታተል ሰው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አንድ ግልጽ የሆነ አዝማሚያ እያደገ መምጣቱን ያስተውላል፡፡ ይኼውም ጥላቻን ያዘሉ ንግግሮች መበራከታቸውን ነው፡፡ የጥላቻ ንግግር እጅግ ብዙ የሆኑ በጎ እሴቶችን የመናጃ መንደርደሪያ ነው፡፡ የጥላቻ ንግግር ጥላቻ ላይ የተመሠረቱ ወንጀሎችን መጥሪያ ነው፡፡ የጥላቻ ንግግር አድልኦና መገለልን ያመጣል፡፡ የጥላቻ ንግግር የአንድን ብሔር አባላት፣ የሃይማኖት ተከታዮች፣ ስደተኞችንና ሌሎች ቡድኖችን እንበለ ምክንያት በጭፍኑ እንዲጠሉ መንገድ ያለሰልሳል፡፡ የከፋው ደግሞ የዘር ማጥፋትን ወይንም ቡድን ጠረጋን ሊያስከትል ይችላል፡፡ በበርካታ አገሮችም ተከስቶ ነበር፡፡

በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አይሁዶችን የጀርመን ናዚዎች ከማጥፋታቸው በፊት በርካታ አይሁዶች በጀርመንና ሌሎች አገሮች በተሻለ የኑሮ ደረጃ ይመሩ ስለነበር እንደ ባለጠጋ ጥገኛ ተሕዋስያን (Wealthy parasite) ተደርገው ተስለዋል፡፡ ጀርመኖች ደግሞ ከሌሎች የላቁ እንደሆኑ ራሳቸውን ቆጥረዋል፡፡ ሁቱዎች በረሮ እንጂ ቱትሲዎች ብሎ መጥራት አቁመው ነበር፡፡ ይህ እንግዲህ ጥላቻው በሕዝብ ደረጃ ከፍ ባለበት ወቅት ነው፡፡ አጠራሩንም አንዱ ቡድን በጅምላ የሌላውን ተቀብሎ አጽድቆታል ማለት ነው፡፡ ይህ ዓይነቱን ፍረጃም ይሁን ስያሜ መነሻው እውነት እንዲሆን አይጠበቅም፡፡ ሕዝቡም ሲጋራው በምክንያታዊነት አስቦና አሰላስሎ አይደለም፡፡ ምክንያታዊነት የግለሰብ ባህርይ እንጂ የሕዝብ አይደለችም፡፡ ቡድንን ጅምላዊነት ያጠቃዋል፡፡ እንደ ግለሰብ ሲታሰብ ወለፈንድና ሐሰት መሆኑን የምንረዳውን ነገር ከቡድናችን ጋር ስንቀላቀል ግን እንተወዋለን፡፡ የጥላቻ ንግግርም ቡድናዊ ቅርጽ ለመያዝ በእጅጉ የተጋለጠ ነው፡፡ ታሪክም ያሳየን ይኼንኑ ነው፡፡

በርካታ አገሮች ከራሳቸውም ገጠመኝም ይሁን ከሌሎች የታሪክ ጠባሳ በመማር የጥላቻ ንግግሮችን የሚከለክሉ ሕግጋት አውጥተዋል፤ ተግባራዊ ለማድረግም ተቋማትን አደራጅተዋል፡፡ የተለያዩ የሲቪክ ማኅበራትም የጥላቻ ንግግር ምንነቱን፣ ይዘቱን፣ መንስዔውን፣ መዘዙንና ሌሎችም ጭብጦች ላይ በመመርኮዝ ጥናት ያጠናሉ፤ የፍትሕ ተቋማትን ያሠለጥናሉ፤ ሕዝብን የማንቃት ሥራ ይፈጽማሉ፡፡ ብሎም ዴሞክራሲያዊ ማኅበረሰብ ለመገንባት አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ፡፡ በዚህ መንገድ ብዙ ማኅበረሰቦች በሠላምና በመቻቻል እንዲኖሩ እያደረጉ ነው፡፡

ይህ ጽሑፍ የጥላቻ ንግግርን ምንነትና ከሌሎች ንግግሮች የሚለይበትን መንገዶች ይገልጻል፡፡ የኢትዮጵያን የሕግ ሁኔታ በመቃኘት የተጨማሪ ሕግ ወይንም ሥርዓት አስፈላጊነቱን በአንድ በኩል ከሕገ መንግሥቱ ጋር ለማጣጣም አስቸጋሪነቱን በሌላ በኩል ያሳያል፡፡ ይህን ለማድረግም ደግሞ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችንና ድንጋጌዎች በመቃኘት እንዲሁም ከሌሎች አገሮች ሕግና አሠራር ጋር በማነፃፀር ያሉትን ክፍተቶች በመጠቆም ምን መደረግ እንዳለበት ጥቆማ ያቀርባል፡፡

Continue reading
  13946 Hits