ደረሰኝ አለመቁረጥ እና የወንጀል ተጠያቂነት

(‘ደረሰኝ የማይሰጥ ከሆነ አይክፈሉ')

ደረሰኝ  ምን ማለት ነው?

የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 አንቀጽ 19፣120 እና 131(1)(ለ) እንዲሁም የፌደራል የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 979/2008 አንቀጽ 82 ላይ የተደነገጉ ድንጋጌዎችን ጣምራዊ ንባብ እና ሌሎች አግባብነት ያላቸው ሕጎች  መሠረት በማድረግ የደረሰኝ ትርጉም እና ምንነት፣ የደረሰኞች ዓይነቶች እና ደረሰኝ የመስጠት ግዴታ ያለባቸው ግብር ከፋዮችን እነማን እነደሆኑ እንዲሁም ደረሰኝ መሰጠት ያለበት መች እንደሆነ በወፍ በረር መልኩ ለመዳሰስ እሞክራለሁኝ፡፡

  20987 Hits

በኢትዮጵያ የክስረት ሕግ ነጋዴ ከሰረ የሚባለው መቼ ነው? ከክሥረት ጋር የተያያዙ ወንጀሎችን ከወንጀል ሕጉ አንፃር

የንግድ ሥራ ኢትዮጵያውያን ከ 11 ኛው ምዕት አመት በፊት ባህር አቋርጠው ድንበር ሳይገድቧቸው ቤትና ሀገር ያፈራውን ከሌላው ለሙሙላትና ለመቀያየር አሁን የምንጠቀምበት አይነት ገንዘብ ከሌለበት ጊዜ ጀምሮ ንግድን ስራዬ ብለው ሲሰሩት ነበር። ረጅም ጉዞ በሚደረግብት የጥንቱ ንግድ ግን ሁሉ አልጋ በአልጋ አልነበረም። ያላሰቡት ሽፍታ ከመንገድ ሁሉን ከነጋዴው መዝረፍ፣ የተቀየሩት ንብረቶች ፈላጊ በማጣት ነጋዴውን አትራፊ ከመሆን ይልቅ አክስሮት፣ ለአባዳሪዎች እንግልትና ሲሳይ ይዳርገው ነበር። የከሰረ ነጋዴ በማህበረሰቡ ዘንድ የሚቆጠረው በስራው የገጠመው ዕድለቢስነት በመሆን ሳይሆን መቅሰፍት የወረደበት ተደርጎ ነው። የከሰረን ነጋዴ በጎሪጥ መመልከት፣ ብድር እንኳ ቢጠይቅ ማንም የማያበድረው በመሆኑ የተነሳ አንዴ ወድቆ የማይነሳ ምሳር የበዛበት የሚሆንበት አጋጣሚ አለ።

  1460 Hits

በፍርድ ከሄደች በቅሎየ ያለፍርድ የሄደች ጭብጦየ (ለውጥ የሚሹ የፍርድ ቤት ጉዳዮች)

ፍርድ ቤት የበደል ስር የሚቆረጥበት ፤ ተበዳይ የሚካስበት፤ አጥፊ የሚቀጣበትና መንግስት ከህግ በታች መሆኑ የሚረጋገጥበት መድረክ ነው፡፡ ፍርድ ቤት ፍትህ ከረቂቅነት ከፍ ብላ የምትታይ ፣ የምትሰማ እና የምትዳሰስ ህልው መሆኗ የሚታወቅበት አደባባይ ነው፡፡ ፍርድ ቤት የሰለጠነ ህዝብ የኔ የሚለውን ህግ የሚያስከብርበት መሳሪያ ነው፡፡ ህይወቱ ፣ ንብረቱና የኔ የሚላቸው እሴቶቹ ሁሉ ጥበቃ ያላቸው ስለመሆኑ የሚተማመንበት ዋሱ ነው ፍርድ ቤት፡፡

