ስለጽሑፉ ላለወት ማንኛውም አስተያየት በዚህ የኢሜይል አድራሻ ቢልኩልኝ ይደርሰኛል bekaluferede0@gmail.com

በፍትሐብሔር ክርክር ቅድመ-ሙግት ሂደት ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች

የዚህ ጽሑፍ ዋና ትኩረት  ከሙግት በፊት ያሉ ሥነ-ሥርዓታዊ ሂደቶች አንድን ክርክር ላይ ያላቸዉን  ሚና ማጉላት እና ፋይዳቸዉን ማሳየት ነዉ፡፡ በፍትሐ ብሔር ክርክር ሂደት ቅደመ ሙግት የሚባለዉ ለክርክሩ መሪ ጭብጥ ተይዞ ግራ ቀኙ ማስረጃ ማሰማት ከመጀመራቸዉ በፊት ያለዉ ሂደት ነዉ፡፡ በፍትሐ ብሔር ክርክር ዋናዉ ሙግት የሚጀምረዉ ጭብጥ ተይዞ በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 257 እና ተከታይ ድንጋጌዎቹ ተከራካሪዎች ማስረጃዎቻቸዉ የሚያስረዷቸዉን ጭብጥ እያስመዘገቡ ማስረጃ ማሰማት ሲጀምሩ ነዉ፡፡ ከዋናዉ ሙግት በፊት ባለዉ  የቅድመ ሙግት ሂደት በዋናነት ክስና ማስረጃ ማቅረብ፣ መጥሪያ ማድረስ፣ መልስ እና ማስረጃ መቅረብ፣ ክስ መሰማት እና የክስ መቃወሚያዉ ላይ የመወሰን ተግባሮች ይፈፀማሉ፡፡ ይህ የክርክር ሂደት ክርክሩን ለመምራት ዋና መሰረት የሆነዉ ነዉ፡፡ የክርክሩ አቅጣጫ የሚወሰነዉም በዚህ የክርክር ደረጃ ላይ  በሚሰሩ ስራዎች ነዉ፡፡ ክርክሩን ግልፅ እና አጭር በሆነ ሂደት ለመፈፀም የሚያስችለዉም የቅድመ ሙግት ሂደቱ ጤናማ መሆን ከቻለ ነዉ፡፡

Continue reading
  5797 Hits

በሕግ አምላክ!

 

አገሬው ስለ ሕግ ሃያልነት ሲናገር "በሕግ አምላክ ሲባል እንኳን ሰው ወራጅ ውሃ ይቆማል" ይል ነበር፡፡ ሕግ ተፈጥሮንም እስከማቆም ሃይል እንዳለው አድርጎ ለመግለፅ ምን ዓይነት በሕግ የፀና እምነት ቢኖር ነበር ያስብላል፡፡ በሕግና ፍትሕ ላይ እምነት ያለው ሕዝብ ያለማንም አስገዳጅነት ለሕግ ተገዢ ነው፡፡ ክስተቶችንም ተከትሎ ለሕግ ያለውንም እምነት በተለያዬ መንገድ ይገልፃል፡፡ ግጭቶችን በጉልበት ከመፍታት በሕግ መፍታት ተመራጭ እንደሆነም ያምናል፡፡ በጉልበቱ አዳሪ ሲገጥመው ሰይፍን በሰይፍ ከመመለስ በሕግ አምላክ ቢል ይመርጣል፡፡ ከማትረባ ጉልበት በሕግ አምላክ ይሻላል የሚለውም ለዚህ ይመስላል፡፡ ስለዚህ የሕግ መከበር ሕበረተሰቡ ስለሕግና ፍትሕ ባለው አመለካከት ይወሰናል ማለት ነው፡፡ ሕግ በሕበረተሰቡ ውስጥ በሚፈለገው ደረጃ ለውጥ እንዲያመጣ ከተፈለገ እያንዳንዱ ሰው ስለሕግ ያለው አመለካከት አብሮ መመለወጥና ማደግ ይኖርበታል፡፡ ሕበረተሰቡ ለሕግና ፍትሕ ያለው አመለካከት ሁለት ነገሮችን ይገልፅልናል፡፡ በአንድ  በኩል ሕብረተሰቡ ስለሕግ ያለውን እምነት ሲገልፅልን በሌላ በኩል ደግሞ የሕግ መከበር ያለበትን ደረጃ ያሳየናል፡፡

