Bank deposit method of proving Tax Evasion: the current litigation heresies

 

INTRODUCTION

Tax evasion is proscribed as crime under Art 125 of Federal Tax administration proclamation no-983/20081. Under this article, the law proscribes transgressions such as understatement of income (evasion of assessment), failure to file tax return with intent to evade tax and evasion of payment as offenses of tax evasion. To proof tax evasion, prosecutors must proof the existence of all ingredients of the offence, namely intent to defraud, affirmative act and evaded tax. Amongst ingredients of crime of tax evasion, the existence or otherwise of evaded tax is a typical one. To identify the nature and amount of evaded tax, one should make use of evidence. We can prove tax evasion both by direct and indirect evidences.

Proof is the establishment or refutation of an alleged fact by evidence. It’s the evidence or argument that compels the mind to accept an assertion as true. In its judicial sense; it encompasses everything that may be adduced at a trial, within the legal rules, for the purpose of producing a conviction in the mind of judge. Evidence is a thing (including testimony, documents and tangible objects) that tends to prove or disprove the existence of an alleged fact.

As indicated above, Tax evasion can be proved both by direct and indirect method of proof. This can be done by auditor which then appears in court of law as an expert witness.

Continue reading
  8208 Hits

ተጨማሪ ሃሳቦች ስለ ግብርና እድገትና የመሬት ፓሊሲና ሕግ

 

ከዚህ በፊት ባለው ጽሁፍ የሚከተሉትን ሃሳቦች አቅርቤ ነበር። በዋናነት የእነዚህ ሃሳቦች ተግባራዊነት ዉጤት፤ አሁን ተበጣጥሶ የሚገኘውን በገጠር መሬት ላይ የግብርና ውሳኔ መብት በአንጻራዊነት እንዲማከል ማድረጉ ነው። የግብርና ውሳኔ ማለት፥ በአንድ እርሻ ላይ ምን ላምርት? መቼ ላምርት? ምን አይነት እና መጠን ያለው ማዳበሪያ ልጠቀም? ምን አይነት የውሃ ቴኬኖሎጂ ልጠቀም? ምን አይነት ማረሻ፥ ማጨጃ፥ እና መውቂያ ልጠቀም? ምን አይነት የመሬትና አፈር ጥበቃና አስተዳደር አሰራሮችን ልከተል? እና የመሳሰሉት ናቸው። ከግብርና ውሳኔዎች ጋር የሚገናኙ የገበያ ውሳኔዎች ይኖራሉ። ለምሳሌ፤ ምን ያህል ምርቴን፥ መቼ፥ ለማን ልሽጥ? ምን ያህል ገንዘብ፥ ከማን፥ በምን ያህል ወለድ ልበደር? እነዚህና የመሳሰሉት ገበያ ነክ ውሳኔዎች ካነሳኋቸው ነጥቦች ጋር በቀጥታ አይገናኙም። እኔ ያነሳሁት የግብርና ውሳኔዎችን ነው።

አሁን ባለው ሁኔታ ሁለት አይነት መበጣጠሶች ይታያሉ። አንደኛው በቀደመው ጽሁፍ እንዳብራራሁት የመሬት መበጣጠስ አለ። በእርግጥ የመሬት መበጣጠሱ ሁኔታ እንደቦታው ይለያያል። እኔ ያደኩበትን አካባቢ ኢህአዴግ ከደርግ ነጻ እንዳወጣና ደርግን ተክቶ የሕዝብ አስተዳደር ሃላፊነትን ሲወስድ ካደረጋቸው ነገሮች አንደኛው መሬትን መልሶ ማከፋፈል ነው። ለምን? ምክንያቱም ጥቂት ‘አድሃሪያን’ ፍትሃዊ ባልሆነ መንገድ ጥሩ ጥሩ መሬቱን በብዛት ስለያዙት። እኔ በበኩሌ የመሬት ክፍፍልና ራሱን አልቃወምም። የኔ ነጥብ የዚህ መሬት ክፍፍልና የክፍፍሉ ስልት ስለፈጠረው የመሬት መበጣጠስ ነው። እንደገለጽኩት አንድ ገበሬ ከግማሽ ኳስ ሜዳ ያነሱ፥ ሶስትና አራት እርሻዎች ይኖሩታል። አንደኛው የጓሮ መሬት ሲሆን ሌሎች ከመኖሪያ ጎጆዉ በተለያየ አቅጣጫ በተለያየ እርቀት ይገኛሉ።  የመሬት መበጣጠስ የምለው ይሄን ነው። ሁለተኛው አይነት መበጣጠስ፥ የግብርና ውሳኔዎችን የመስጠት መብት መበጣጠስ ነው።

