ፍትሕ እና ጤና

በሀገራችን የፍትሕ ሥርዓት ውስጥ ራሳቸውን በተለየ መልኩ የፍትሕ አካላት በማለት በየዓመቱ ሚያዝያ/ግንቦት ወር የፍትሕ ሣምንት የሚያከብሩ የፖሊስ፣ የማረሚያ ቤቶች አስተዳደር፣ ዐቃቤ ሕግ እና ፍ/ቤቶችን እንመለከታለን፡፡ በየዓመቱም በአዲስ አበባ ከተማችን በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ቅጥር ገቢ ድንኳን እየተተከለ ሥራዎቻቸውን በፎቶ ግራፎች፣ በጽሑፎችና በውይይት በተደገፈ ለሕዝብ በተለይም ለፍ/ቤቱ ባለጉዳዮች ያስጎበኛሉ፡፡ ነገር ግን ፍትሕ ተቋሞቻችን በመሠረታዊነት ከሚመዘኑበት የሥራዎቻቸው ቅልጥፍና፣ ውጤታማነትና ተገማችነት ባሻገር በአካል ለሚመለከታቸው ህንፃዎቻቸው፣ ግቢያቸው፣ የችሎት አዳራሾቻቸው/ክፍሎቻቸው፣ ቢሮዎቻቸው፣ መጸዳጃ ቤቶቻቸው ቢጎበኙ በተለይም ለጤና ተስማሚነታቸው ምን ይመስላሉ? የሚለው ጉዳይ ለዚህ ጽሁፍ ዐብይ መነሻ ምክንያት ነው፡፡

  572 Hits