ዘመናዊ የፍትሕ ሥርዓት ሳይዋቀር በፊት አገሬው ስለሕግ የበላይነት የፀና እምነት ነበረው ማለት እንችላለን፡፡ አስገዳጅ ነገር ሳይኖር በአገር ደንብ ብቻ መንገድ ላይ ባላጋራውን ሲያገኘው በሕግ አምላክ ብሎ ተላላፊው መንገደኛ ጉዳዩን እንዲመለከትለት ያደርግ ነበር፡፡ ተላላፊው መንገደኛም ዳኝነቱን ተቀብሎ የግራ ቀኙን ጉዳይ ሰምቶ ይፈርዳል፡፡ ውሳኔው ከተስማማቸው ይፈጽማሉ ካልተስማቸው በአካባቢው ወዳለው ጭቃ ሹም ተያይዞ መሄድ ነው፡፡ ይህን ተላላፊ መንገደኛ ዳኛ የሕግ ሙሁር አበራ ጀንበሬ የመንገድ ዳሩ ፍርድ ቤት(የመንገድ ዳር ዳኛ) በማለት ሲገልፁት ከሳቴ ብርሃን የአማርኛ መዝገበ ቃላት ደግሞ "ዳኛ የውሃ ወራጅ ዳኛ" በማለት ይገልፀዋል፡፡ ስያሜው ምንም ይሁን ተላላፊውን መንገደኛ ዳኛ፣ ባላጋራዎችን ተከራካሪ አድርጎ ሲያቆማቸው የነበረው ያገር ደንብና ልማድ፣ፈቃደኝነትና ለሕግና ፍትሕ የፀና እምነት መኖር  እንጅ ሌላ አስገዳጅ ሃይል አልነበረም፡፡

ሕዝብ ስለሕግና ፍትሕ ባለው የፀና እምነት ብቻ አገር ይዳኝ እንደነበር ሌላ ምሳሌ እንመልከት፡፡ በአዶልፍ ፓርለሳክ ተፅፎ ተጫኔ ጆብሬ መኮንን በተረጎመው የሃበሻ ጀብዱ መፃፍ የተገለፀ ነገር ነው፤ ታሪኩ 1928 ዓ.ም  አካባቢ አዲስ አበባ ገበያ ላይ የተመለከተው ነበር፡፡ ለአንባቢ እንዲመችና የነገሩን ሥር እንዳልስተው ቢረዝምም ተርጓሚው እንደፃፈው ሙሉ ታሪኩን ላስቀምጠው፡-

"በጨርቅ ተራ ሁለት ገበያተኞች ይጨቃጨቃሉ፤ጨርቁን የሚገዛው ሰውየ እጅግ በጣም ረጅም ሲሆን ሻጩ ደግሞ በጣም አጭር ነው፡፡ እናም ገዥ በሚችለው መልኩ ክንዱን ዘርግቶ፣ጣቶችን ወጥሮ አስር ክንድ ለካና ምልክት አደረገ፡፡ ሻጩ ደግሞ በሚችለው ሁሉ ጣቶችን ወጥሮ አስር ክንድ ለካና እሱም ምልክት አደረገ፡፡ ሁለቱ በለኩት መካከል ከአንድ ክንድ የሚበልጥ ልዩነት መጣ፡፡ ገዥው ሻጩን አውቆ ክንዱን ሳይወጥር ይለካል ሲል አመረረ፡፡ ሻጩ በምኒልክ እየማለ ሃቀኛ ነጋዴ መሆኑን እግዚአብሔርን ምስክርነት ጠራ፡፡ በዚህ መሀል ብዙ ወሬኛ ገበያተኞች ከበቧቸው፡፡ በነዚህ ወረኞች ፊት ሁለቱም ደጋግመው ቢለኩም ልዩነቱ ተመሳሳይ ነበር፡፡ እናም መግባባት ባለመቻላቸው ያላቸው ብቸኛ አማራጭ ዳኛ ፍለጋ መሄድ ነበርና ሸማቸውን አያይዘውና አቆላልፈው፣ ጎን ለጎን ግራና ቀኝ እጃቸውን በነጠላቸው ጫፎች ሸብ አድርገው አስረው ከቋጠሩ በኋላ ወደ ገበያው ሽምጋይ ዳኛ በብዙ ወረኞች ታጅበው ሄዱ፡፡

Continue reading
  7452 Hits
Tags:

የተሻሻለው የአማራ ክልል የገጠር መሬት አዋጅ እና አከራካሪው የይርጋ ድንጋጌ

የአማራ ክልል የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 133/98 የተካው የተሻሻለው የገጠር መሬት አዋጅ ቁጥር 252/2009 ቀደም ሲል በሕግ ደረጃ ሽፋን ያላገኙ አዲስ ነገሮችን ይዞ እንደወጣ ይታወቃል፡፡ አዲስ ከሚባሉ ነገሮች አንዱ በገጠር መሬት ላይ በሚነሱ ክርክሮች ላይ የይርጋ መቃወሚያ ተፈፃሚ ሊሆን እንደማይችል ያስቀመጠው ነገር ነው፡፡ ይህ የይርጋ ድንጋጌ በሕጉ የተካተተ አዲስ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ገና ከጅምሩ አከራካሪ ጉዳይ እየሆነ መጥቷል፡፡ አከራካሪነቱም በባለሙያዎች መካከል ሁለት ጫፍ የያዙ አቋም እንዲኖር ከማድረግ አልፎ አዲስ የክርክር ምክንያትም እየሆነ ነው፡፡ አዋጁ ስራ ላይ ከዋለ ጀምሮም የገጠር መሬትን ተከትሎ የሚቀርቡ ክሶች ላይ የይርጋ መቃወሚያ ተፈፃሚነት የለውም በሚል  ብዙ ዶሴዎች ከተዳፈኑበት አቧራቸውን እያራገፉ በክስ መልክ  እየቀረቡ ነው፡፡ ፍርድ ቤቶችም በባለሙያዎች መካከል በይርጋው ተፈፃሚነት ላይ  ባለ ሁለት ጫፍ የያዘ አቋም ምክንያት ከወዲሁ ተገማችነታቸውና ወጥነታቸው አደጋ ላይ እየወደቀ ነው፡፡ ስለዚህም በጉዳዩ ዙሪያ  የሚነሱ አቋሞችን እና ምክንያቶችን በማየት ሃሳቡን መመልከቱ አስፈላጊ እና ትኩረት የሚያስፈልገው ነው፡፡ የፁሁፉ ዋና ትኩረትም በተሻሻለው የገጠር መሬት አዋጅ ላይ የተቀመጠጠው የይርጋ ድንጋጌ ወሰን አለው ወይስ የለውም የሚል ይሆናል፡፡

በቅድሚያ የተሻሻለው የገጠር መሬት አዋጅ ቁጥር 252/2009 አንቀፅ 55 ስለይርጋ ያስቀመጠውን የድንጋጌውን ሙሉ ይዘት መመልከት ተገቢ ነው፡፡

አንቀፅ 55 ስለይርጋ

የገጠር መሬትን በወረራ ወይም በሌላ በማናቸውም ህገ ወጥ መንገድ ይዞ በመገልገል ላይ የሚገኝ ማንኛውም ሰው መሬቱን እንዲለቅ በማንኛውም ሌላ ሰው ወይም ሥልጣን ባለው የመንግሥት አስተዳደር አካል ሲጠየቅ ወይም በመደበኛ ፍርድ ቤት ሲከሰስ የይርጋ ጊዜ ገደብን በሥነ ስርዓት መቃወሚያነት ሊያነሳ አይችልም፡፡