  13412 Hits
Tags:

ስለ ንብረት የዋጋ ግምት ጥቂት ነጥቦች

ለፍርድ ቤቶች በሚቀርቡ ክርክሮች ላይ የንብረትን ትክክለኛ የዋጋ ግምት ማወቅ የግድ አስፈላጊ የሚሆንባቸው ጊዜያቶች አሉ፡፡ ለመሆኑ የንብረት የዋጋ ግምት ማወቅ ለምን ያስፈልጋል? የንብረት የዋጋ ግምት ተገምቶ እንዲቀርብ የሚጠይቁ ሕጎች የትኞቹ ናቸው? የንብረት የዋጋ ግምት የመገመት ኃላፊነት በሕግ የተሰጠው ለማን ነው? በአሠራር ደረጃ የንብረት የዋጋ ግምት በማን እና እንዴት እየተገመተ ይገኛል? የንብረት ዋጋ ግምትን አስመልክቶ የሚታዩ ችግሮች ምንድን ናቸው? የንብረት የዋጋ ግምት ሲሰራ በመሠረታዊነት ሊካተቱ የሚገባቸው ነጥቦችስ ምንድን ናቸው? የሚሉና ሌሎች ተያያዥ ነጥቦች በዚህ ፅሁፍ በጥቂቱ እንዳስሳለን፡፡  

  19578 Hits

በፍትሐብሔር ጉዳይ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ላይ ብቻ በሚደረግ የክርክር ሥነ-ሥርዓታዊ ሂደት የተከራካሪዎች አለመቅረብ ውጤት፡ ሕጉና ትግበራ

“Law is nothing else, but the best reason of wise men applied for ages to the transaction and business of mankind” Abraham Lincoln

መነሻ ክስተት

ነገሩ እንዲህ ነው! የሙያ ባልደረቦቼ ደንበኞቻቸው ተከሳሽ በሆኑባቸው የፍትሐብሔር የፍርድ ሂደት ላይ መከላከያ መልሳቸውን ሲያቀርቡ በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 244(2) (ለ) መሠረት “ክስ የቀረበበት ጉዳይ አስቀድሞ በፍርድ የተወሰነ” መሆኑን እና (ሠ) መሠረት የቀረበው ክስ “በይርጋ የታገደ” መሆኑን ጠቅሰው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያቸውን በዋናው ክርክር ላይ ካላቸው መልስ ጋር አያይዘው አቅረበው ነበር፡፡ ነገር ግን ፍ/ቤቶች በቀረበው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ላይ ክርክር ለመስማት በተያዘ ቀነ ቀጠሮ ከሳሾች ሳይገኙ በመቅረታቸው ምክንያት ጉዳዩን እየመረመሩ የነበሩት ፍ/ቤቶች ተከሳሾች የቀረበባቸውን ክስ እንደሚክዱ ከጠየቁ በኃላ በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 73 መሠረት ክስ ለመስማት በተያዘ ቀነ-ቀጠሮ ከሳሾች ባለመቅረባቸው እና ተከሳሾች ክደው በመከራከራቸው መዝገቡን ዘግተናል በማለት ትዕዛዝ ሰጥተዋል፡፡

  22509 Hits

Active Participation of Children in Hostilities

Although there is no particular armed conflict or civil unrest in Ethiopia, it’s becoming common to see persons under 15 carrying a gun in different parts of the country. Although these pictures has been looked as fun by so many people, it becomes more serious when the children carrying the gun used some flags and have some connection with organized groups and parties in the country. Based on this assessment, there is a worry that in any case of an armed struggle or any hostilities there would be some kind of resentment to use those children under the age of 15 to actively participate in situations of conflicts. Thus, the following short legal analysis is made to inform any concerned party about the legal ramification of their activity in using children under the age of 15 to execute their military or any hostility related missions.