 

ኤኮኖሚ ኦፍ ስኬል (economy of scale)

የሁለት አይነት መበጣጠሶች፥ መጠን/ስኬል ከሚያስገኘው ጥቅም መጠቀም እንዳንችል ሆኗል። ብዙ አይነት የስኬል ጥቅሞች አሉ። አንደኛው ስኬል የሚባለውና ብዙ የሚታወቀው፥ ‘ኤኮኖሚ ኦፍ ስኬል’ ነው። ‘ኤኮኖሚ ኦፍ ስኬል’ ማለት በብዛት በማምረት የሚገኝ የነፍስ ወከፍ ወጪ መቀነስና የምርት መጨመር ነው።

Continue reading
  7682 Hits

አንዳንድ ጉዳዮች ስለ ግብርና እድገትና የመሬት ፓሊሲና ሕግ

 

 

የግብርና እድገትና የመንግስት ሚና

ግብርና የሃገራችን ወሳኝ የኤኮኖሚ ዘርፍ ነው። ምጣኔ ሃብት ምሁሮች እንደሚሉት፥ በቅጥርና አገራዊ ምርት የግብርናው ድርሻ እንዲቀንስ (በሌሎች ዘርፎች እንዲተካ)፥ ግብርናው በፍጥነት ማደግ አለበት። ለማነስ፤ በፍጥነት ማደግ።

የግብርና እድገት ምን ይጠይቃል? የመስኖ መሰረተልማት። የተሻሻለ ግብአት፥ ምርጥ ዘር፥ ማዳበሪያ፥ አረም ማጥፊያ። የምርት ገበያ። መሬት። ጉልበት። እውቀት። የገጠር መንገድ። የአርብቶ እና አርሶ አደሮች ትምህርት። የገጠር የጤና አገልግሎት። የገጠር የመጠጥ ውሃ አገልግሎት። የገጠር ሃይል አቅርቦት። የገጠር ሰላምና ደህንነት ማስከበር። የግብርና ግብይቶችን እና ድርጅቶችን መጠበቅ።

እነዚህን ሁሉ ማነው የሚያቀርበው? አሁን ባለበት ሁኔታ እነዚህን ሁሉ በዋናነት የሚያቀርበው መንግስት ነው። የፌዴራሉ መንግስት፥ የክልሎች መንግስታት፥ እና አካባቢያዊ መስተዳድሮች። የእነዚህ ሁሉ ዋና አቅራቢ መንግስት ሆኖ፥ እንዴት ነው ታዲያ ግብርናውን በፍጥነት ማሳደግ የሚቻለው? መንግስት እኮ ከግብርናው በተጨማሪ ሌሎች ሃላፊነቶችም አሉበት።