የድንጋጌው ይዘት በተጠቀሰው መልኩ የቀረበ ሲሆን አንደኛው አቋም ይህ የይርጋ ድንጋጌ  በማንኛውም ከገጠር መሬት ላይ የሚነሳ ክርክርን የይርጋ መቃወሚያ እንዳይቀርበበት እና ይርጋን መቃወሚያ ማድረግ እንደማይቻል ተደርጎ እንደተደነገገ የሚገልፅ ነው፡፡ እንደዚህ አቋም አራማጆች ሕጉ በግልፅ የገጠር መሬትን በወረራ ወይም በማናቸውም ሕገ ወጥ መንገድ የያዘ ሰው የይርጋ መቃወሚያ ሊያነሳ እንደማይችል ስለሚናገር በመሬት ክርክር ይርጋ ተፈፃሚ ሊሆን አይገባም በማለት ይገልፃሉ፡፡  በድንጋጌው “በማናቸውም ሕገ ወጥ መንገድ መያዝ” የሚለው ሃረግ  የሚያመለክተው የገጠር መሬት ሊያዝ ከሚችልባቸው መንገዶች ማለትም (በድልድል፣ በስጦታ፣ በውርስ፣ በኪራይ) ውጪ የገጠር መሬትን ይዞ መገኘት እንደሆነ ተደርጎ የተቀመጠ ነው፡፡ በተሻሻለው አዋጅ አንቀፅ 2(39) በተቀመጠው የትርጓሜ ክፍል “ህገ ወጥ ይዞታ” ማለት ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ የተያዘና አግባብ ባለው አካል እውቅና ያልተሰጠው ማናቸውም የገጠር መሬት ይዞታ ስለመሆኑ ይናገራል፡፡  ይሕ የትርጓሜ ክፍል በሕጉ መሬት ከሚገኝባቸው መንገዶች ወይም ሥርዓት ውጪ የሚያዙና አግባብ ባለው አካል እውቅና ያልተሰጠው የገጠር መሬት እንደ ሕገ ወጥ ይዞታ የሚቆጠር ስለሆነ የይርጋው ድንጋጌም ሕገ ወጥ ይዞታ ከሚለው ትርጉም ጋር ተናዝቦ ሊታይ የሚገባ ነው፡፡ በይርጋ ድንጋጌውም የተቀመጠው በማናቸውም መንገድ በሕገ ወጥ መንገድ መያዝ የሚለው በሕግ ከተቀመጠው መሬት ከሚያዝበት ውጪ መያዝ ስለሆነ ከሕግ ውጪ የገጠር መሬትን ይዞ ይርጋን መከራከሪያ ማድረግ አይቻልም፡፡ በማናቸውም ሕገ ወጥ መንገድ የሚለውም ሁሉንም ከሕግ ውጪ የሚያዙበትን መንገዶች ክፍተት እንዳኖራቸው ዝግ አድርጎ ያስቀመጠ ስለሆነ የይርጋ መቃወሚያ ተቀባይነት ሊኖረው አይገባም፡፡ በተጨማሪም የመሬት ክርክር ይርጋ ሊያግደው እንደማይገባ የፌደሬሽን ምክር ቤት ሳይቀር ውሳኔ የሰጠ ስለሆነ በመሬት ክርክር በሁሉም ጉዳዮች ይርጋ ተፈፃሚነት ሊኖረው አይገባም በማለት መከራከሪያቸውን ያቀርባሉ፡፡

Continue reading
  40256 Hits

ዳኛ  እግዜር! ዳኛ ከችሎት ይነሳ!

 

 