  9931 Hits

የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ማቆም መብትና ሕገወጥ ተግባሮች ምንነት በኢትዮጵያ የሕግ ማዕቀፍ

የዚህ አጭር ጽሑፍ ዓላማ የሲቪል አቪዬሽን ሠራተኞች የሥራ ማቆም አድማና የፌዴራል ፖሊስ የእስር ዕርምጃ ተከትሎ በተለያዩ ሚዲያዎች በመንግሥት በኩል በተወሰዱት ዕርምጃዎች ዙሪያ እየቀረቡ ያሉ ሕግ ነክ አስተያየቶች ውይይቶች፣ ሰሞነኛ ክርክሮችንና ተያያዥ ነጥቦች መነሻ በማድረግ በኢትዮጵያ ውስጥ የመንግሥት ሠራተኞች ሕጋዊ የሥራ ማቆም መብት የሕግ ወሰን እስከ የት ድረስ ነው? የሚለውን ጥያቄ ከሕገ መንግሥት መሠረታዊ መርሆች አንፃር በመመልከት በመብቱ አፈጻጸም ላይ የሚነሱ አንዳንድ የሕግ ጉዳዮችን በአጠቃላይ በአገሪቱ የተለያዩ የአሠሪና ሠራተኛ መብትና ግዴታዎችን አስመልክቶ በፌዴራል መንግሥት በኩል ከወጡ ሕጎች አንፃር በመጠኑ መዳሰስ ነው፡፡

  14764 Hits

Why Party-Appointed Arbitrators: A reflection

Arbitration has been a prevalent method of dispute settlement, in various countries of the world of today and yesterday. Arbitration is defined in the Black’s Law Dictionary as “a method of dispute resolution involving one or more neutral third party who the disputing parties usually agree to and whose decision is binding.”

  12043 Hits

The Right to Liberty and Privacy Right in Europe and the UK: Case Comment

The case originated by the application of two British nationals, Mr Kevin Gillan and Ms Pennie Quinton, against the United Kingdom of Great Britain and Northern Ireland alleging that the powers of stop and search used against them by the police breached their rights under arts 5, 8, 10 and 11 of the ECHR. The applicants were stopped and searched by police officers On 9 September 2003 near the site of an arms fair in east London, which was the subject of protests and demonstrations.

  10789 Hits

በሕግ አምላክ!

አገሬው ስለ ሕግ ሃያልነት ሲናገር "በሕግ አምላክ ሲባል እንኳን ሰው ወራጅ ውሃ ይቆማል" ይል ነበር፡፡ ሕግ ተፈጥሮንም እስከማቆም ሃይል እንዳለው አድርጎ ለመግለፅ ምን ዓይነት በሕግ የፀና እምነት ቢኖር ነበር ያስብላል፡፡ በሕግና ፍትሕ ላይ እምነት ያለው ሕዝብ ያለማንም አስገዳጅነት ለሕግ ተገዢ ነው፡፡ ክስተቶችንም ተከትሎ ለሕግ ያለውንም እምነት በተለያዬ መንገድ ይገልፃል፡፡ ግጭቶችን በጉልበት ከመፍታት በሕግ መፍታት ተመራጭ እንደሆነም ያምናል፡፡ በጉልበቱ አዳሪ ሲገጥመው ሰይፍን በሰይፍ ከመመለስ በሕግ አምላክ ቢል ይመርጣል፡፡ ከማትረባ ጉልበት በሕግ አምላክ ይሻላል የሚለውም ለዚህ ይመስላል፡፡ ስለዚህ የሕግ መከበር ሕበረተሰቡ ስለሕግና ፍትሕ ባለው አመለካከት ይወሰናል ማለት ነው፡፡ ሕግ በሕበረተሰቡ ውስጥ በሚፈለገው ደረጃ ለውጥ እንዲያመጣ ከተፈለገ እያንዳንዱ ሰው ስለሕግ ያለው አመለካከት አብሮ መመለወጥና ማደግ ይኖርበታል፡፡ ሕበረተሰቡ ለሕግና ፍትሕ ያለው አመለካከት ሁለት ነገሮችን ይገልፅልናል፡፡ በአንድ  በኩል ሕብረተሰቡ ስለሕግ ያለውን እምነት ሲገልፅልን በሌላ በኩል ደግሞ የሕግ መከበር ያለበትን ደረጃ ያሳየናል፡፡

  10926 Hits
Tags: