ስለ ሸሪኣ ፍርድ ቤቶች መልስ የሚሹ ጉዳዮች

በተደራጀ እና በብሔራዊ ሕግ ዕውቅና አይሰጣቸው እንጂ በኢትዮጵያ የሸሪኣ ሕግን መሠረት በማድረግ ውሳኔ መስጠት የቅርብ ታሪክ አይደለም፡፡ በታወቀ ሁኔታ እና በመንግሥት ድጋፍ የሸሪኣ ፍርድ ቤቶች የተቋቋሙት ግን በ1934 ዓ.ም. ነው፡፡ ከዚያ ብዙም ሳይቆይ ሕጉ ከሁለት ዓመት በኋላ ተሻሻለ፡፡ ቀጥሎም አገሪቱ በፌደራል ሥርዓት መተዳዳር ከጀመረች በኋላ በ1992 ዓ.ም. እንደ አዲስ የፌደራል ሸሪኣ ፍርድ ቤቶች ተቋቋሙ፡፡ በፌደራል ብቻ ሳይወሰኑ በክልሎቹም እንዲሁ ተቋቋሙ፡፡ ለዚህ ደግሞ ዋና መሠረቱ አሁን በሥራ ላይ ያለው ሕገ መንግሥት ነው፡፡ በአንዳንድ ክልሎች፣ ከመደበኛው ፍርድ ቤት ጎን ለጎን በችሎትነት ሲቋቋሙ በፌደራል ደረጃ ግን ራሳቸውን ችለው የመጀመሪያ ደረጃ፣ ከፍተኛ እና ጠቅላይ ሸሪኣ ፍርድ ቤቶች በመባል ተቋቁመዋል፡፡

Continue reading
  15815 Hits

የዘገየ ፍርድ

እኔ አንቺን ስጠብቅ

ጠበኩሽ እኔማ…….

እዚያው ሰፈር ቆሜ

በአክሱም ቁመና በላሊበላ ዕድሜ

እግሮቼን ተክዬ ቀኔን አስረዝሜ

ትመጫለሽ ብዬ በቆምኩበት ስፍራ

ስንት ነገር መጣ ስንት ነገር ሄደ

ስንት ጊዜ ነጋ ስንቴ ጎህ ቀደደ

በቀጠርሽኝ ስፍራ ስጠብቅሽ ቆሜ

ስንት ሳቅ አለፈ ስንትና ስንት እንባ

ስንቴ ክረምት ሆነ ስንቴ ጸደይ ጠባ……..

                    ታገል ሰይፉ

Continue reading
  14844 Hits

ስለማስረጃ ሕግ አደረጃጀት

የማስረጃ ሕግ የማስረጃን አግባብነት፣ የማስረጃን ተቀባይነት እንዲሁም የማስረጃን ክብደትና ብቃት የሚገዙ ደንቦችና መርሆዎች ጥርቅም ነው፡፡ ማስረጃ ተሟጋቾች በአቤቱታቸው አማካኝነት ፍርድ ቤት የያዘውን ጭብጥ የሚያረጋግጡበት ዘዴ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ማስረጃ ማለት ፍርድ ቤት የያዘውን አከራካሪ ጉዳይ ወይም ጭብጥ በሚሰማበት ጊዜ ተሟጋቾች የጥያቄውን አግባብነት፣ እውነትነት፣ በምስክሮች፣ በሠነድ፣ ተጨባጭነት ባላቸው ሌሎች ነገሮች፣ ወዘተ… ማስረጃ ለፍርድ ቤቱ የሚያረጋግጡበት አሊያም ውድቅ የሚያደርጉበት ዘዴ ነው፡፡ ማስረጃ ሲባል የአንድን ፍሬ ነገር ህልው መሆን ወይም አለመሆን ለማረጋገጥ ያገለግል ዘንድ ክስ በሚሰማበት ጊዜ ወይም የክርክር ጭብጥ በሚጣራበት ወቅት በተከራካሪ ወገኖች ወይም ክርክሩን በሚያየው ፍርድ ቤት ትዕዛዝ አማካኝነት የሚቀርብ ማናቸውም ዓይነት የአስረጂነት ባህርይ ያለው ነገር ነው፡፡ ማስረጃ በምስክሮች (Witnesses)፣ በዘገባ (Record)፣ በሠነድ (Document)፣ ተጨባጭነት ባላቸው ሊታዩ ሊዳሰሱ በሚችሉ ነገሮች (Concrete Objects) እና በኤግዚቢት መልክ ሊቀርብ ይቸላል፡፡ አቀራረቡም በሕግ በተደነገገው ሥርዓት መሠረት ነው፡፡ የክርክሩን ጭብጥ ፍሬ ነገር እውነት ወይም ሀሰት መሆኑን የማሳመን ኃይል ያለው እንደመሆኑ እና በዚህም ወደ ውሳኔ የሚያደርሰው ስለሆነ ሊገኝም ሊቀርብም የሚገባው በሕግ አግባብ ነው፡፡ ማስረጃው ተቀባይነት ወይም ውድቅ የሚደረገው እንደዚሁም ሊሰጠው የሚገባው ክብደት የሚመዘነውም በሕግ አግባብ ነው፡፡

Continue reading
  17940 Hits
Tags:

አስገዳጁ የኮንስትራክሽን ኢንሹራንስ የሕንጻ መደርመስን ይከላከለው ይሆን?

ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነው ጉዳይ ልክ የዛሬ አመት ገደማ በአዲስ አበባ ቦሌ ክ/ከተማ ልዩ ስሙ ሰሚት በሚባል ስፍራ የተደረመሰውን ህንጻ እና እሱን ተከትሎ የከተማ አስተዳደሩ ባወጣው ደብዳቤ (circular) መሰረት አስገዳጅ የኮንስትራክሽን ኢንሹራንስ በድጋሜ እንዲኖር መደረጉን በማስመልከት ነው፡፡ ኢንሹራንስ (መድን) የሚለው ቃል ሲነሳ ምንግዜም ቢሆን ሊዘነጋ የማይችለውጉዳይ የአደጋ (risk) መኖር ነው፡፡ የአደጋ መከሰት ለመድን ቅድመ ሁኔታ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡

Continue reading
  15941 Hits

የሦስተኛ ወገኖች መብትና የግልግል ሂደት

ግልግል በፍትሐብሔር ሕጋችን እውቅና ከተሰጣቸው የሙግት መፍቻ ዘዴዎች አንዱ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ተከራካሪዎችም ጉዳያቸውን ወደ ግልግል የሚወስዱት በመካከላቸው በሕግ ፊት የሚጸና የግልግል ስምምነት እስካለ ድረስ ብቻ ነው፡፡ በዚህ ጽሑፍ በግልግል ሂደት መብታቸው የሚነካ ሦስተኛ ወገኖች ምን ዓይነት መፍትሔ ሊያገኙ ይችላሉ የሚለውን ለመመልከት ይሞክራሉ፡፡ በዚህ ጽሑፍ ላይ የቀረበው በየካቲት ወር 2009 ዓ.ም ለገበያ ከበቃው ‹‹የግልግል ዳኝነት በኢትዮጵያ›› ከተሰኘው መጽሐፍ ላይ የተቀነጨበ ነው፡፡

Continue reading
  19622 Hits

ሕግ መንግሥቱን በፖለሲ ማዕቀፍ ሥር?

ሰሞኑን በአንድ ካፌ ገብቼ የተደረደሩ ቀን ያለፈባቸው ጋዜጦች ስመለከት የሪፖርተር ጋዜጣ በሚያዚያ 1/2009 የእለተ-እሁድ እትሙ ላይ “ሰበር ሰሚ ችሎት  በክራውን ሆቴል የንግድ ምልክት ላይ የሰጠው የመጨረሻ ውሳኔ ሕገ መንግሥታዊ ትርጉም ያስፈልገዋል ተባለ” በሚል ርእስ ባወጣው ዘገባ ላይ ዐይኔ አረፈ። ከዚህ በፊት በርካታ ጉዳዮች ወደ ሕገ መንግሥት አጣሪ ጉባኤ ስለመቅረባቸው አውቃለሁ። በሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ላይ የሕገ መንግሥት ጉዳይ ክርክር ተነስቶበት ወደ ጉባኤው ስለመቅረቡ ሳነብ ግን የመጀመሪያዬ ነው።  ምናልባት እኔ ያላወቅኳዋቸው ተመሳሳይ ጉዳዮች ከዚህ በፊት ቀርበው ይሆናል። ያም ሆነ ይህ ርእሰ ጉዳዩ ቀልቤን ስለሳበው ባለጉዳዮቹ  ስለተከራከሩበት ጉዳይና የችሎቱ ውሰኔ  ለማወቅ ጉጉት አደረብኝ። እናም  ወደ ሕገ መንግሥት አጣሪ ጉባኤ ስለተወሰደው የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔና ስለክርክሩ ከሥሩ ለማየት ወሰንኩ። ስለሆነም የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ቅጂ ፈልጌ በመመልከት የሚከተለውን  የግል እስተያየቴን ለመጻፍ ውደድኩኝ።

