ቀለብ የመስጠጥ ግዴታ ፅንሰ ሀሳብ በተሻሻለው የኢትዮጵያ የቤተሰብ ሕግ

 

1. መግቢ

ግዴታ ህጋዊ ግንኙነት ሲሆን መሰረታዊ መርሁም የሚያካተው አንድ ዕዳ ያለበት ሰው ወይም ባለዕዳ ለአበዳሪው ዕዳውን የሚፈጽምበት ሂደት ነው፡፡ በዚህ ግንኙነት ውስጥ ባለዕዳው ለአበዳሪው አንድን ነገር ለማድረግ ፣ ለመስጠት ወይም ላለማድረግና ላለመስጠት የሚያደርገው ህጋዊ ግዴታ ነው፤ በተቃራኒው ደግሞ አበዳሪው ከባለዕዳው የሚገባውን እና በሕግ የተፈቀደለትን ጥቅም የሚያገኝበት ሁነት ነው፡፡ ግዴታዎች ከሁለት ምንጮች ይቀዳሉ፤ የመጀመሪያው ከውል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ከሕግ ነው፡፡ ከውል የሚመነጭ የግዴታ አይነት በተዋዋይ ወገኖች ስምምነት ላይ የሚመሰረት ሲሆን ስምምነቱም በተዋዋይ ወገኖቹ ላይ እንደ ሕግ እንደሚያገለግል የፍትሐብሔር ህጉ አንቀጽ 1731 ያትታል፡፡ ሁለተኛው የግዴታ ምንጭ ደግሞ ከሕግ የሚመዘዝ ነው፤ የዚህ አይነት ግዴታዎች በቀጥታ ከሕግ  የሚመነጩ ሲሆን ግዴታውም በባለዕዳው እና አበዳሪ ሰዎች ሊቀየር ፣ ሊሻሻል እንዲሁም ሊቀር አይችልም፡፡       

ቤተሰብ የአንድ ማህበረሰብ በጣም ጠቃሚ እና መሰረት የሆነ አካል ነው፡፡ ቤተሰብ አንድ ግለሰብን ከአጠቃላይ ማህበረሰብ ጋር የሚያገናኝ ታላቅ ድልድይ ነው፡፡ እንዲሁም ተፈጥሮዊ ኢኮነሚያዊ እና ማህበረሰባዊ ጥቅም አለው፡፡ ቀለብ የመስጠት ግዴታ በአብዛኛው በቤተሰብ መካከል የሚገኝ ሲሆን ተገላቢጦሽ ባህሪ አለው፡፡ ይህም ወላጆች ለልጆቻቸው ለሚያደርጉላቸው እንክብካቤ እና ለማሳደግ ላለባቸው ግዴታ ልጆችም በተራቸው ለቤተሰቦቻቸው በዕርጅና ወቅት፣ በችግር ላይ ላሉ ወንድም እና እህት እና ለሚወልዷቸው ልጆች ቀለብ የመስጠት ግዴታ ይኖርባቸዋል፡፡ ቀለብ የመስጠት ግዴታ ዋንኛ ምንጩ ከሕግ ቢሆንም በስምምነት ግዴታውን መመስረት ግን በግልጽ በሕግ አልተከለከለም፡፡ ይህ የሆነውም ቀለብ የመስጠት ግዴታ መሰረቱ በቤተሰብ መካከል የሚገኝን ግብረገባዊ ወይም ስነ-ምግባራዊ የመተጋገዝ ፣ የመረዳዳትና የመደጋገፍ ተግባር ስለሆነ ነው፡፡    

 

Continue reading
  13264 Hits

ስምና ድንጋጌዎቹ በኢትዮጵያ የፍትሐብሔር ሕግ

 

 

1. መግቢያ

 

ስም ሰዎችን ለመለየት የምንጠቀምበት ሁነኛ ዘዴ ነው፡፡ ይህም አንድን ሰው ከሌላ ሰው ለመለየት ለሰዎቹ ስያሜ በመስጠት በቀላሉ መለየት ይቻላል፡፡ የአገራችን ሕገ መንግሥት በአንቀጽ 36 (1) (ለ) ስምን የመሰየም የሁሉም ህጻናት መብት ነው ሲል ያትታል፡፡ በተጨማሪም ICCPR አንቀጽ 24 (2) እንደሚደነግገው ሁሉም ህጻናት እንደተወለዱ ወዲያውኑ እንዲመዘገቡ እና ስም እንዲወጣላቸው ያዛል፡፡