Continue reading
  9792 Hits

ደብዳቤው

ያው ጉባኤው የሚለውን ርእስ መኮረጄ ነው

እየመረጥክ ከዘገብክ የገለልተኝነት እና የእኩልነትን መርህ ጥሰሃል፡፡

/በበውቀቱ እስታይል/

ተከታዮ የመጀመሪያ አንቀፅ ለአገላለፅ ውበት እንጅ በጉዳዩ ላይ ያለኝ መቆጨት እንዳገላለፁ አለመሆኑ ይታወቅልኝ፡፡

የኢትዮጵያ ፕሮድካስቲንግ ባለስልጣል ለኢ ኤን ኤን የቴሌቪዚን ጣቢያ የፃፈውን ደብዳቤ እዚህ የፌስቡክ መንደር ውስጥ እያወቁ በድፍረት ሳያውቁ በስህተት እንደሆን እንጃ እጅጉን ሲተች ባይ ሆድ ባሰኝ፤ እንባየ መጣ ፤ቁጭት ልቤን መዘመዘው፤ አላስችል አለኝ በመጀመሪያ መብት የለውም አሉ ዝም አልኩኝ እነሱ ግን ይህን ሳያርሙ ሌላ ገደፉ እንዴት  ማለት ሲገባቸው ስህተት ነው ብለው ተናገሩ፡፡ በዚህ መች አብቅተው  እኩልነት ተጥሷል እል ብለው የሀሳብ ነጻነት ተደፍሯል ብለው አረፉ እንግዲህ ይህን ዝም ብሎ ማለፍ እንደምን ይቻላል፡፡ ምእመናን  አሳምራችሁ እንደምታወቁት የመገናኛ ብዙሃን መሰረት ገለልተኝነት እና በእኩልነት መርህ መገዛት አይደለምን? የመረጃ ነጻነት አደጋ ላይ የወደቀው እነዚህን መርሆች በጥብቅ ባለመከበራቸው መሆኑስ ይዘናጋል ምእመናን፡፡ እነዚህን መርሆች አለማክበርስ የመገናኛ ብዙሃንን ሃላፊነት በቅጡ ካለመረዳት የመጣ አይደለምን? መቼም ይህን ለማወቅ በዘርፉ ሙህር መሆን ይጠይቃል እያልኩ አይደለም ጎበዝ አስተዋይ ለሆነ ሰው ባለፈው ግዜ ሚዲያዋች የሰሩትን በማየት  ሚዲያዎቹ አድር ባይ የመንግስት አፈ ቀላጤ የነበሩ መሆናቸውን  መረዳት ይቸግረዋል ወይ ምእመናን? ስለዚህ እንደኔ እንደኔ ይን ጉዳይ በቀላሉ ልናልፈው አይገባም ባይ ነኝ፡፡

Continue reading
  7237 Hits

የብሮድካስቲንግ ቁጥጥር/ሪጉሌሽን እና የባለሥልጣኑ ደብዳቤ

ስለሪጉላቶሪ መሳሪያዎች መግቢያ

ዛሬ የብሮድካስቲንግ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ለሁለት ብሮድካስተሮች ጽፈውታል የተባለ ደብዳቤ በፌስቡክ መለጠፉን ተከትሎ የተለያዩ አስተያየቶች እየተስተናገዱ ነው። በደብዳቤው ብሮድካስተሮቹ ለምን የቅዳሜውን የድጋፍ ሰልፍ እንዳላስተላለፉ መረጃ በተጠቀሰው ቀን ይዘው በመምጣት ከባለሥልጣኑ ጋር እንዲወያዩ ያሳስባል። ባለሥልጣኑ ይህን ደብዳቤ “ሊመልሰው፣ ይቅርታ ሊጠይቅ ይገባል”፣ እና የመሳሰሉት አስተያየቶች በመሰጠት ላይ ይገኛሉ። የዚህ ጽሑፍ አቅራቢ ምንም እንኳን በሚዲያ ተቋማት ዙሪያ የግሌ ጠቅላላ አስተያየትና እምነት ቢኖረኝም የብሮድካስቲንግ አዋጁን አስመልክቶ ያለኝን ግንዛቤና አረዳድ እንደሚከተለው አካፍላለሁ።

እንደሚታወቀው ብሮድካስቲንግ ባለሥልጣን ተቆጣጣሪ አካል ወይም ሪጉሌተር ነው። በመሆኑም ለመግቢያ ያህል በጠቅላላው በተለያዩ ማህበራዊና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮች የተለያዩ ሪጉላቶሪ አካላት የመቆጣጠር ስልጣናቸውን ምን ዓይነት የፓሊሲ ወይም የሪጉላቶሪ መሳሪያዎችን በመጠቀም እንደሚያሳኩ ባጭሩ እንመልከት። የተለያዩ ሪጉላቶሪ አካላት የሚከተሉትን ስምንት ዋና ዋና መሳሪያዎች በአማራጭ ወይም በስብጥር ይጠቀማሉ።

አንደኛው የፈቃድ ሥርዓት መዘርጋት ነው። በአንድ የተለየ ተግባር ላይ መሰማራት የሚፈልግ አካል፣ ወደ ተግባር ከመግባቱ በፊት ከሚመለከተው ተቆጣጣሪ/ሪጉሌተር ፈቃድ እንዲያወጣ ይጠበቅበታል። የፈቃድ ሥርዓት ከማሳወቅ ሥርዓት ይለያል። ምክንያቱም ፈቃዱ ሊከለከል ይችላል። ፈቃዱን ለማግኘት አመልካቹ ማሟላት ያለበት ቅድመ ሁኔታዎች በሕግ ይቀመጣሉ። እነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች የተለያዩ መልኮች ሊይዙ ይችላሉ፤  የዜግነት ወይም የነዋሪነት ግዴታ፣  የትምህርት ወይም የብቃት ደረጃ፣ የድርጅት ዓይነት (ለምሳሌ በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ለመሰማራት፣ የግድ አክሲዮን ማህበር ማደራጀት ያስፈልጋል ሊባል ይችላል)፣ የገንዘብ አቅም፣ ፈተና፣ ልምድ፣ እና የሃላፊነት መድን (በሥራው የተነሳ በሌሎች አካላት ላይ ጉዳት ቢያደርስ፣ ጉዳቱን የሚክስ መድን አስቀድሞ እንዲገባ ማድረግ።

ሁለተኛው የሪጉላቶሪ መሳሪያ የጥራት ቁጥጥር ነው። አንዴ ፈቃድ አግኝቶ ወደ ተግባር የገባ አካል፣ የሚያቀርባቸው ምርትና አገልግሎቶች ሊያሟሏቸው የሚገባቸውን የጥራት ደረጃ ቁጥጥር ማድረግ። የጥራት ቁጥጥር ሁለት ዓይነት ዋና ዋና የጥራት ስታንዳርዶችን በመጠቀም ይከናወናል። አንደኛው የተግባሩ ውጤት ወይም ፍሬ ሊያሟላው የሚገባ የጥራት መለኪያ በወለል ወይም በጣሪያ መልክ ሊቀመጥ ይችላል። ለምሳሌ የታሸገ ውሃ ሊኖረው የሚገባው ከፍተኛ የአርሰኒክ መጠን በተቆጣጣሪው አካል በሕግ ሊደነገግ ይችላል። ሁለተኛው የጥራት ስታንዳርድ ዓይነት የግብአት ወይም ቴክኖሎጂ ወይም የሂደት ጥራት ነው። በዚህኛው መሠረት የተግባሩ ውጤት ወይም ፍሬ ሊያሟላው የሚገባ የጥራት ደረጃ ሳይሆን ትኩረት የሚደረገው፣ ውጤቱን ወይም ፍሬውን ለማምረት ወይም ለማቅረብ አምራቹ ወይም አቅራቢው ሊጠቀመው የሚገባ የግብአት፣ ቴክኖሎጂ፣ ወይም ሂደት ዓይነትና ጥራት በሪጉላቶሪ አካሉ ወይም በሕግ አውጪው በሕግ ሊደነገግና ክትትል ሊደረግበት ይችላል። ሁለቱንም ዓይነት ስታንዳርዶችን አሰባጥሮ መጠቀም ቢቻልም ብዙ ጊዜ ሁለተኛው ዓይነት ስታንዳርድ የምንጠቀመው፣ የመጀመሪያውን ዓይነት ስታንዳርድ ማውጣት ወይም ክትትል ማድረግ አስቸጋሪ በሚሆንበት ጊዜ ነው። ለምሳሌ የትምህርት ተቋማትን የአገልግሎት ጥራት ለመለካት የስራቸው ፍሬ የሆኑትን ተማሪዎቻቸው ሊያሟሏቸው የሚገቡ የጥራት መለኪያዎችን ማስቀመጥ ከባድ ስለሆነ የትምህርት ተቋማቱ ሊጠቀሙባቸው በሚገቡ ግብአቶች (ለምሳሌ የትምህርት መጽሐፍት፣ የመማሪያ ክፍሎች፣ የተማሪና የአስተማሪ የቁጥር ምጣኔ)፣ ሂደቶችና ቴኬኖሎጂዎች ላይ ትኩረት ይደረጋል። እንዲሁም በከተሞች የሚቀርቡ የቧንቧ የመጠጥ ውሃን አስመልክቶ የመጀመሪያውን ዓይነት ስታንዳርድ ማውጣትቢቻልም፣ ክትትሉ ግን እጅግ አስቸጋሪ ስለሚሆንን እና አስተማማኝነቱም ዝቅተኛ ስለሚሆን በዋናነት በሁለተኛው ዓይነት የጥራት ስታንዳርድ ስራ ላይ ሲውሉ ይስተዋላል። ሊታወቅ የሚገባው ጉዳይ ሁለተኛው ዓይነት የሪጉላቶሪ መሳሪያ ለኪራይ ሰብሳቢነት የተጋለጠ ከመሆኑ በተጨማሪ፣ አማራጭ ቴክኖሎጂዎች፣ ግብአቶች፣ ወይም ሂደቶች እንዳይዳብሩ ወይም እንዲከስሙ ማድረጉ ነው።

