The blogger graduated from Haramaya University and works at FDRE Ministry of Justice as a public prosecutor and Part Time Law Instructor at Addis Ababa University College of Law.

ወንበዴ ማነው? ውንብድናስ ምንድነው?

የተከበራችሁ አንባቢዎች ለዛሬው ርዕሰ አንቀፅ መነሻ የሆነኝ የውንብድና ወንጀልን የሚያቋቁሙ ፍሬ ነገሮች በአግባቡ ባለመረዳት ወይም በተለያዩ መልኩ በመተርጎም የሚፈፀሙ የክስ አመሰራረት ልዩነቶች ናቸው፡፡ በመሆኑም ያለውን አሰራር እና አንቀፁን እኔ በምረዳው መልኩ በማቅረብ ለአንባቢዎቼ እንደሚከተለው ለውይይት እና አስተያየት ክፍት አድርጊያለሁ፡፡

የቀድሞ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ አንቀፅ 636 ስር ተደንግጎ የነበረ ሲሆን በዚህም አንቀፅ መሰረት ወንበዴነት “የስርቆት ወንጀል ለመስራት አስቦ ወይም በስርቆት ወንጀል ተይዞ ወይም ደግሞ በስርቆት ያገኘውን ነገር ለመሰወር በማሰብ” የሃይል ተግባር ፈፅሞ እንደሆነ ተደንግጎ ይገኝ ነበር፡፡ በመሰረቱ ይህ ድንጋጌ ተሻሽሎ በ1996ቱ የወንጀል ህግ ውስጥ እንዲካተት ተደርጓል፡፡ በአንቀፁ ላይ ማሻሻያ ማድረግ ያስፈለገበት ምክንያት የስርቆት ወንጀል የሚፈፀመው ባለንብረቱ ወይም ሌላ ሰው እንደማያየው ወይም እንደማይዘው በማረጋገጥ ስለሆነ የሰውን ንብረት ከመውሰድ ጋር የሃይል ተግባር ከተጣመረ የንብረት አወሳሰዱ ስርቆት መሆኑ የሚቀር በመሆኑ መሆኑን የወንጀል ህግ ሐተታ ዘምክንያት ያትታል፡፡

በ1996 ዓ.ም በወጣው የወንጀል ህግ መሰረት ውንብድናን ከስርቆት አንፃር መቶረጎሙን በመተው ውንብድና እንደሚከተለው ተደንግጎ ይገኛል፡፡

ማንም ሰው ተገቢ ያልሆነ ብልጽግና ለራሱ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት አስቦ፣ የሌላ ሰው ንብረት የሆነውን ተንቀሳቃሽ ዕቃ ለመውሰድ እንዲያመቸው ወይም በሚወስድበት ጊዜም ሆነ ከወሰደ በኋላ የገጠመውን ተቃውሞ ውጤታማነት ለማስቀረት ሲል በሌላ ሰው ላይ የኃይል ድርጊት ወይም ከባድ የሆነ የማገላታት ተግባር ወይም ከባድ ዛቻ የፈጸመ፣ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ ይህን ሰው ለመከላከል እንዳይችል ያደረገው ሲሆን ከአሥራ አምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራት ይቀጣል፡፡

በመጀመርያ ደረጃ ውንብድና የሚፈፀመው ተገቢ ያለሆነ ብልፅግና ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት መሆን ይኖርበታል፡፡ የማይገባውን ብልፅግና የማግኘት ሃሳብ ተንቀሳቃሽ እቃ ለመውሰድ እንጂ የማይንቀሳቀስ ንብረት በመውሰድ ላይ ተፈፃሚነት አይኖረውም፡፡ ከሃሳቡ ቀጥሎ የሚመጣው ውንብድናን የሚያቋቁመው የወንጀል ፍሬ ነገር የሌላ ሰው ንብረት የሆነውን ተንቀሳቃሽ ዕቃ ለመውሰድ እንዲያመቸው ወይም በሚወስድበት ጊዜም ሆነ ከወሰደ በኋላ የገጠመውን ተቃውሞ ውጤታማነት ለማስቀረት የሃይል ወይም የዛቻ ተግባር መፈፀም ነው፡፡ በአንዳንድ ክሶች ላይ እንደሚታየው ከሆነ ውንብድና ተፈፀመ የሚባለው ንብረት ተወስዶ እንደሆነ ነው፡፡ ነገር ግን በወ/ህ/ቁ. 670 ላይ በግልፅ እንደተደነገገው ተንቀሳቃሽ ዕቃ ለመውሰድ እንዲያመቸው ብሎ ብቻ የሃይል ተግባር መፈፀም በራሱ ወንጀሉን ያቋቁማል፡፡

Continue reading
  9939 Hits
Tags:

Prosecution for Several Counts Resulting from a Single Criminal Act

Abstract

It is inevitable fact today that one criminal act can inflict upon several victims harm of certain nature. In doing so the criminal act though flowing from the same criminal intention or negligence and violating the same criminal provision may cause the same harm against the rights or interests of more than one person. In such instances the law dictates the liability to be equalled with the numbers of victims though the practice shows divergence among courts and also between prosecutors.

 

1.  Introduction

 

Continue reading
  15740 Hits
Tags:

ተከሳሽ በሌለበት የወንጀል ክስ ስለመስማት (Trial in absentia)

1.  ተከሳሽ በሌለበት የወንጀል ክስ ስለመስማት (Trial in absentia) ፅንሰ ሃሳብ

ተከሳሽ በሌለበት የወንጀል ክስ መስማት (Trial in absentia) ማለት ተከሳሹ በወንጀል ክሱ በፍርድ ቤት ጉዳዩ በመታየት ላይ የሚገኝ ቢሆንም ተከሳሹ ግን በአካል በፍርድ ቤት ሳይገኝ ጉዳዩ በሌለበት በመታየት ላይ የሚገኝ ማለት ነው፡፡ ይህ አይነቱ የህግ ስረዓት በተለያዩ ሃገሮች የሚተገበር ሲሆን በእኛም ሃገር በወንጀል ሥነሥርዓት ህጉ እና በመገናኛ ብዙሃን የመረጃ ነፃነት አዋጅ ቁጥር 590/2000 ላይ በልዩ ሁኔታ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ ተከሳሽ በሌለበት የወንጀል ክስ መስማት ተገቢነቱ መታየት ያለበት ከወንጀል ህጉ አላማ፤ ከፍትህ እና ከሰብዓዊ መብት አንፃር ነው፡፡

2.  ተከሳሽ በሌለበት የወንጀል ክስ መስማት ያለው ጠቀሜታ እና ጉዳት

የወንጀል ክስ በሚሰማበት ወቅት የተከሳሽ በፍ/ቤት መገኘት ብዙ አይነት ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡ በፍ/ቤት በመገኘትም ተከሳሽ ሙሉ መብቶቹ እንዲከበሩ እና ማንኛውም አይነት የተከሳሽ መብቶች እንዳይታለፍ ማድረግ ይችላል፡፡ በዚህም ሳያበቃ በወንጀል ፍትህ አስተዳደሩ ላይ እውነታውን ከማውጣጣት አንፃር ፋይዳ አለው፡፡ ተከሳሽ በሌለበት የሚታይ ጉዳይ የአንድ ወገንን ማስረጃ ብቻ የሚመዘንበት በመሆኑ ጥፋተኛ የመባል እድልን የሚያሰፋ በመሆኑ ያለጥፋት የሚቀጡ ሰዎችን ሊያበዛ ይችላል፡፡

በሌላ መልኩ ደግሞ ተከሳሽ በሌለበት የወንጀል ክስ መስማት ተከሳሽን በመጠበቅ ሊጠፋ የሚችለውን ጊዜ በመቀነስ አፋጣኝ የፍትህ ስርዓት እንዲኖር ያደርጋል፡፡ ተከሳሽን በመጠበቅ ሊጠፋ ይችል የነበረውን የማስረጃ መሳሳት ይቀንሳል፡፡

Continue reading
  10598 Hits