Continue reading
  12417 Hits

የፍርድ አፈፃፀም መሠረታዊ ታሳቢዎችና ያጋጠሙ ችግሮች

 

 

አፈፃፀም ፍርድ ቤት የሰጠውን ፍርድ በእራሱ አማካኝነት ወደ ተግባር የሚለውጥበት ሥርዓት ነው፡፡ ስለፍርድ አፈፃፀም የተደነገጉትን ድንጋጌዎች በመከተል ፍርድን በተግባር መተርጎም እንደመሆኑ መጠን የማስፈፀሚያ ሥርዓቱ በጥቅሉ የፍ/ብ/ሥ/ሥ ህጉን መሠረታዊ ዓላማ ተከትሎ በተቀላጠፈ ሁኔታ እንዲፈፀም በሚያስችል አኳኋን የተዋቀረ ነው፡፡

ይሁን እንጂ በተግባር እንደሚታየው ክስ አቅርቦ ለማስፈረድ ከሚወሰደው ውጭ ጊዜና ጉልበት ባልተናነሰ ሁኔታ የተፈረደን ፍርድ ለማስፈፀም የሚጠይቀው ወጭና ጊዜ በልጦ የሚታይበት ጊዜ ይከሰታል፡፡ ምክንያቶቹ በርካታ ናቸው፡፡

ከነዚህም ጥቂቶቹ፡-

Continue reading
  17129 Hits

ችሎት መድፈር በኢትዮጵያ ሕግ: ሕጉና አተገባበር

 

መግቢያ

"ችሎት መድፈር" ወይም Contempt of Court በአብዛኛው ሃገራት የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ግልጋሎት ላይ እየዋሉ ካሉ የሕግ ፅንሰ ሃሳቦች አንዱ ነው። ይህ የሕግ ፅንሰ ሃሳብ በእኛ ሃገር በሰፊው ሥራ ላይ እየዋለ ቢሆንም ከሕጉ መንፈስ ውጭ አተገባበሩ ላይ የሚታየው የሕግ አተረጓጎም ክፍተትና ልዩነት የተለያዩ የዜጎች መብት ጥሰቶችን ሲያስከትል ይታያል። 

ችሎት መድፈር በኢትዮጵያ ሕግ ምን ይመስላል? አተገባበሩና ችግሮቹስ?

"ችሎት መድፈር" ምን ማለት ነው?

ለሕግ ወይም ለፍርድ ቤት አለመታዘዝ፣ ለችሎት ክብር መንፈግ ወይም የፍርድ ቤትን ሥራ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለማወክ መሞከር አልያም ደግሞ በዳኝነት ሥራው ጣልቃ መግባት በተለምዶ "ችሎት መድፈር" ተብሎ ይጠራል።

Continue reading
  8525 Hits

የፌዴሬሽኑ አባል ክልሎች የፌዴራሉን መንግሥት ሕጎች አልፈፅምም ማለት ይችሉ ይሆን?

መግቢያ

የፌዴራል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 53 መሠረት በተቋቋመ ወዲህ ላለፉት 24 ዓመታት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከ1100 በላይ አዋጆችን ያወጣ ሲሆን ከእነዚህም አዋጆች ውስጥ በምክር ቤቱ በሚገኙ የገዢው ፓርቲ አባላት መካከል ሞቅ ያሉ ክርክሮችና የልዩነት ሃሳቦች ያስተናገዱ በጣት የሚቆጠሩ አዋጆች መሆናቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ሞቅ ያሉ ንትርክ አዘልና የልዩነት ሃሳቦች ከተንፀባረቁባቸው ሕጎች መካከል ለአብነት ያህል በሚንስትሮች ምክር ቤት ከየካቲት 06 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ ተፈፃሚነት የነበረውንና ለሁለተኛ ጊዜ በሚኒስትሮች ምክር ቤት አዋጅ ቁጥር 2/2010 የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተቀባይነት እንዲያገኝ በቀረበ ወቅት የተደረገው እልህ አስጨራሽ ክርክር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው፡፡

በተመሳሳይ መልኩ የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1101/2011 የፀደቀባት ሁኔታ የጋለ ክርክርን ያስተናገደ ነበር፡፡ የፌዴራሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ታህሳስ 11 ቀን 2011 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የኮሚሽኑን ማቋቋሚያ አዋጅን በ33 ተቃውሞ በ4 ድምፅ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል፡፡ በዚህ አዋጅ ላይ የተደረገው ክርክርና የሰላ ሂስ በምክር ቤቱ ባሉአባላት ብቻ ሳይወሰን ከምክር ቤቱ ውጪ ባሉ የፖለቲካና የሕግ ሊሂቃን መካከል የከረረ ክርክርና ትችት ሲያስተናግድ ሰንብቷል፡፡

የኮሚሽኑን ማቋቋሚያ አዋጅ ሕገ-መንግሥታዊነቱንና ሥልጣኑን በተመለከተ የሚቀርበው ድጋፍና ትችት በግለሰቦች ደረጃ ብቻ የቀረ ሳይሆን የትግራይ ክልል ምክር ቤት በጥር 18 ቀን 2011 ዓ.ም ባካሄደው 5ኛ ዓመት 14ኛ መደበኛ ጉባዔ ላይም የመከራከሪያ አድማስ ሆኖ በአዋጅ አፈፃፀም ላይ የክልል ምክር ቤቱን የውሳኔ ሃሳብ እስከማሰጠት ደርሷል፡፡

የዚህ ጽሑፍ መነሻ ሃሳብም የትግራይ ክልል ምክር ቤት በኮሚሽኑ ማቋቋሚያ አዋጅ ላይ በሰጠው የውሳኔ ሃሳብ ላይ ሲሆን በዚህም አግባብ የክልሉ ምክር ቤት የፌዴራሉን መንግሥት ሕጎች አልተገብርም ማለቱን ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንፃር ያለውን ውጤት እና የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ሥልጣንና ተግባርን አጠቃላይ እንድምታ የምንዳስስ ይሆናል፡፡

Continue reading
  11810 Hits

ሳይፋቱ ፍቺ በተሻሻለው የኢትዮጵያ የቤተሰብ ሕግ

 

1. መግቢ

ቤተሰብ የአንድ ማኅበረሰብ በጣም ጠቃሚ እና መሠረት የሆነ አካል ነው፡፡ ቤተሰብ አንድ ግለሰብን ከአጠቃላይ ማኅበረሰብ ጋር የሚያገናኝ ታላቅ ድልድይ ነው፡፡ እንዲሁም ተፈጥሮዊ ኢኮነሚያዊ እና ማኅበረሰባዊ ጥቅም አለው፡፡ በእርግጥ ቤተሰብ በቁጥር ትንሽ ሊሆን ይችላል ነገረግን የአንድ ቤተሰብ መፍረስ አጠቃላይ ማኅበረሰቡን ይጎዳል፡፡

ቤተሰብ በጋብቻ እንደሚመሠረት ሁሉ በፍቺ ይፈርሳል፡፡ በተለምዶ በቤተሰብ ሕጋችን ከተቀመጡት ጋብቻ ከሚፈርስባቸው መንገዶች በተጨማሪ ተጋቢዎች ለተለያዩ ምክንያቶች ሲሉ ህጋዊ ፍቺ ሳይፈፅሙ የሚያደርጉት መለያየት አንዱ ሲሆን ሳይፋቱ ፍቺ የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ይህ ሳይፋቱ ፍቺ ምንም እንኳን በሕግ አግባብ የሚደረግ ፍቺ ባይሆንም እንኳን ውርስ ላይ የራሱ የሆነ አስተዋፅኦ አሉት፡፡

 

Continue reading
  18936 Hits

Rocks of Hope: Interrogating PM DR Abiy Ahmed’s Reform within the Boomerang Model of Human Rights

 

Introduction

As I write this term paper, stream of demonstrations across Ethiopia has continued owing to human rights violations. Human rights and social movements have constitutive relationship. An Ethiopian scholar of human rights focuses on policy outcomes and legal decisions. Scholarship that examines this link in Ethiopia is relatively slow to develop.