Continue reading
  7912 Hits

አንዳንድ ነጥቦች ስለአዲሱ የመንገድ ትራፊክ መቆጣጠሪያ ማሻሻያ ደንብ ቁጥር 395/2009

 

በየካቲት ወር 2008 ዓ/ም መዲናችን አዲስ አበባ ላይ የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 208/2003 ዓ/ም የሪከርድ አያያዝ ትግበራ መጀመሩን ተከትሎ የታክሲ የአሽከርካሪዎች ስራ የማቆም አድማ ነበረ፡፡ በዚህም መሰረት ተግባራዊ መደረግ ተጀምሮ የነበረው የሪከርድ አያያዝ ተግባራዊነቱ እንዲቋረጥ ተደርጎ ከአሽከርካሪዎች እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ከተደረገ በኋላ የደንቡ መሻሻል አስፈላጊነት ታምኖበት ደንቡ እንዲሻሻል ተደርጓል፡፡ በወቅቱ በአሽከርካሪዎች በኩል ሀገሪቱ ባላት የትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ብቃት ደረጃ፣ የመንገድ መሰረተ ልማት ችግሮች፣ ልል የሆነ የትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ተጠያቂነት፣ የተቆጣጣሪዎች ስነምግባር ችግር እንዲሁም ከብዙ ተያያዥ ጉዳዮች ጋር በተገናኘ በደንብ ቁጥር 208/2003 ዓ/ም ላይ ሪከርድን የሚመለከተው ክፍል ወደ ተግባር የሚገባ ከሆነ አስቸጋሪ ሁኔታዎች እንደሚፈጠርባቸው ለስራ ማቆም አድማው የተሰጡት ምክንያቶች ነበሩ፡፡ ደንቡ በ2003 ዓ/ም እንደመውጣቱ እሪከርድን የሚመለከተው ክፍል ተግባራዊ መደረግ የጀመረው በ2008 ዓ/ም መሆኑ በራሱ የህግ አስፈጻሚውን ቸልተኝነት የሚያሳይ ሲሆን ደንቡን በመተግበር ረገድ ቀድመው የጀመሩ እንደ አማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ያሉትን ደግሞ በክልላቸው የሚንቀሳቀሱትን አሽከርካሪዎች በሀገሪቷ ውስጥ ካሉ ሌሎች አሽከርካሪዎች በተለየ ሁኔታ ተጎጂ ሲያደርጋቸው ነበር፡፡ ይህ ጽሁፍ ደንቡ የተሻሻለበትን ምክንያቶች አግባብነት፣ ማሻሻያው ውስጥ የተጨመሩ እና ማስተካከያ የተደረገባቸውን አንቀጾች እንዲሁም የማሻሻያውን አንድምታ በተወሰነ መልኩ ለመዳሰስ ይሞክራል፡፡

የደንብ ቁጥር 208/2003 መሻሻል አስፈላጊነት

የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ የሚንስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 208/2003 ዓ/ም / ከዚህ በኋላ "ደንቡ" እያለ ይቀጥላል / በርከት ያሉ ድንጋጌዎች ከያዙ እና የመንገድ ትራፊክ ፍሰትን ለማሳለጥ ከሚያስችሉ መሰረታዊ ህጎች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ለዚህ ደንብ መሻሻል ገፊ ምክንያት የሆነው ከደንቡ የሪከርድ ክፍል ጋር በተያያዘ የተነሳው ተቃውሞ ቢሆንም ከጊዜ ቆይታ እና የሁኔታዎች ተለዋዋጭነት አንጻር እንዲሁም ደንቡ ቀድሞውንም ሲወጣ ከነበሩበት የህግ አወጣጥ ችግሮች ጋር በተያያዘ መሻሻል የነበረበት በመሆኑ የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ማሻሻያ ደንብ ቁጥር 395/2009 ዓ/ም /ከዚህ በኋላ "ማሻሻያው" እያለ ይቀጥላል /መውጣቱ ተገቢነት ያለው ነው፡፡ ይህ ደንብ ሲሻሻል ከግምት ውስጥ ሊያስገባ የሚገባው መሰረታዊ ነጥብ ቢኖር ሀገሪቷ በአሁኑ ሰአት ከየትኛውም አደጋ በላይ በአመት ከ5000 /አምስት ሺ/ የሚበልጥ የሰው ሂወት እየቀጠፈ እና ከባድ የሆነ የንብረት ውድመት እያስከተለ ያለውን የትራፊክ አደጋን መቀነስ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር አብዛኞቹ የትራፊክ አደጋዎች የሚደርሱት በአሽከርካሪዎች ጥፋት መሆኑ እየታወቀ ሪከርድን የሚመለከተው የህጉ ክፍል የተሻሻለበት መንገድ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ከማስገባት ይልቅ በነበረው ተቃውሞ ተጽእኖ ስር ሆኖ የተሻሻለ ነው፡፡ ይህንን ከታች በዝርዝር እንመለከተዋለን፡፡ ሪከርድን ከሚመለከተው ክፍል ውጪ የተሻሻለው የደንቡ ክፍል ከነ ክፍተቶቹም ቢሆን ከዚህ ቀደም በደንቡ ላይ ግልጽነት የጎደላቸውን ድንጋጌዎች ለማስተካከል ከመሞከሩም በላይ አዳዲስ አንቀጾችን በመጨመር የደንቡን ክፍተቶች ጥሩ በሚባል መልኩ አስተካክሏል፡፡

መሰረታዊ ማሻሻያ የተደረገባቸው እና አዲስ የተጨመሩ ድንጋጌዎች በከፊል

Continue reading
  20552 Hits

“ለእግረኛ ቅድሚያ በመከልከል…” ከሕግ አንጻር ሲታይ


በሀገራችን እጅግ አሳሳቢ እና አነጋጋሪ ከሆኑት የወንጀል ድርጊቶች መካከል በአሽከርካሪዎች የሚፈጸመው ወንጀል ቀዳሚውን ሥፍራ ይይዛል ለማለት ይቻላል፡፡ ከትራፊክ ፖሊስ ዕለታዊ ሪፖርት በየዕለቱ እንደምንሰማው በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ እንኳን ያለበትን ሁኔታ ብንመለከት በንብረትና በሰው ላይ፣ ቢያንስ በአንደኛው ላይ አደጋ ሳይደርስ የዋለበት ቀን የለም ለማለት ይቻላል፡፡ የአደጋ ዜናው በ24 ሰዓት፣ በወርና በዓመት ስሌት ሲነገር ስንሰማው እጅግ አሳሳቢ ነገር ነው፡፡ በትርፊክ ፖሊስ የዘወትር ሪፖርት እንደምንሰማውም ብዙውን ጊዜ አደጋው የደረሰው ለእግረኛ ቅድሚያ መከልከል በአሽከርካሪ ጥፋት መሆኑን መዘገቡ የተለመደ ነው፡፡


በዚህ ጽሁፍ ፍተሻ የምናደርግባቸው ነጥቦች አሽከርካሪ አጥፍቷል ወይም በቸልተኝነት ወንጀል ፈጽሟል የሚባለው መቼ ነው; የወንጀል ድርጊቱን ለመከላከል/ለመቀነስ እግረኞችስ ምን ዓይነት ግዴታ አለባቸው; አደጋውን እያባባሱ ያሉት ዋና ዋና ሁኔታዎች ምንድን ናቸው; የሕግ ስርዓታችንና በፍርድ ቤቶች የተሰጠው ቦታስ ምን ይመስላል; የሚሉትንና ተያያዥነት ያላቸውን ነጥቦች ናቸው፡፡


ወደ ዝርዝር ነጥቦች ከመግባታችን በፊት ጭብጡን በፍርድ ቤቶች በታዩና ፍርድ በተሰጠባቸው ጉዳዮች ለመደገፍ ይቻል ዘንድ በቅድሚያ ሶስት ዐቃቤ ህግ የወንጀል ክስ ያቀረበባቸውንና ፍርድ ቤት ፍርድ የሠጠባቸውን ናሙና ጉዳዮችን በአጭሩ እንመልከት፡፡


ጉዳይ አንድ፡ ጊዜው ነሐሴ ወር 2002 ዓ.ም ነው፡፡ በ70ዎቹ የዕድሜ ክልል የሚገኙት አዛውንት ከኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ለሥራ ጉዳይ በማለት ወደ አዲስ አበባ ይመጣሉ፡፡ አዛውንቱ ሥራ ያሉትም በመንገድ ላይ ገንዘብ ለምኖና አጠራቅሞ ወደመጡበት መመለስ ነበር፡፡ ሥራቸውንም በተክለሃይማኖት አካባቢ ባለው አስፋልት ላይ ቀኑን እንደ ሸማኔ መወርወሪያ ከግራ ወደቀኝ በመመላለስ በትጋት ሲያከናውኑ መዋል ጀመሩ፡፡ የልመና ገንዘቡም በዋናነት ከአሽከርካሪዎች እየተሰበሰበና እየተጠራቀመ ነው፡፡ ይሁንና በአንዲቷ ጎደሎ ቀን ከአንዱ አሽከርካሪ ሳንቲም ተቀብለው በሌላኛው ተሽከርካሪ ተከልለው መንገዱን ከቀኝ ወደ ግራ ሲያቋርጡ ከአንድ የጭነት ተሽከርካሪ አይሱዙ ጋር ይጋጩና ከአስፋልቱ ላይ ይወድቃሉ፡፡ አዛውንቱም የሰበሰቡትን ገንዘብ የት እንዳስቀመጡት ሳይናገሩና እንዳሰቡትም ወደ መጡበት ሳይመለሱ እንደወጡ ቀሩ፡፡ የትራፊክ ፖሊስ የአዛውንቱ ሞት በአሽከርካሪ ጥፋት ለእግረኛ ቅድሚያ መከልከል የተፈጸመ መሆኑን በመግለጽ ፕላኑን አዘጋጅቶና ሪፖርቱን ጽፎ ጉዳዩን ለዐቃቤ ህግ አስተላለፈ፡፡ ዐቃቤ ህግም በሪፖርቱ መሠረት ክሱን በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀጽ 543/2/ ተላልፎ በቸልተኝነት ሰው መግደል የወንጀል ክስ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቀረበ፡፡


ጉዳይ ሁለት፡ ጊዜው በስድስተኛው ወር በ2002 ሲሆን አሽከርካሪዋ ሴት ነች፡፡ አሽከርካሪዋ ባለቤቷ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለይ የነበራቸውን ጅምር ቤት በመሸጥ ሁለት ህጻናት ልጆቿን ለማሳደጊያ ይሆናት ዘንድ በማሰብ አንድ ትንሽ ላዳ ታክሴ በመግዛት ሹፌር ቀጥራ ገቢ ማግኘት ጀመረች፡፡ ሴትዮዋ ያላት የመንጃ ፈቃድ 2ኛ ሆኖባት እንጅ 3ኛ ቢሆን ኖሮ ታክሲዋን ራሷ በማሽከርከር ገቢዋን የተሻለ የማድረግ ሀሳቡ ነበራት፡፡ ሀሳቧን ከግብ ለማድረስም 3ኛ ደረጃ አሽከርካሪነት የሙያ ፈቃድ ለማግኘት ልምምድ ጀመረች፡፡ ነገር ግን ልምምዱ በተፈቀደላቸው አሰልጣኞችና የመለማመጃ ተሸከርካሪዎች ብቻ የተወሰነ አልነበረም፡፡ ከዚህ አልፎ በራሷ ታክሲ እና በሹፌሯ አለማማጅነት ልምምዷን በኮተቤ አስፋልት ቀጠለች፡፡ ይሁንና እንኳን በ3ኛ ደረጃ መንጃ ፈቃድ የሚነዳውን ተሸከርካሪ ማሽከርከር ይቅርና ችሎታዋ በ2ኛ ደረጃ ለሚሽከረከረውም አጥጋቢ አልነበረምና ከኋላ በተከተላትና ድምጹን በሰማቸው ከባድ ተሸከርካሪ ምክንያት በድንጋጤ ከመንገዱ በመውጣት በከባድ ቸልተኝነት የመንገዳቸውን ቀኝ ጠርዝ ይዘው ይጓዙ ከነበሩት ሴት ህጻናት ተማሪዎች መካከል በአንዷ ላይ የሞት አደጋ፣ በሁለቱ ላይ የአካል ጉዳት አደጋ በማድረስ ግቢ ጥሳ በመግባት በንብረትም ላይ ጉዳት የማድረስ ድረጊት ይፈጸማል፡፡ የትርፊክ ፖሊስም አደጋው የደረሰው ከመንጃ ፈቃድ ደረጃ ውጭ ደንብ በመተላለፍ፣ በአሽከርካሪ ጥፋት ለእግረኛ ቅድሚያ መከልከል የተፈጸመ መሆኑን በመግለጽ ፕላኑን አዘጋጅቶና ሪፖርቱን ጽፎ፣ አለማማጁንም ከምስክሮች መካከል አድርጎ (እያለማመደ የነበረ መሆኑን ክዷል) ጉዳዩን ለዐቃቤ ህግ አስተላለፈ፡፡ ዐቃቤ ህግም በሪፖርቱ መሠረት ክሱን በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀጽ 543/2/ እና 559/2/ ተላልፎ በቸልተኝነት ሰው መግደል እና የአካል ጉዳት ማድረስ እንዲሁም በመንጃ ፈቃዱ ደንብ በመተላለፍ ሦስት የወንጀል ክሶችን በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቀረበ፡፡ 

