Mr. Mulugeta Belay is a consultant and attorney at law. He is best known for his role as a 'Judge' on Chilot television drama

የሕግ የበላይነትን የሚያናጋው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ (የቤት ኪራይ ማእቀብና የሕግ ጥሰቶቹ)
Mulugeta Belay
About the Law Blog
መግቢያ የአዲስ አባባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ቀደም ሲል አውጥቶት የነበረውና የተከራየን ሰው ማስወጣት (በርግጥ ደንቡ ይህን ድርጊት አልከለከለም) እና የኪራይ ዋጋን መጨመር ለማገድ የወጣውን የደንብ ቁጥር 122/13 ማራዘሙን በድጋሜ አስታዉቋል፡፡ ይህ ደንብ የቤት አከራዮች ያከራዬት ቤት ላይ ዋጋ እንዳንይጨምሩ ክልከላ ይጥላል፡፡ በዚህ አጭር ጽሑፍ የደንቡን ህጋዊነት ለሕግ የበላይነት ያለውን መጥፎ ተምስሌትነት በርግጥ ሊፈታ ያሰበውን ችግር ለመፍታት ያለውን ፋይዳ በአጭር ባጭሩ ለመዳሰስ ይሞክራል፡፡ አንባቢያንን ለተራዘመ እና አሰልቺ የንባብ ሂደቶች ላለመዳረግ ጉዳዩን በቀጥታና በጭሩ ለመዳሰስም ተሞክሯል፡፡
Continue reading
ስለቅድመ ሳንሱር
Mulugeta Belay
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
ቅድመ ሳንሱር በማንኛውም ቅርፅ በማንኛውም አካል ክልል ነው። ሰሞኑን ዎልታ ቴሌቪዥን ለማሰራጨት ያዘጋጃቸውን ፕሮግራሞች እንዳያሰራጭ የፍርድ ቤት ትእዛዝ እንደተሰጠ አድምጠናል። የመናገር ነፃነትና የሚዲያ ነፃነት የሕግ እና የአሰራር ገደቦች የትላንት ከትላንት ወዲያ የጭቆና አርእስቶች ነበሩ። ምንም አስብ፣ ምንም አቅድ መናገርና ሀሳብህን በስእል፣ በፅሁፍ፣ በሙዚቃ እና በየትኛውም ራስን የመግለፅ ጥበብ መግለጽ ተፈጥሮአዊ እና ህገመንግስታዊ መብት ነው።
Continue reading
የዜግነት ቅድመ ሁኔታዎች መሟላታቸውን ማረጋገጥ የቅድመ ሁኔታዎቹ ቅድመ ሁኔታ ስለመሆኑ:- ለአቶ ግዛው ለገሰ የተሰጠ ምላሽ
Mulugeta Belay
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
ስለ ዜግነት አዎጁ በፃፍኩት ጽሑፍ ላይ አቶ ግዛዉ ለገሰ የተባሉ የሕግ ባለሙያ የፃፉት ምላሽ ደርሶኝ ተመለከትኩት፡፡ (የአቶ ግዛው ለገሰ ጽሑፍን ለማግኘት ይህንን ይጫኑ፡፡ ) በመጀመሪያ ጸሐፊው የሕግ ባለሙያ እንደመሆናቸውም ብሎም ጽሑፉን ያወጡት እሳቸው ስላልተስማሙበት የሕግ ጽሑፍ ምላሽ ለመስጠት እንደ መሆኑ አቶ ጀዋር መሐመድን ለመደገፍ አልፃፍኩትም ለማለት አቶ ጀዋር የራሱ ጉዳይ ብለው ጽሑፉን መጀመራቸው፤ በጽሑፉ ውስጥ ለተነሱ እያንዳንዱ ክርክሮች ተገቢውን የሕግ ክርክር ከማንሳት ይልቅ በአመዛኙ በተራ የአዋቃለሁ ባይነት ጉራ ተሞልተው እኩይ ሴራ የሚሉ ያልተገቡ ቃላቶች መጠቀማቸው ብሎም በጽሑፉ ውስጥ  ለድምዳሜቸው