Ethiopian People’s Democratic Revolutionary Front (EPDRF) has been attempting to silence social movements. There have been brutal crackdowns. The crackdown on people’s social movement resulted in further resistance. At this stage, the regime is giving locus for dissident voices and we are experiencing glimmer of hope for human rights protection is taking its resonance.  Hitherto, rapid pace of reform is taking place since the appointment of Prime Minister (PM) DR Abiy Ahmed as of April 2, 2018.

Rocks of hope are an engagement citizens have been taking for protection of human rights in Ethiopia. It represents a struggle for justice in the face of injustice.  It represents those who fought for equality in the face of inequality. It connotes optimism followed the reform. These are values of legitimate struggle. Values of legitimate struggle are terse in the Constitution of Federal Democratic Republic of Ethiopia, the Constitution herein after. Under the 7th paragraph of the Preamble of the Constitution, it is provided that the common struggle of Nations, Nationalities and Peoples has brought the peace and the prospects of democratic order of the country.

In human rights language, Boomerang Model is the strategy of identifying human rights violations someplace and then generating attention in order to bring pressure to bear on the perpetrators back in the country of concern. Repressive regimes may be subject to internal and external pressures to conform with human rights norms. In response, they may consider concessions to secure trade advantages, or because they have been ashamed for not conforming to the standards of the international community.

The theme of this term paper is interrogating the reform within the Boomerang Model. It deals with the resistance paid to bring the reform and the responses and steps taken. The pace of reform will be assessed in terms of the ramifications it has on human rights protection. It ends with conclusion and recommendation.

Continue reading
  11260 Hits

የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ሕገ-መንግሥታዊነት

ባለፈው ሳምንት መጨረሻ መንግሥት የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽንን የሚያቋቁም አዋጅ ማፅደቁ ይታወቃል፡፡ አዋጁ በተወካዮች ምክር ቤት ውስጥ የጦፈ ክርክርን አስነስቶ በ33 ተቃውሞ እና በ4 ድምፀ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምፅ ቢፀድቅም በፓርላማ ውስጥ ለአዋጁ ድምፅ ከነፈጉ የሕዝብ ተወካዮች ጀምሮ እስከ ክልል መንግሥታት ድረስ ሰፊ ተቃውሞን አስተናግዷል፡፡ ለተቃውሞው መነሻ የሆነው ዋነው ጉዳይ የማንነትም ሆነ በክልሎች መካከል የሚነሱ አለመግባባቶችን መፍታት የፌዴሬሽን ምክር ቤት እና የክልሎች ሥልጣን ሆኖ ሳለ ሌላ ተቋም የማቋቋም አስፈላጊነት እና ሕገ መንግሥታዊነት ጥያቄ ነው፡፡

ለእነዚህ ጉዳዮች በሕግ አግባብ መልስ ለመስጠት ሁለት ጉዳዮችን በጥልቀት ማገናዘብ ይጠይቃል፡፡ አንደኛው እና መሠረታዊው ጉዳይ በሕገመንግሥቱ እና በሥራ ላይ በነበሩ ሕጎች  መሠረት የማንነት እና ራስን የማስተዳደር ጥያቄዎች እንዲሁም በክልሎች መካከል የሚነሱ አለመግባባቶች የሚፈቱበት ሥርዓት ምን እንደሆነ መፈተሸ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ለኮሚሽኑ የተሰጠውን ሥልጣን እና ተግባር ከሕገ-መንግሥቱ ጋር በንፅፅር አይቶ ሕገ መንግሥታዊነቱን መመርመር ነው፡፡

የማንነት እና ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄዎች

በሕገ መንግሥቱ መሠረት የማንነት እና ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄዎችን የመፍታተት ሥልጣን በመሰረታዊነት የተሰጠው ለክልሎች (ምክር ቤት) ነው፡፡ ነገር ግን የመጨረሻ ውሳኔ የመስጠት ሥልጣን የፌዴሬሽን ምክር ቤት መሆኑ በሕገ መንግሥቱ ከመደንገጉም በላይ በአዋጅ ቁጥር 251/1993 እንደተቀመጠው ክልሎች ለቀረበላቸው ጥያቄ በአንድ ዓመት ውስጥ አጥጋቢ መልስ ካልሰጡ ጥያቄው በይግባኝ መልክ ለፌዴሬሽ ምክር ቤት ቀርቦ የመጨረሻ ውሳኔ ማግኘት ይችላል፡፡

በመሠረቱ በማንነት እና ራስን በራስ በማስተዳደር ጥያቄዎች መሀል ምን ልዩነት እና አንድነት እንዳለ በግልፅ ያስቀመጠ ሕግ የለም፡፡ በሕገ መንግሥቱና በሌሎች ሕጎችም ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ እንጂ ‹የማንነት ጥያቄ› በሚል አገላለፅ የተቀመጠ መብትም ሆነ ሥርዓት የለም፡፡ ከዚህ ባለፈም በአንዳንዶች ዘንድ በክልሎች መካከል የሚነሱ የወሰን አለመግባባቶች እና በማንነት ጥያቄዎች መካከል ያለውን ልዩነት ያለመረዳት ስህተት ይስተዋላል፡፡ በዚህ ላይ የሚነሱ ክፍተቶች እና አከራካሪ ጉዳዮች በሌላ ሰፊ ጽሑፍ ቢታዩ ተመራጭ ስለሆነ ዝርዝሩን በመተው ወደ ቀጣዩ ጉዳይ እናልፋለን፡፡

Continue reading
  10829 Hits

በኢትዮጵያ በኢንተርኔት ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብት እና ገደቡ

መግቢያ

ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብት ለዲሞክራሲያዊ ማህብረሰብ መፈጠር የመሰረት ድንጋይ ነው፡፡ ይህ መብት በጣም ረጅም ጊዜ ያስቆጥረ የሰው ልጅ መብት ሲሆን በዘመናት መካከል በፈላጭቆራጭ ነገስታት እና መሪዎች ጫና ተደርጎበታል፡፡ ለአብነት ያህልም በጥንታዊ ባቢሎናዊያን የልዩነት ሃሳብ (being dissenter) መያዝ ወደ እቶን እሳት ያስጨምር እንደነበር ከመጽሃፈ ዳንኤል  ምዕራፍ 3 ንባብ መረዳት እንችላለን፡፡

ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብት የፍልስፍና መሰረቱ ከጥንት ግሪካዊያን ስልጣኔ ጋር አብሮ ይነሳል፡፡ በተለየም የዴሞክራሲ ታሪካዊ ከተማ በሆነችው አቴንስ የመናገር ነጻነት ዋጋ ህይዎትን እስከወዲያኛው ሊያስነጥቅ የሚችል ነገር ነበር፡፡ በዚህ ረገድ የሶቀራጥስ የፍርድ ችሎት ለዘመናት እንደ የመናገር ነጻነት ጥሰት ተደርጎ በድርሳናት ይወሳል፡፡ (አርሊን ሳክሶንሃውስ፡2006፡102)

በአውሮፓዊያን የዕውቀት ስልጣኔ (enlightenment period) ጫፍ በነካበት ወቅት የመናገር ነጻነት አምባገነን መንግስታትን በሃሳብ ለመሞገት የሚስችል መሳሪያ ነበር፡፡ ለምሳሌ:- ባሮን ሞንተስኩ የተባለ የፈረንሳይ ፈላስፋ የመንግስት ስልጣን ሕግ አውጪ፣ ሕግ አስፍፃሚ እና ሕግ ተርጓሚ ተብሎ መከፈል እንዳለበት በጹሁፍ እና በቃል በማስተማሩ የማታ ማታ ሃሳቡ ተቀባይነት ሊያገኝ ችሏል፡፡ በኋላም እኤአ ከ 1789_1799 ዓ.ም በነበረው የፈረንሳይ አቢዮት የመናገር መብት የሰው ልጆች ትልቁ ነጻነት እንደነበር ታሪክ መዝግቦታል፡፡ በታላቋ ብሪታኒያ እና አሜሪካም የመናገር ነጻነት የሊብራል የፖለቲካ አስተሳሰብ እና ዴሞክራሲ እንዲያብብ በማስቻል ረገድ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል፡፡ በተለይም እነዚህ አገራት ጆን ሚልተን፣ ጆን ስቱዋርት ሚልን ጨምሮ ጀምስ ማዲሰንን የመሰሉ ሃሳብን በነጻነት የመናገር መብት ተሟጋቾችን አፍርተዋል፡፡