ሀገሬው የዳኝነትን ሥራ (ፍትሕ መስጠት) ሃሳባዊ በማድረግ ደረጃውን ከፍ ሲያደርገውዳኛ እግዜር!” ይላል፡፡ ከሳቴ ብርሃን የአማርኛ መዝገበ ቃላትም ዳኛ ማሪያም! ተሙዋጋች በዳኛ ፊት ቆሞ ሲአመለክት ዳኛ እግዚአብሔር! ያሳይህ ዳኛ ማርያም ወይም ሲሙአገት ጭብጥ የያዘውን አስመስካሪውን ዳኛ የምስክሮቹን ቃል ለማሳሰብ ተዘከረኝ ዳኛ ማሪያም ይላል በማለት ይገልፀዋል፡፡ እንደ ፕልቶ ያሉ ሃሳባውያን (idealist) ፈላስፎችፍትሕሃሳባዊ ተፈጥሮ ያለው፣ ከሰብዓዊ ባህርይ ውጪ የሆነ እና አሁን ባለው ዓለም (physical world) ሳይሆን በጊዜ እና በቦታ ባልተገደበው ሃሳባዊ ዓለም የሚገኝ እንደመሆኑ ስሙ ብቻ የሚታየውን ሃሳብ ቅርፅ ወዳለው ድርጊት በሕግ መልክ ሆነ በሌላ ዘዴ ወደ ዚህኛው ዓለም ሊመልሱት እና ሊፈፅሙት የሚችሉት እውነተኛው ሃሳብ የሚታያቸው ሰዎች ናቸው ይላል፡፡ እንግዲህ ሀገሬውዳኛ እግዜርሲል በፍትሕ ላይ ሃሳባዊ መሆኑ ነው፡፡ፍትሕ ከፈጣሪ  ነውብሎ ለሚያምን ማህበረሰብ ሰው በፈራጅነት ቦታ ቁጭ ብሎ ሲያገኘው  በአገረኛ ዘዬ ኧረ! ዳኛ እግዜር! ቢል አይገርምም፡፡ ሌላው ሀገሬው በፍትሕ ላይ ሃሳባዊ ለመሆኑ መገለጫ የሚሆነው ለዳኛ ሲሰጠው የነበረው ልዩ ቦታ ነው፡፡ የአንድ ማህበረሰብ ወግ እና ሥርዓት የሚቀዳው ካለው አካባቢያዊ የእምነት እና አስተሳሰብ መሠረት አድርጎ ነው፡፡ ለማሳያ ያህል  ከፍትሐ ነገስቱ አንድ ነገር አንጠልጥለን እንውጣ፡፡

ፍትሐ ነገስቱ አንቀጽ 43 ዳኛ የፍርድን ልዩነት የሚያውቅ፣ አዕምሮው ያማረለት፣ ከድንቁርና የራቀ በአዕምሮውም መራቀቅ የጭንቅና የተሰወረውን ወደ ፍርድ ፍፃሜ መግለፅ የሚደርስ ይሁን፤ ነፃነት ያለው ይሁን፤ ራሱን ለማስተዳደር ሥልጣን ያለው ያልሆነ ሰው ሌሎችን ሊያስተዳድር አይቻለውምና፤ ዳኞች በፍርድ ጊዜ የማያደሉ ፊት አይተው መማለጃ (ጉቦ) የማይቀበሉ ይሁኑ፤ መማለጃ (ጉቦ) እውነትን እንዳያዩ የብልሆችን ዓይን ያሳውራልና፤ የቀናውንም ፍርድ ይለውጣልና በማለት ይገልፀዋል፡፡  

ፍትሐ ነገስቱ ከአፄ ዘርዐያቆብ ንግስና ዘመን 1444 . ጀምሮ የኢትዮጵያ ሁለተኛው ሕገ መንግሥት ተረቆ በአዋጅ ሥራ ላይ እስከዋለበት 1948 . ድረስ  ለብዙ ዘመናት በሥራ ላይ የዋለ እንደመሆኑ ማህበረሰባዊ ቅቡልነቱ አጠያያቂ አይደለም፡፡ ህዝቡ ለዳኛ የሚሰጠው ስብዕናም ከፍትሐ ነገስቱ የተቀዳ እና ከትውልድ ትውልድ በቅብብሎሽ መልኩ የመጣ ነው፡፡ በአብዛኛው የማህበረሰብ ክፍል ለዳኛ ስብዕና  ያለው ግልፅ መረዳት (pereception) የሚመነጨው ፍትሕን ወደ ተግባር ሊያወርዱት የሚችሉት የተለየ ሥነ-ምግባር እና ያማረ ረቂቅ የሆነ አእምሮ ያለቸው ስዎች መሆን አለባቸው ከሚለው እሳቤ ነው፡፡ ሀገሬው ዳኞች ከመረመሩ ይናገራል ምድሩ፤ ይገኛል ነገሩ በማለት ያዳንቅ የነበር እና ዳኛው የረገጠውን ዲካ (ዱካ) እኔም ረገጥኩት በማለት ሀሴት ያደርግ የነበረው ለዳኝነት ሙያ  በነበረው ልዩ ምልከታ  እንጅ ዳኛ የተለዬ ፍጡር ስለነበር አልነበረም፡፡

Continue reading
  9633 Hits

በጣልቃ ገብ እና የተያዘ ወይም የተከበረ ንብረት ይለቀቅኝ  አቤቱታ ላይ የዳኝነት ይከፈላል?

