አካለመጠን ባልደረሱ ወጣት የወንጀል ሕግ ተላላፊዎች ላይ የኢትዮጵያ የሕግ ማዕቀፍ - የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓትና የወንጀል ሕጉን መነሻ በማድረግ

በ1995 የወጣው የኢፌዲሪ ህገ-መንግስት ለተጠረጠሩና ለተከሰሱ ሰዎች በርካታ የሕግ ጥበቃዎችን ያደርጋል። እነዚህ ጥበቃዎች በዋናነት በሕግ ፊት በእኩል የመታየት፣ በሕግ አግባብ የመዳኘት፣ አላግባብ ቤታቸውና አካላቸው ከመበርበር የመጠበቅ፣ ከሕግ አግባብ ውጭ ያለመያዝ፣ በጠበቃ የመወከል፣ ንፁህ ሆኖ የመገመት፣ የፍርድ ሂደታቸው በግልፅ ችሎት ፈጣን በሆነ መልኩ እንዲካሄድ የማድረግ፣ የሚቀርብባቸውን ማስረጃ የመመልከትና መስቀለኛ ጥያቄ የመጠየቅ፣ ኢሰብአዊ ከሆነና ጭካኔ ከተሞላበት ቅጣት የመጠበቅ እና በአንድ ወንጀል ሁለት ጊዜ ያለመቀጣት መብት ናቸው። እነዚህ መብቶች በአብዛኛው እድሜያቸው ከ18 አመት በላይ በሆኑ ወይም ለአካለመጠን በደረሱ ወጣቶች ላይ የሚተገበሩ ሲሆን አካለመጠን ባልደረሱ ሰዎች ላይ ሁኔታው የተለየ ሆኖ ይገኛል። በወንጀል ለተጠረጠሩና ለተከሰሱ አዋቂ ሰዎች በሕግ የተቀመጡ ጥበቃዎች አካለመጠን ላልደረሱ ሰዎች ሲከለከሉ ወይም በዝምታ ሲታለፉ ይስተዋላል።

  7344 Hits

በኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነ ሥርዓት የቀዳሚ ምርመራ ድንጋጌዎችና አተገባበራቸው አጭር ዳሰሳ

የወንጀል ክስን በማስረጃ አስደግፎ በማረጋገጥ እና ተከሳሽን ወደ ፍርድ ቤት በማቅረብ ጥፋተኛ ማስደረግ በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ትልቅ ጥረትና ድካም የሚጠይቅ ተግባር ነው፡፡ አንድ ወንጀል ማህበረሰቡ ላይ ሲፈጸም ወንጀሉን የፈጸመን አካል ነቅሶ በማውጣት ለፍርድ በማቅረብ ማስቀጣት የመንግሥት ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ አንድ መንግሥት የሕዝብን  ሥልጣን  ሲቀበል  የማህበረሰቡን  ሰላም  መጠበቅ ከሕዝቡ የተጣለበት  ግደታው  ነው፡፡ ይህንን ሰላም ለመጠበቅ  ደግሞ  ወንጀል  እንዳይፈፀም ይከላከላል፡፡ ከተፈፀመ በኋላ ፈፃሚውን ለሕግ ያቀርባል፣ ወንጀል ለመፈፀሙ ሊያሥረዱ የሚችሉ ማስረጃወችን አብሮ ያቀርባል፡፡

  26211 Hits

የግል አቤቱታ የማቅረብ መብት በጠቅላላው

የሥነ-ሥርዓት ሕግ ሰዎች መሠረታዊ የሆኑ የፍትሕ አቤቱታዎች ሲቀርቡ የሚመሩበትን እና መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች በሚመለከታቸው የፍትሕ አካላት የሚወስኑበትንና ተፈፃሚ ሊሆኑ የሚችሉበትን ሥርዓት የሚያሳይ ጽንሰ ሀሳብ ነው። የሥነ-ሥርዓት ሕግ መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች በምንና እንዴት ባለ አኳኋን ወደ ተግባር ሊፈፀሙ እንደሚችሉ የሚዘረዝር የሕግ ክፍል ነው። የእነዚህን መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች ይዘትና አይነት ተንትኖ የሚያቀረበው የሕግ ክፍል መሠረታዊ ሕግ (Substantive Law) ተብሎ የሚጠራ ነው። መሠረታዊ ሕግ የሰው ልጆችን መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች በግልፅ የሚደነግግ በመሆኑ ጠቀሚታው ከፍተኛ እንደሆነ ይታመናል። ይሁን እንጅ እንዚህ ዝርዝር መብቶችና ግዴታዎች በተግባር ተፈፃሚ እንዲሆኑ ካልተደረገ የመኖራቸው ጉዳይ ትርጉም የለሽ ይሆናል ማለት ነው። እነዚህ መደበኛና ልዩ መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች እንዲፈፀሙ የማድረጉ ሐላፊነት የሥነ-ሥርዓት ሕግ ቢሆንም ውጤታማ የሥነ-ሥርዓት ሕግ ከሌለ ግን መብቶችንና ግዴታዎችን የማስፈፀሙ ዓላማ እረብ የለሽ ይሆናል። ለዚህም ነው የሥነ-ሥርዓት ሕግ ከመሠረታዊው ሕግ ባላነሰ አስፈላጊና ጠቃሚ ነው የሚባለው።

  20985 Hits

ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ

መግቢያ ፡- ተበዳዮች በወንጀል ፍትሕ ሥርዓቱ የነበራቸው የተሳትፎ ሚና፡ ጥቅል ምልከታ

በኢትዮጵያ የወንጀል ተጎጂዎች በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ያላቸው ሚና ከነበረበት የማማ ደረጃ በጊዜ ሂደት ‹‹ከማማ የመውረድ›› ያህል ዝቅ እያለ መጥቷል። ሀገሪቱ በዳግም የኢጣሊያ ወረራ ተፈፅሞባት ከመያዝዋ እ.እ.አ ከ 1935 ዓ.ም በፊት በወንጀል ጉዳት ደርሶባቸው በቀጥታ ተበዳይ የሆኑ ሰዎች ወይም የተበዳይ ተወካይና ቤተዘመዶች በደል ካደረሰባቸው ሰው ፍትሕን በገዛ እጃቸው ያገኙ ነበር። ተበዳይ ጥቃት ያደረሰበትን ሰው ሲፈልግ ይበቀላል፣ ሲፈልግ በፍርድ አደባባይ ይከሳል ወይም ለደረሰበት በደል ከተበዳይ ከሳ ይቀበላል። አይ ይህን ሁሉ አልፈልግም ካለም ከሁሉም ታቅቦ ፍትሕን ከእግዚአብሔር እየጠየቀ ይኖራል። በዚህ ጊዜ ምርመራ አጣርቶ ክስ የሚመሰርት የዐቃቤ ሕግ ተቋም በሀገሪቱ አልነበረም። በግለሰቦች መሀከል የሚፈጠር አለመግባባቶችን ‹‹የወንጀል›› ጉዳይ እና የግለሰቦች የፍትሐብሔር ጉዳይ ብሎ የሚከፋፍል የሕግ ስርአት ባለመኖሩ ጥቂት በሀይማኖትና በመንግስት ላይ የሚፈፀሙ በአሁኑ ሰአት የፓለቲካ ወንጀል እየተባሉ ከሚጠሩ ወንጀሎች በስተቀር ሁሉም አለመግባባቶች ላይ ግለሰቦች በራሳቸው ከሳሽ በመሆን ጉዳያቸውን ለፍርድ ቤት ያቀርባሉ ወይም ፍትሕን በእጃቸው ያገኙ ነበር። ጉዳያቸውን ወደ ፍርድ ቤት የሚወስዱ ከሆነ ክስ የመመስረት፣ የተጀመረን ክስ የሟቋረጥ፣ ቅጣትን በመምረጥ ተበዳይ ግለሰብ ሁሉን አድራጊ ነበር። የወንጀል ይዘት ያላቸው ጉዳዮችን ከፍትሀብሔር ጉዳዮች ጋር በማጣመር የጉዳት ካሳን መጠየቅም ይቻል ነበር። በዘመኑ የወንጀል ተበዳዮች በወንጀል ጉዳይ የሉአላዊ ስልጣን ባለቤቶች ነበሩ።

  5047 Hits

ዳኞች፣ ዐቃቤ ሕጎች፣ ጠበቆች እና ፖሊሶች ሊዘነጓቸው የማይገቡ የወንጀል ሥነ ሥርዓት ሕግ መርህዎች

መንግሥት የሃገርን ሰላምና ደህንነት የመጠበቅ እና የማስጠበቅ እንዲሁም የሕዝቦቹን እና የነዋሪዎቹን መሠረታዊ የግለሰብና የቡድን ነፃነት መብት እና ጥቅም የማክበርና የማረጋገጥ ግንባር ቀደም ኃላፊነትና ሚና አለበት፡፡ ይህንን ኃላፊነቱን ለመወጣት ከሚያከናውናቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት መካከል በግልጽ በሚመራ ሥርዓት የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ማዕቀፍን መዘርጋትና ማቋቋም አንዱና ዋነኛው ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ማዕቀፍን ከሚያቋቁሙ ምሰሶዎች መካከል የወንጀል ሕግ፣ የወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕግ እና የማስረጃ ሕግ በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ፡፡

  26582 Hits