ልክ እንደ ዘመነ ሶክራጥስ ሁሉ ዛሬም ሃሳብን በነጻ መግለጽ እንደ ጅማል ካሾጊ ህይዎትን እስክ ወዲያኛው ሊያስከፍል ይችላል፡፡ በአምባገነኖች ግፊት አገር እስጥሎ ስደተኛ ያደርጋል፤ ለእስር ብሎም ለተለያዩ እንግልቶች ይዳርጋል፡፡

ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብት ሲባል ግለሰቦች ሃሳባችውን መግለጽ፣ መረጃ ማግኘት፣ መጠየቅ እንዲሁም ለሌሎች የማካፈል መብትን ጨምሮ በፈለጉት መንገድ ማለትም በጽሁፍ፣ በንግግር፣ በምልክት፤ በኢንተርኔት ወይም በሌላ መንገድ በመጠቀም መልዕክት የማስተላልፍ መብት ነው፡፡

Continue reading
  12777 Hits

Stolen Asset Recovery in Ethiopia: Critical Legal Issues and Challenges

  1. Introduction

Staling public money hurts the poor disproportionately by diverting funds intended for development, undermining a Government’s ability to provide basic services, feeding inequality and injustice, discouraging foreign aid and investment, fundamentally distorts public policy and  leads to the misallocation of resources. What makes things worse is that the offence is usually committed by political parties.  Political parties are often seen as actors who abuse their powerful position to extort bribes, to supply members and followers with lucrative positions in the public sector, or to channel public resources into the hands of party leaders or supporters.  In this regard, the 2016 Republican Presidential candidate Dr. Ben Carson once made a statement, “We have been conditioned to think that only politicians can solve our problems. But at some point, maybe we will wake up and recognize that it was politicians who created our problems.”

Party corruption is especially problematic in developing and transitional countries where political and economic institutions are not yet fixed. This is highly prevalent in most fragile states including Ethiopia. The real problems of corruption in developing countries like ours are highlighted by the then UN Secretary-General, Ban Ki-moon in his 2009 speech for the international anti-Corruption day as:

When public money is stolen for private gain, it means fewer resources to build schools, hospitals, roads and water treatment facilities. When foreign aid is diverted into private bank accounts, major infrastructure projects come to a halt. Corruption enables fake or substandard medicines to be dumped on the market, and hazardous waste to be dumped in landfill sites and in oceans. The vulnerable suffer first and worst.”

In Ethiopia, corruption is perceived to have significant adverse effects and that public sector red tape is the biggest hurdle in the way of improved government-citizen relationships. Currently, what makes things worse is that beyond the corrupted officials deposited their stolen asset in foreign country like Singapore and Dubai bank, the government allows corrupt officials to stay in power.

It is a euphemistic way of saying to corrupted individuals as, “Hi folks, you are in safe heaven now as long as we are in power and as long as you support our government policies no matter what.” The result of all this makes Ethiopia among the fragile state and aid dependent, in which the poor and the vulnerable suffer first and worst. To overcome the aforementioned problems, a strong legislative and regulatory framework with multiple legal tools to detect criminal activity and illicit financial flows, rapidly freeze assets, and conduct effective investigations and court processes is necessary. Off course, some Ethiopian officials starting to make a statement in various spots that Ethiopia had been doing its best and committed to the implementation of international agreements, stolen asset recovery. Accordingly, in this paper the author tries to analyze the international legal instruments on stolen asset recovery, showing the barriers of stolen asset recovery and identifying the legal lacunas witnessed under the Ethiopian legal frameworks regulating stolen asset recovery. 

Continue reading
  9564 Hits