 

ለዚህ ጽሑፍ  መነሻ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 41 አንድ ሰው በተጀመረ ክርክር መብቴ ይነካል፤ ወደ ክርክሩ ጣልቃ ገብቼ ልከራከር ብሎ ሲጠይቅ እና በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 418 ለፍርድ ማስፈፀሚያ የተያዘ ወይም የተከበረ ንብረት ይለቀቅልኝ በማለት አቤቱታ ሲያቀርብ የዳኝነት ይከፈላል ወይስ አይከፈልም የሚለው ጉዳይ ነው፡፡

የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ መሠረት አድረገው የሚደረጉ ክርክሮች ቅድሚያ የዳኝነት ሊከፈልባቸው እንደሚገባ በቁጥር 215 ተቀምጧል፡፡ ለዚህ ጽሑፍ በማዕከልነት የቀረበው በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 41 መሠረት ጣልቃ ሲገባ እና በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 418 መሠረት ለአፈፃፀም የተያዘ ወይም የተከበረ ንብረት ይለቀቅልኝ በማለት አቤቱታ ሲቀርብ የዳኝነት ይከፈላል ወይስ አይከፈልም የሚለው ጉዳይ ነው፡፡ ጉዳዩን በተመለከተ በባለሙያዎች ሁለት ዓይነት አቋምና አሠራር ሲንፀባረቅ ይታያል፡፡ የሁለቱን  አቋምና አሠራር ከነምክንያታቸው መመልከቱ ልዩነቱን በማጥበብ ወደ አንድ የተቀራረበ አሠራር ሊያመጣ ስለሚችል ለያይቶ መመልከቱ ተመራጭ ነው፡፡

የመጀመሪያው አቋምና አሠራር በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 41 እና 418 መሠረት አቤታቸውን የሚያቀርቡ ወገኖች የዳኝነት ሊከፍሉ አይገባም የሚለው ነው፡፡ የአቋሙ አራማጆች መከራከሪያቸው በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 41 አንድ ሰው ቀድሞ በተጀመረው ክርክር መብቴ ወይም ጥቅሜ ይነካል በማለት አቤቱታውን የሚያቀርበው የቀደሙት ተከራካሪ ወገኖች የዳኝነት በከፈሉት ጉዳይ ላይ ነው፡፡ ጉዳዩ ዳኝነት የተከፈለበት ሆኖ እያለ በድጋሚ ጣልቃ የሚገባውን ሰው ዳኝነት ክፈል ማለት ያላግባብ ለአገልግሎቱ ሁለት ጊዜ ማስከፈል ነው፡፡ በተጨማሪም ጣልቃ የሚገባው ያለፍላጎቱ በተጀመረው ክርክር ጥቅሙና መብቱ ሊነካበት ስለሚችል በመገደድ ስለሆነ ተገዶ በገባበት ክርክር የዳኝነት ክፍል ማለቱ የሥነ ሥርዓት ሕጉ ዓላማ ባለመሆኑ የዳኝነት ሊከፍል አይገባም፡፡ አቤቱታውን ብቻ በማቅረብ ወደ ክርክሩ በመግባት መብትና ጠቅሙን ማስከበር አለበት በማለት ምክንያታቸውን ያስቀምጣሉ፡፡

በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 418 የሚቀርቡ አቤቱታዎች የዳኝነት ሊከፈልባቸው አይገባም በማለት መከራከሪያቸውን የሚያቀርቡት አቤቱታውን ተከትሎ ሊሰጥ የሚችለውን ውሳኔ ይዘት በመመልከት ነው፡፡ የሚጠየቀው ዳኝነት ለአፈፃፀም የተያዘ ወይም የተከበረ ንብረት ይለቀቅልኝ የሚል በመሆኑ የሚሰጠው ውሳኔ ሊለቀቅ ይገባል ወይም አይገባም የሚል እንጅ መብት የሚሰጥ ውሳኔ ባለመሆኑ ዳኝትነት መከፈል የለበትም፡፡ ፍርድ ቤቱ አቤቱታው ሲቀርብለት ለአፈፃፀም ምክንያት የሆነውን ውሳኔ በሚሽር መልኩ ውሳኔ መስጠት አይችልም፡፡ ውሳኔው ንብረቱ ለአፈፃፀም ይውላል ወይስ አይውልም፤ ሊለቀቅ ይገባል ወይስ አይገባም የሚለው ላይ ስለሆነ መብት በማይሰጥ ውሳኔ ላይ ዳኝነት ማስከፈሉ ተገቢ አይደለም በማለት ይከራከራሉ፡፡