ማስረጃ አድርገው ስላቀረቡት የሕግ ግምት (presumption of law) ምንነት ያሉት ነገር አለመኖሩ እና ሃሳባቸው ልክ ስለመሆኑ የሚደግፍ የሕግ አስተምሮ ሳይጠቅሱ በደፈናው የሕግ ግምት ያልገባው የሚል የወረደ ምላሽ መስጠታቸው ከሙያ ሥነ-ምግባር የወጣ ተራ ብሽሽቅ የመሰለ መውረድ ሆኖ አግንቼዋለሁ፡፡ በተለይ ደግሞ የመጀመሪየው ጽሑፍ በግልፅ ዜግነትን መልሶ ስለማግኘት ላይ ብቻ አተኮሮ እንደተፃፈ በተገለፀበት ሁኔታ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ስለሌላቸው እንደ በሕግ ዜግነት ስለማግኘት የመሳሰሉ ለምላሹ ፋይዳ በሌላቸው ዝርዝሮች ላይ ማተኮራቸውም አስቀድመው ላልተስማሙበት ጽሑፍ ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት በቂ እድል ነፍጓቸዋል ጊዜያቸው አጥንቱን በመጋጥ ላይ መዋል ሲገባው መረቅ ለመጠጣት ውሏል፡፡
Continue reading
የኢትዮጵያ ዜግነትን መልሶ ስለማግኘት - የኢትዮጵያ ዜግነትን ያለባለሥልጣኑ (ኤጀንሲው) ውሳኔ መልሶ ማግኘት የማይቻል ስለመሆኑ
Mulugeta Belay
About the Law Blog
ሰሞኑን የአቶ ጀዋር መሐመድን ኢትዮጵያዊ ዜግነት መልሶ የማግኘት ጉዳይ በኦፌኮ እና በምርጫ ቦርድ መካከል ክርክሮችን ማስነሳቱን በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየሰማን እንገኛለን፡፡ በመሆኑም የዜግነት ሕጉ ኢትዮጵያዊ ዜግነት መልሶ ስለማግኘት ስላሰቀመጣቸው ቅድመ ሁኔታዎች እና ዜግነት መልሶ ማግኘት ስለሚረጋገጥበት መንገድ ያለኝን መረዳት ለማካፈል ወደድኩኝ፡፡
Continue reading
የማናከብረውን እና የማንተገብረውን ሕግ ማውጣት ከሕግ አልባነት አይሻልም- መረጃ የማግኘት መብት
Mulugeta Belay
About the Law Blog
ሕግ ጭራሽ ካለመከበሩ በከፋ ተመርጦ ሲከበር የበለጠ አልተከበረም፡፡ አሁን ባለን መረጃ ሀገሪቱ ከቻይና ጋር ስለገባነው የብድር ስምምነት የሚያትትውን 1000ኛውን አዋጅ ካወጀች ብኋላ  እንኳ ከመቶ በላይ አዋጆች ወጥተዋል፡፡ ኑሮው፣ ፖለቲካው፣ ኢኮኖሚውና ማህበራዊ ጉዳያችን ብዙ ነው እና ሕጎቹ በዙ አይደለም ጉዳዩ፡፡ ስንቱ በርግጥ ወጥቶ ሥራ ላይ ዋለ ነው ጥያቄው፡፡ የማናከብረውን እና የማንተገብረውን ሕግ ማውጣት ከሕግ አልባነት አይሻልም፡፡ 
Continue reading
በፍርድ ከሄደች በቅሎየ ያለፍርድ የሄደች ጭብጦየ (ለውጥ የሚሹ የፍርድ ቤት ጉዳዮች)
Mulugeta Belay
Property Law Blog
ፍርድ ቤት የበደል ስር የሚቆረጥበት ፤ ተበዳይ የሚካስበት፤ አጥፊ የሚቀጣበትና መንግስት ከህግ በታች መሆኑ የሚረጋገጥበት መድረክ ነው፡፡ ፍርድ ቤት ፍትህ ከረቂቅነት ከፍ ብላ የምትታይ ፣ የምትሰማ እና የምትዳሰስ ህልው መሆኗ የሚታወቅበት አደባባይ ነው፡፡ ፍርድ ቤት የሰለጠነ ህዝብ የኔ የሚለውን ህግ የሚያስከብርበት መሳሪያ ነው፡፡ ህይወቱ ፣ ንብረቱና የኔ የሚላቸው እሴቶቹ ሁሉ ጥበቃ ያላቸው ስለመሆኑ የሚተማመንበት ዋሱ ነው ፍርድ ቤት፡፡
