አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 እና አንዳንድ ጉዳዮች

 

ከዚህ ቀደም በሀገራችን ኢትዮጵያ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይን የሚገዙ ሕጎች እንደነበሩ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ በ1955 ዓ.ም የወጣው የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 210/1955፣ በ1968 ዓ.ም የወጣው የሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 64/1968፣ የሠራተኛ ጉዳይ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 85/1968፣ ስለአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ የወጣው አዋጅ ቁጥር 42/1985 እና አዋጅ ቁጥር 377/1996 የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

ከየካቲት 18 ቀን 1996 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ በግሉ ዘርፍ ያለውን የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነትና መስተጋብር እንደ ዋነኛ ምሰሶ በመሆን ሲያስተዳድር የነበረው ሕግ አዋጅ ቁጥር 377/1996 እና የዚህ አዋጅ ማሻሻያ ሕጎቹ አዋጅ ቁጥር 466/1997 እና አዋጅ ቁጥር 494/1998 ነበሩ፡፡ እነዚህ ሕጎች ከ14 አመታት በላይ በሥራ ላይ የዋሉ በመሆናቸው አሁን ካለው የማህበረሰብ እድገት ጋር የተጣጣሙ ባለመሆናቸው የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቀን ሰኔ 27 ቀን 2011 ዓ.ም ባደረገው 4ኛ አመት የሥራ ዘመን 48ኛ መደበኛ ስብሰባው የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ረቅቅ አዋጅን መርምሮ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡

ይህም ሕግ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ዓ.ም ሆኖ ነሐሴ 30 ቀን 2011 ዓ.ም በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ በሥራ ላይ ውሏል፡፡ ይህ አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ምን ምን ሀሳቦችን አካቶ ነው የተሻሻለው? ለሠራተኛው ምን ዓይነት ሕጋዊ ጥቅምና መብቶችን አካቷል? እንዲሁም የአሠሪ ግዴታና መብት ምን ይመስላል? የሚሉትን ጉዳዮች እና አዲሱን አዋጅ ከተሻረው የአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ቁጥር 377/96 በማነፃፀር በወፍ በረር (Bird’s Eye View) እንደሚከተለው እንመለከታለን፡፡

አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ከዚህ ቀደም የነበረውን አዋጅ ከነ ማሻሻያዎቹ በመሻር እና የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጄንሲ አዋጅ ቁጥር 632/2001ን በአዲሱ አዋጅ ውስጥ በማካተት ነው በሥራ ላይ የዋለው፡፡

Continue reading
  79658 Hits

The Quest to modernize: Is acceding to the New York Convention the right thing for Ethiopia?

 

It would be appropriate to begin by saying few words about the New York Convention for the Recognition and Enforcement of Foreign Arbitral Awards which came into being in 1948. By the way, our Civil Procedure Code was enacted in 1948 E.C; while the convention was passed in 1948 G.C. Now, simply put, it is a very popular convention in the international arbitration community and is used to enforce an arbitral award (both commercial and non-commercial) in another country.

 

The main point of this post is not to explain the nature of the convention, but to ask if Ethiopia’s initiation to accede to the convention is the right thing. Recently, the Ethiopian government is weighing pros and cons of approving the instrument. It is inviting legal professionals and major stakeholders to speak their concerns or forward their comments on the advantages or disadvantages of signing the New York Convention.

 

Continue reading
  7947 Hits

Contemporary Violations of Human Rights in Ethiopia in light of Tripartite Human Rights Obligations

 

 

“The world can never be at peace unless people have security in their daily lives.”

UNDP. 1994. Human Development Report 1994.

When governments or non-state actors do horrible, cruel and unjust things to their citizens we are now likely to describe those actions as violations of human rights-instead of simply saying that they are unjust, immoral, or barbaric. Human rights are not just illusions they are certain basic entitlements tied to all human beings irrespective of any status.

Continue reading
  9206 Hits
Tags:

በቂ ምክንያት ሳይኖር ዳኛ ከችሎት ይነሳልኝ በሚል የሚቀርብ ማመልከቻ ላይ ስለተቀመጠው ቅጣት

 