Continue reading
  10694 Hits

በገጠር መሬት የመጠቀም መብትን በዋስትና ማስያዝና አርሶ አደሩ

 

መሬት ካለው ተፈጥሮዋዊ ባሕርይም ሆነ ግዙፍነት የተነሳ በሃገራችን ፖለቲካል ኢኮኖሚ ማዕከል ሆኖ እስካሁን ዘልቋል፡፡ በተለይም አብዛኛው ሕዝብ በእርሻ  የሚተዳደር ባለበት ሃገር የመሬት ጉዳይ የኢኮኖሚያዊ መሣሪያ ብቻ ሳይሆን ፖለቲካዊ የሆነ ጠቀሜታ አለው፡፡ የሃገሪቱን የመሬት ስሪት (land tenure) ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንመለከተው በእያንዳንዱርዓት የተለየ ባሕርይ ይዞ እናገኘዋለን፡፡

1966 . በፊት የነበረው የመሬት ስሪት የራሱ ሆነ ባሕርይ የነበረው ሲሆንየርስት ጉልትግንኙነትን ያማከለ ነበር፡፡ መሬት በአብዘኛው የቤተ ክርስቲያን ይዞታ፣ የርስት ጉልት ይዞታ በሚል የተከፋፈለ ነው፡፡ ይህ የመሬት ስሪት በሃገሪቱ አብዛኛውን ክፍል በሚሸፍነው እና መተዳደሪያ መሬት ያለውን አርሶ አደሩን የሚያገል፣ የባለቤትነትም ሆነ የመጠቀም መብትን ዋስትና በማይሰጥ መልኩ የተዋቀረ እንደመሆኑ መሬት በጥቂቶች እጅ እንዲሆን ያደረገ ነበር፡፡

1966 . ተከትሎ የመጣው ለውጥ ቀደም ሲል የነበረውን የርስት ጉልት ግንኙነት በመሻር በመሬት ላይ አዲስ መዕራፍ ከፍቷል፡፡ በጊዜው ወደ ሥልጣን የመጣው የደርግ ሥርዓት ይከተል በነበረውን የሶሻሊስት ርዮተ ዓለም በመመራት ኢኮኖሚውን የሚመሩትን ዋና ዋና ነገሮች ከግል ባለቤትነት ወደ ሕዝብ ባለቤትነት ሲያሸጋግር መሬትም የገጠር መሬትን የሕዝብ ኃብት ለማድረግ በሚል አዋጅ ቁጥር 31/67 የሕዝብ ኃብት በሚል ታወጀ፡፡ አዋጁም መሬት አይሸጥም አይለወጥም የሚለውን ጥብቅ የሆነና የመሬት ጉዳይን ከሌሎች ንብረቶች የሚለየውን ገደብ ይዞ ብቅ ብሎ ነበር፡፡ 

ምንም እንኳን እንደ አዲስ የተደረገው የመሬት ስሪት ለውጥ ከገባር ሥርዓት አውጥቶ ወደ ሕዝብ ያሸጋገረ ክስተት ቢሆንም መሬት ተጠቃሚውን መብት ያጣበበ ነበር፡፡ የገጠር መሬትን የሕዝብ ለማድረግ በወጣው አዋጅ ቁጥር 31/67 አንቀጽ 5 አንድ የመሬት ተጠቃሚ  በይዞታ የያዘውን መብት መሸጥ፣ መለወጥ፣ በስጦታ ማስተላለፍ፣ በማስያዝ፣ በወልድ አገድ ወይም በሌላ ሁኔታ ማስተላለፍ እንደማይችል ገደብ ያስቀምጣል፡፡

Continue reading
  27288 Hits