Continue reading
  14869 Hits

የባንክ ዋስትና ሰነዶች (Letter of Guarantees) በኢትዮጵያ ሕግ ያላቸው ሽፋን

የዋስትና ሰነዶች ባንኮች በተለይም ለደንበኞቻቸው ከሚሰጧቸው የብድር አገልግሎቶች መካከል ዋነኞቹ ናቸው። የዋስትና ሰነዶች በተለያዩ ስያሜዎች የሚጠሩ ሲሆን በዚህም መሠረት በእንግሊዝኛ ‘independent undertakings’, ‘performance bonds/guarantees’, ‘tender bonds/guarantees’, ‘independent (bank) guarantees’, ‘demand guarantees’, ‘first demand guarantees’, ‘bank guarantees’, and ‘default undertakings’ በሚሉ ስሞች ሊጠሩ ይችላሉ። ከዚህ በተጨማሪም እነዚሁ ሰነዶች ‘standby Letters of Credit’ ተብለው ሊጠሩ እንደሚችሉ የተለያዩ ጽሑፎች ያሳያሉ። በዚህ መጽሐፍ ውስጥም የዋስትና ሰነዶች የሚለው ጥቅል ስያሜን ለመጠቀም የተሞከረ ሲሆን አንዳንዶቹ ስያሜዎችም የዋስትና ዓይነቶችን የሚያመለክቱ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል። የዋስትና ሰነዶች በባንኮች የሚሰጡት ደንበኞች የተለያዩ ስምምነቶችን ከሌሎች ሦስተኛ ወገኞች ጋር ፈጽመው ያለባቸውን ግዴታ በአግባቡ ለመወጣታቸው ከባንኮች ዋስትና እንዲሰጥላቸው በሚያቀርቡት ጥያቄ መሠረት ነው። የዋስትና ደብዳቤ የሚሰጠውም አንድን ሰው የብድር አገልግሎት ወይም እቃዎቸንና አገልግሎቶችን ለሌላ ሦስተኛ ወገን በብቃት እንዲያቀርብ መተማመኛ በመሆን ነው። ዋስትና ሰነድም አንድ ሰው አንድን የተለየና የተወሰነ ሥራ ለሌላ ሰው ለመሥራት ግዴታ ከገባ ይኸው ሰው በውሉ መሠረት የገባውን ግዴታ መፈጸም የሚችል መሆኑን ለማረጋገጥ ሌላው ሰው የሚያቀርበው ውል ነው። (የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰበር መዝገብ ቁጥር 47004 ተመልከቱ) የዋስትና ሰነዶች የባንክ የብድር ዓይነቶች ወይም የብድር አገልግሎት መሆናቸውን ከማየታችን በፊት ግን የዋስትና ሰነዶች ምን ማለት እንደሆኑ ማየቱ ተገቢነት ይኖረዋል።

Continue reading
  22611 Hits

DNA አባትነትን ማረጋገጫ ማስረጃ ስላለመሆኑ

ሁሉም ሰው ባዮሎጂካዊ አባት አለው ሁሉም ሰው ግን ህጋዊ አባት ላይኖረው ይችላል፡፡ ይህ አረፍተ ነገር በብዙዎቻችሁ ጭንቅላት እንዴ! የሚል ግርምት እንደሚያጭር እገምታለሁ፡፡ በተለይ ሁሉም ልጅ እኩል ነው ልጆች አባትና እናታቸውን የማወቅ ሕገ መንግሥታዊ መብት አላችሁ የሚለው አነጋገር አብዝቶ ከመሰማቱ የተነሳ በሕግ አባት የሌለው ልጅ ሊኖር ይችላል ብሎ መገመት ሩቅ ሊሆን ይችላል በቀጣዩ ጽሑፍ በመግቢዬ የገለፅኩት ሀሳብ ምን ያህል እውነት እንደሆነ ለማሳየት እታትራለሁ፡፡

Continue reading
  27232 Hits
Tags:

ስለ ይርጋ ጥቂት ነጥቦች

ይርጋ ምንድን ነው? ይርጋ ዓላማው (ጠቀሜታው) ምንድን ነው? ይርጋ ጉዳቱስ ምንድን ነው? ይርጋ የሚያስጠብቀው የማንን መብት ነው? የይርጋ መሠረታዊ መርሆዎች ምንድን ናቸው? ይርጋን የሚመለከቱ የሕግ ድንጋጌዎች ምን ይመስላሉ? በይርጋ የማይታገዱ ጉዳዮች ምንድን ናቸው? የሚሉና ሌሎች ተያያዥ ነጥቦች በዚህ ጽሑፍ ይዳሰሳሉ፡፡

Continue reading
  37825 Hits

ዓለም አቀፍ ስምምነቶች በኢትዮጵያ የሕግ ሥርዓት ያላቸው ደረጃ

ስለዓለም አቀፍ ሕግ በአጭሩ

ዓለም አቀፍ ሕግ በሉዓላዊ አገሮች መካከል ያለን ግንኙነት ወይም በአገሮችና እንደተባበሩት መንግሥታት ያሉ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች መካከል ያለን ግንኙነት የሚገዛ የሁሉ አቀፍ ደንቦች እና መርሆዎች ሥርዓት ነው። በሌላ አነጋገር «International law is the universal system of rules and principles concerning the relations between sovereign States, and relations between States and international organizations such as the United Nations» የሚል ትርጉም ተሰጥቶት እናገኘዋለን። ቀደም ባሉት ጊዜያት በዓለም አቀፍ ሕግ እና በየሐገሩ በሚገኙ ዜጎች፣ ሉአላዊ ባለሆኑ አካላት (Transnational Corporations) እና መንግሥታዊ ባለሆኑ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች (International Non-Governmental Organization) ቀጥተኛ ግንኙነት ያለነበረ ቢሆንም አሁን አሁን ግን ይህ የታሰበው ቀጥተኛ ግንኙነት በስፋት እየታየ መሆኑን ዓለም አቀፍ ምሁራንን እያስማማ ነው።

Continue reading
  18900 Hits