መግቢያ

ለዚህ ጽሑፍ ምክንያት የሆነኝ ከታች እንደተገለጸው አንድ ተከራካሪ ወገን በፍ/ቤት ክርክር በሚያቀርብበት ወቅት ሊያጋጥሙት ከሚችሉ ጉዳዮች አንዱ ከችሎት ይነሳልኝ (ችሎት ይቀየርልኝ) በሚል የሚቀርብ አቤቱታ ሲሆን ዳኞች ከችሎት የሚነሱባቸውን ምክንያቶችና ባለጉዳዮች ምን ማድረግ እንዳለባቸው በአዋጅ ቁጥር 25/88 ከአንቀጽ 27 እስከ 30 ባሉት ድንጋጌዎች የተመለከተ ሲሆን የዚህ ጽሑፍ ዋነኛ አላማ እነዚህን ምክንያቶች ማብራራት ሳይሆን ማመልከቻው ውድቅ ቢደረግ አመልካቹ (ተከራካሪው) ሊቀጣ የሚችለውን አዋጁ በአንቀጽ 30 ላይ ያስቀመጠውን የገንዘብ መቀጫ አግባብነትና ፍትሃዊነት ላይ ሃሳብ ለመስጠት ነው፡፡

አንቀጽ 30 - በቂ ምክንያት ሳይኖር የሚቀርብ ማመልከቻ ስለሚያስከትለው ቅጣት

“ከተከራካሪዎቹ አንድኛው ወገን ዳኛው ከችሎት እንዲነሳለት ያቀረበው ማመልከቻ በቂ ምክንያት ሳይኖረው የቀረ እንደሆነ ፍ/ቤቱ ማመልከቻውን ውድቅ አድርጎ በአመልካቹ ላይ እስከ አምስ መቶ (፭፻) ብር መቀጫ ሊጥልበት ይችላል፡፡”

Continue reading
  7952 Hits

Effect of Irregularities in Public Contract Awarding

 

 

 

Abstract

Continue reading
  7953 Hits

‘ኮማንድ ፖስት’ ለአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተሰጠ ልዋጭ ስም?

በሀገራችን ኢትዮጵያ የፀጥታ ችግር በተለያዩ ጊዜያትና ቦታዎች ሲከሰት መንግሥት በሕግ የተቀመጠለትን መደበኛውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመጠቀም ፈንታ በስም የተለየ ነገር ግን በአተገባበር ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር ተመሳሳይነት ያለውን የሕግ ማስከበር መንገድ ‘ኮማንድ ፖስት’ በሚል ስያሜ እያዘወተረ እየተጠቀመ ይገኛል፡፡ ከዚህም በመነሳት ህብረተሰቡም ይህንኑ ኮማንድ ፖስት የተባለውን ስያሜ እኩል ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር አገናኝቶ ሲጠቀም ይስተዋላል፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት ኮማንድ ፖስት መንግሥት በመደበኛ የሕግ ማስከበር መንገድ ሕግን ማስከበር ሲቸገር እየተጠቀመው የሚገኝና በተግባርም የግለሰቦችን መብት የሚገድቡ ክልከላዎችን ጭምር በማውጣት በተግባር ተጠያቂ እያደረገ በመስተዋሉ ነው፡፡ ብዙን ጊዜ ይህንን አዋጅ ሲያውጅ የሚስተዋለው በፌደራል ደረጃ የተዋቀረ ‘ብሔራዊ የፀጥታ ም/ቤት’ የሚባል አካል እነደሆነ ይደመጣል፡፡ ይህ አካል አዋጁን ያውጅ ዘንድ በሕገ-መንግሥቱ ሥልጣን የተሰጠው አካል እንዳይደለ መረዳትም ይቻላል፡፡

በሌላ በኩል እየተዘወተረ የመጣው የክልሎች የጸጥታ መደፍረስን ምክንያት በማድረግ ‘ኮማንድ ፖስት’ እያወጁ የግለሰቦችን መብት መገደብ በብዛት እየተስተዋለ የመጣ ሲሆን ይህ ስልጣን በህገ-መንግስቱ ለነርሱ ያልተሰጠ ሆኖ ሳለ ይኸው ‘ኮማንድ ፖስት’ የተባለው ሲያሜ ምቹ አጋጣሚ እንደፈጠረላቸው እንመለከታለን፡፡

በዚህ ጽሑፍ ስለአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምንነት፤ ለምን እንደሚታወጅ፤ ማን እንደሚያውጀው እና ሲታወጅም ይሁን ከታወጀ በኃላ አዋጁንና አፈፃፀሙን በሚመለከት ሊሟሉ የሚገባቸው ይዘታዊም ሆኑ ሥነ-ሥርዓታዊ የሕግ መጠይቆችን እንመለከታለን፡፡ ከዚሁ ጋር አያይዘንም ከላይ ያተትነው ኮማንድ ፖስት የተባለው አዋጅን ከመደበኛው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጽንሰ ሃሳብ ጋር አገናኝተን እንመለከትና በዚሁ ኢ-መደበኛ አዋጅ ያሉትን ችግሮች ነቅሰን በማውጣት መሆን አለበት የምንላቸውን መፍትሔዎች እናስቀምጣለን፡፡