Continue reading
ደብዳቤው
Mulugeta Belay
About the Law Blog
ያው ጉባኤው የሚለውን ርእስ መኮረጄ ነው እየመረጥክ ከዘገብክ የገለልተኝነት እና የእኩልነትን መርህ ጥሰሃል፡፡ /በበውቀቱ እስታይል/ ተከታዮ የመጀመሪያ አንቀፅ ለአገላለፅ ውበት እንጅ በጉዳዩ ላይ ያለኝ መቆጨት እንዳገላለፁ አለመሆኑ ይታወቅልኝ፡፡
Continue reading
የቴዲ አፍሮ አልበም ምርቃት ክልከላ እና የመሰብሰብ መብት
Mulugeta Belay
Constitutional Law Blog
የዚህ ጽሑፍ መነሻ የቴዲ አፍሮ የአልበም ምረቃ መከልከል ሲሆን ጽሑፉ ይህን መነሻ በማድረግ በኢትዮጵያ ሕግ መሠረት በማንኛውም ምክንያት መሰብሰብ አድማሱ እስከምን ነው? የሚለውን መሠረታዊ ነጥብ የሚዳስስ ሲሆን የአልበም ምርቃቱን መከልከል ምክንያቶች በተመለከተ ግን ጸሐፊው በሁለቱም ወገኖች በኩል ያለውን እውነት በማስረጃ ባለማረጋገጡ አቋም ከመያዝ ተቆጥቧል፡፡ ይሁን እንጂ አጋጣሚው በአስፈፃሚውም ይሁን በስብሰባ አዝጋጆቹ ብሎም በማህበረስቡ ላይ ያለውን መደናገር የመሰብሰብ መብትን አድማስ ለማብራራት ምቹ በመሆኑ ጸሐፊው በርግጥ ለቴዲ አፍሮ የአልበም ምረቃ ፈቃድ ያስፈልግ ነበር? ፈቃድ ካስፈለገውስ መከልከል ይቻል ነበር? የመከልከል ተግባሩ የሚጥሳቸው መሠረታዊ ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌዎችና መብቶችስ ምንምን ናቸው? ለሚሉ መሠረታዊ ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት ይሞክራል፡፡
Continue reading
የዘገየ ፍርድ
Mulugeta Belay
Criminal Law Blog
እኔ አንቺን ስጠብቅ ጠበኩሽ እኔማ……. እዚያው ሰፈር ቆሜ በአክሱም ቁመና በላሊበላ ዕድሜ እግሮቼን ተክዬ ቀኔን አስረዝሜ ትመጫለሽ ብዬ በቆምኩበት ስፍራ ስንት ነገር መጣ ስንት ነገር ሄደ ስንት ጊዜ ነጋ ስንቴ ጎህ ቀደደ በቀጠርሽኝ ስፍራ ስጠብቅሽ ቆሜ ስንት ሳቅ አለፈ ስንትና ስንት እንባ ስንቴ ክረምት ሆነ ስንቴ ጸደይ ጠባ……..                     ታገል ሰይፉ
Continue reading
DNA አባትነትን ማረጋገጫ ማስረጃ ስላለመሆኑ
Mulugeta Belay
Family Law Blog
ሁሉም ሰው ባዮሎጂካዊ አባት አለው ሁሉም ሰው ግን ህጋዊ አባት ላይኖረው ይችላል፡፡ ይህ አረፍተ ነገር በብዙዎቻችሁ ጭንቅላት እንዴ! የሚል ግርምት እንደሚያጭር እገምታለሁ፡፡ በተለይ ሁሉም ልጅ እኩል ነው ልጆች አባትና እናታቸውን የማወቅ ሕገ መንግሥታዊ መብት አላችሁ የሚለው አነጋገር አብዝቶ ከመሰማቱ የተነሳ በሕግ አባት የሌለው ልጅ ሊኖር ይችላል ብሎ መገመት ሩቅ ሊሆን ይችላል በቀጣዩ ጽሑፍ በመግቢዬ የገለፅኩት ሀሳብ ምን ያህል እውነት እንደሆነ ለማሳየት እታትራለሁ፡፡
Continue reading