መግቢያ

አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማለት መንግሥት በመደበኛ ሕግና የሕግ አስከባሪ አካላት ሕግን የማስከበር አቅሙ ጥያቄ ውስጥ ሲገባ የሚታወጅ የግለሰቦችን መብት የመገደቢያና የተፈጠረን ችግርን ለመፍታት የሚሰራበት የሕግ ስሪት መንገድ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ ምክንያት የሚሆኑ ጉዳዮች ምንጫቸው ተፈጥሮአዊ (ለምሳሌ፡- የመሬት መደርመስ /መንሸራተት/፤ ያልተጠበቀ ጎርፍ እና የህዘብን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ ተላላፊ በሽታዎች መከሰት ወይም ሰው ሰራሽ (ለምሳሌ፡- የውጭ ወረራ ሲያጋጥም፤ አመጽ፤ መፈንቅለ መንግሥትና የመሳሰሉት….) ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

Continue reading
  8410 Hits

ወደኋላ ሄዶ ተግባራዊ የሚያደርጉ የታክስና ጉምሩክ ሕግ ድንጋጌዎች ሕገ መንግሥታዊነት

 

 

   . ወደኋላ ሄዶ ተግባራዊ የሚያደርጉ የታክስና ጉምሩክ ሕግ ድንጋጌዎች ሕገ መንግሥታዊነት 

የታክስና የጉምሩክ ሕጎች ስንል ምን ማለታችን ነው? ከሕገ መንግሥቱ ጋር ያላቸው ዝምድናስ ምን ይመስላል ?

በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/08 አንቀጽ 2(36) መሠረት የታክስ ሕግ ማለት የጉምሩክ ሕግን ሳይጨምር የታክስ አስተዳደር አዋጅ፣ የፌደራል የገቢ ግብር አዋጅ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ፣ የኤክሳይስ ታክስ አዋጅ፣ የቴምብርና የተርን ኦቨር ታክስ አዋጅ፣ ታክስ/ቀረጥ/ክፍያ ለመጣል የሚወጣ ሕግ እንድሁም እነዚህን አዋጆች መሠረት በማድረግ የሚወጡ ደንብና መመሪያዎችን ያካትታል፡፡ የጉምሩክ ሕግ ማለት ደግሞ በጉምሩክ አዋጅ ቁጥር 859/06 አንቀጽ 2(39) መሠረት የጉምሩክ አዋጁን፣ አዋጁን ተከትለው የሚወጡ የጉምሩክ ደንብና መመሪያዎችን እንድሁም የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን /የአሁኑ ገቢዎች ሚኒሰቴር/ የሚያስፈፀማቸውን ሌሎች ሕጎች ያካትታል፡፡

Continue reading
  10199 Hits

ንብረት የማፍራት እና ፍትሐዊ ዳኝነት የማግኘት መብት: ከወቅታዊው የሕገ-ወጥ መሬትና ንብረት ማስመለስና ማፍረስ ጋር በተያያዘ

አሁን አሁን በተለያዩ የሃገራችን ክልሎች በተለይ ደግሞ በአዲስ አበባ ዙርያ በሚገኙ የኦሮሚያ ልዩ ከተሞች ላይ ከዕለት ወደዕለት በዜጎች የመዘዋወር መብት፤ንብረት የማፍራት፤ የእኩልነት እና ፍትህ የማግኘት ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በሕግ ማስከበር ሰበብ ሲጣሱ ማዬት የዕለት ተዕለት ተግባራዊ ኩነት እየሆነ መጥቷል፡፡

የዚህ አጭር ጽሑፍ መነሻ ነጥብም በሕግ ማስከበር ሰበብ ለረዥም አመታት ከማህበረሰቡ ጋር በመቀላቀል ሕገ-መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው ንብረት ያፈሩ ዜጎች ላይ በሕገ ወጥነት ሰበብ እየተወሰደ ያለውን ከገዛ ቤታቸውና ንብረታቸው የማፈናቀል እርምጃን በተመለከተ ዜጎች መብቶቻቸውን በሕግ አግባብ እንዴት ማስከበር እንዳለባቸው የሚያሳይ ፍኖተ ሕግ ነው፡፡

የህጉን ዝርዝር ነጥብ ከመመልከታቸን በፊት አሁን መሬት ላይ ያለው እውነትን በጨረፍታ ለመመልከት መሞከሩ ተገቢ ነው የሚል እምነት አለኝ፡፡ በቅርቡ በአዲስ አበባ ዙርያ የሚገኙ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞች መካከል የሰበታ ከተማ አስተዳደር፤ የቡራዩ ከተማ አስተዳደር፤ የለገጣፎ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም የሱሉልታ ከተማ አስተዳደር የከተሞቻቸውን የማስተር ፕላን ጋር ተቃራኒ የሆኑ እንዲሁም ቀድሞ ካሳ የተከፈላቸው እና በሕገ ወጥ መንገድ ከመንግስት እውቅና ውጭ ንብረት ያፈሩ ወይም በተለምዶ ወቅታዊ አጠራሩ ሕገ ወጥ ግንባታዎችን  አጭር የማስጠንቀቂያ ጊዜ በመስጠት ነዋሪዎቹ ለዓመታት ይኖሩበት የነበረውን በጉልበታቸውና በጥሪታቸው ያፈሩትን ሃብቶቻቸውን በሃይል ድርጊት እንዲፈርስ በማድረግ በተጨባጭ ዜጎች ከሃብት ንብረታቸው እንዲፈናቀሉ መደረጉ ለብዙ ቅሬታ መነሻ ነጥብ ሆኖ መገኘቱ ነው የዚህ ጽሑፍ መነሻ ነጥብ፡፡ በመሆኑም ዜጎች ተመሳሳይ ድርጊት ሲፈጸምባቸው በምን አግባብ መብቶቻቻውን ማስከበር እንደሚችሉ ከኢፌዴሪ ሕገ-መንግስት እና ከአዋጅ ቁጥር 721/2004 ጋር በማመሳከር ረጂ ናቸው ብዬ ያሰብኳቸውን ነጥቦች ለመዳሰስ እሞክራለሁ፡፡  

በቅድሚያ የኢፌዲሪ ሕገ መንግስት አንቀፅ 25 መሰረት ማንኛውም ሰው ልዩነት ሳይደረግበት በሕግ እኩል ያልተነጣጠለ እና አድሏዊ ባልሆነ መልኩ ጥበቃ እንደሚደረግለትና  እኩልና ተጨባጭ የሕግ ዋስትና የማግኘት መብት እንዳላቸው በማያሻማ ቋንቋ የማይገረሰሰ ሰብዓዊ መብት እንደሆነ ደንግጎ ይገኛል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ከጉዳያችን ጋር ተያያዥነት ባለው መልኩ በዚሁ ሕገ መንግስት አንቀፅ 32 ላይ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በመረጠው የሃገሪቱ አካባቢ የመዘዋዋርና የመኖርያ ቤት የመመስረት እንዲሁም በፈለገው ጊዜ ከሃገር የመውጣት ነፃነት እንዳለውና በአንቀጽ 40/7ም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በጉልበቱ ወይም በገንዘቡ በመሬት ላይ ለሚገነባው ቋሚ ንብረት ወይም ለሚያደርገው ቋሚ መሻሻል ሙሉ መብት አለው በማለት እርስ በርስ ተመጋጋቢ እና ተደጋጋፊ በሆነ መልኩ የዜጎችን ንብረት የማፍራትና በሃገራቸው በነፃነት የመዘዋወር ዲሞክራሲያዊ መብቶችን በዝርዝር ይጠቅሳል፡፡

Continue reading
  11086 Hits
Tags:

ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብሮ መኖር፤ አንድምታዎቹ እና ተግዳሮቶቹ

 

  1. መግቢያ

በተሻሻለው የኢትዮጲያ የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 1 መሰረት ህጋዊ ጋብቻ በተለያዩ ሰነ-ስረዓቶች ሊፈፀም ይችላል፡፡ እነሱም በክብር መዝገብ ሹም ፊት፣በሐይማኖት እና በባህል መሰረት የሚፈፀሙ የጋብቻ አይነቶች ናቸው፡፡ በተጨማሪም ጋብቻ ከላይ በተጠቀሱት በአንዳቸው ስነ-ስርዓቶች ቢፈፀም እንኳን ውጤቱም አንድ መሆኑን የዚሁ ህግ አንቀፅ 40 ያትታል፡፡ ህጋዊ ጋብቻ በተጋቢዎቹ ላይ ሁለት ዓይነት ውጤት ይኖረዋል፡፡ የመጀመሪያው በተጋቢዎች ግለዊ ግንኙነት ላይ የሚኖረው ውጤት ሲሆን፤ በስሩም የመከባበር ፣ የመተጋገዝና የመደጋገፍ ግዴታ ፣ ቤተሰብን በጋራ የመስተዳደር እና በጋራ አንድ ላይ የመኖር ግዴታዎችን ያቅፋል፡፡ ሁለተኛው ውጤት ደግሞ ጋብቻ በተጋቢዎች ንብረት ላይ የሚኖረው ውጤት ነው፡፡ ይህም ተጋቢዎች  ጋብቻቸውን በሚፈፅሙበት ጊዜ በግል የነበሯቸው ንብረቶች ወይም ከጋብቻ በኋላ በውርስ እና በስጦታ በየግላቸው ያገኙዋቸው ንብረቶች የግል ንበረታቸው ሆነው ሲቀሩ ከዚህ ውጪ ያሉ ንብረቶች በሙሉ የጋራ  ንብረት ይሆናሉ፡፡

ከጥንት ጀምሮ በወነዶችና በሴቶች መካከል ከነበሩ ማህበራዊ ግንኙነቶች መካከል ጋብቻ ሳይፈፀሙ እንደባልና ሚስት አብሮ መኖር አንዱ ነው፡፡ የዚህ አይነት ግንኙነት ምንም እንኳን ለቤተሰብ መመስረት ምክንያት  ቢሆንም በህግ አግባብ የሚደረግ ጋብቻ ሟሟላት ያለባቸውን ሁኔታዎችን ያላሟላ ስርዓት ነው፡፡ በሀገራችን እንደ ፍትሃ ነገስት ያሉ ጥንታዊ ጋብቻ ህጎች ጋብቻ ሳይፈፅሙ እንደ ባልና ሚስት አብሮ መኖሩን ቢያወግዝም የፍትሐብሔር ህግ እና በተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አስፈላጊነቱን በማመን ከለላ አድረግውታል፡፡

  1. አንድምታዎቹ

የተሸሻለው የኢትዮጲያ የቤተሰብ ህግ በአንቀፅ 98 ስር እንደሚያትተው ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብሮ መኖር ማለት አንድ ወንድ እና አንድ ሴት በህግ በሚፀና አኳኋን ጋብቻ ሳይፈፀሙ በትዳር መልክ የኖሩ ሲሆን ነው፡፡ የዚህ አይነቱ ግንኙነት በህግ አግባብ  ከሚደረጉ ጋብቻ ጋር ተቃራኒ ነው ተብሎ ሰለሚታሰብ እንደ “ፍተሃ ነገስት” ያሉ ጥንታዊ ህጎች እንደ ሃጥያት በመቁጠር ያወግዙት ነበር፡፡

ከጊዜ ወደ ጊዜ  በዓለማችን ከትዳር ውጪ የሚወለዱ ልጆችና የፍቺ መጠን ፍጥነት እየጨመረ ሲመጣ በተቃራኒው ደግሞ ከትዳር ውጪ አብሮ መኖር እየተለመደና እየበዛ መጥቷል፡፡ ይህም ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብሮ መኖርን ከለላ መስጠት አስፈላጊ እና የማይታለፍ መሆኑን ህጉ ተቀብሎታል::  እንደምክንያትነትም የኢትዮጲያ ህግ መንግስት አንቀፅ 34 ለቤተሰብ የሚሰጠው ከለላ ይነሳል፤ ይህም ልክ በህግ እንደሚደረግ ጋብቻ ሁሉ ጋብቻ ሳይፈፀም እንደ ባልና ሚስት አብሮ መኖርም ቤተሰብን ይመሰረታል፡፡

Continue reading
  16516 Hits

በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ መሠረት በተሰጠ የፍርድ ውሳኔ ላይ የሚቀርብ የአፈጻጸም ክስ በይርጋ ቀሪ ስለሚሆንበት የሕግ አግባብ

መግቢያ

አፈጻጸም ማለት አንድ መብቱ በፍርድ ውሳኔ እንዲከበር ለፍርድ ቤት ክስ ያቀረበ ሰው የፍርድ ውሳኔ አግኝቶ በፍርዱ መሰረት ሳይፈጸምለት ሲቀር ፍርዱ የተፈረደበት ወገን እንደ ፍርዱ እንዲፈጽም የሚገደድበት የሕግ ሥርዐት ነው፡፡ ይህ ስርዐት የሚመራውም በፍትሐብሔር ሥነ- ሥርአት ሕግ ቁጥር 375 ጀምሮ በተደነገጉ ድንጋጌዎች መሰረት ሲሆን በእነዚህ የሕግ ማእቀፎች ተንተርሶ መብቱ እንዲፈጸምልት ሚጠይቅ ወገን የፍርድ ባለመብት ሲባል እንዲፈጽም የሚገደደው ደግሞ የፍርድ ባለእዳ ተብሎ ይጠራል፡፡

Continue reading
  13231 Hits