Continue reading
  9225 Hits

የታክስ ይግባኝ ኮሚሽን እና የአዲስ አበባና ድሬዳዋ ከተሞች ራስን በራስ የማስተዳደር መብት

 

የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 እራስን በራስ የማስተዳደር መብትን ከአዲስ አበባ እና ከድሬዳዋ ከተሞች ላይ የገፈፈ ስለመሆኑ እና የመፍትሔ አቅጣጫዎቹ፡፡  

እራስን በራስ የማስተዳደር መብት የፌዴራል ሥርዓትን በሚከተሉ አገሮች የተለመደ አሰራር ሲሆን በዋናነትም ክልሎች ወይም ራስ ገዝ አስተዳድሮች ከፌዴራል መንግስቱ ተፅእኖ ውጪ የራሳቸው ሕግ አውጪ፤ ሕግ ተርጓሚ (የዳኝነት አካል) እንዲሁም የህግ አስፈፃሚ አካላት ኖሯቸው በcheck and balance መርህ ክልላቸውን ወይም አካባቢያቸውን የሚያስተዳድሩበት ቁልፍ ቃል-ኪዳናቸው ነው፡፡

ይህ እራስን በራስ የማስተዳደር መብት በኢትዮጵያ ሕገ መንግስት አንቀፅ 39(3) ለኢትዮጵያ ብሄር፤ ብሄረተሰቦች፤ ሕዝቦች የሰጠ እንዲሁም በአንቀፅ 49(2) ላይ ደግሞ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ ስልጣን እንዳለው የሚደነግግ  ሲሆን በአንፃሩ የድሬዳዋ አስተዳደር ግን ይሄን መብት ሕገ-መንግስቱ እንደነፈገው የሚታወቅ ግልፅ ሐቅ ነው፡፡

በመሆኑም የዚህ ጽሑፍ ዋናው ትኩረት ከዳኝነት አካላት ውስጥ አንዱ ከሆነው የድሬዳዋ  እና የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድሮች የግብር ይግባኝ ሰሚ ጉባኤን የዳኝነት ስልጣን ከሕገ-መንግስቱ (እራስን በራስ ከማስተዳደር መብት ለአዲስ አበባ ከተማ ከተሰጠ መብት አንፃር)፤ ከፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጁ እና ከተሞቹ ከሚመሩባቸው አዋጆች አንፃር ያሉ የሕግ ጉዳዮችን/ችግሮችን በንፅፅር በወፍ በረር በመዳሰስ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ማመላከት ነው፡፡   

Continue reading
  10350 Hits

የንግድ ፈቃድን ማከራየት በወንጀል ያስቀጣል?


በሀገራችን የንግድ ሕግ ሥርዓት መሠረት ነጋዴነት ምን መብቶችና ግዴታዎች አሉበት? ለመሆኑ አንድ ነጋዴ በሥሙ ያወጣውን የንግድ ፈቃድ ለሌላ ሰው ማከራየትና በኪራይ ውል ማስተላለፍ ይችላል? አከራይቶ ቢገኝስ በወንጀል ሊያስከስሰውና ሊያስቀጣው ይችላልን? የነጋዴነት መብቶችና ግዴታዎች በየትኞቹ ህግጋት ይገዛል? የነጋዴዎችን መብትና ግዴታዎች በዋናነት የሚመለከቱት ሕግጋት በአዋጅ ቁጥር 166/1952 የወጣውና ከመስከረም 1 ቀን 1953 ዓ.ም ጀምሮ በሥራ ላይ የዋለው የንግድ ሕግ፣ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅና ደንብ እና ግብርን የሚመለከቱ ሕጎች ሲሆኑ ሌሎች ህግጋትም እንደ የውል ሕግ፣ የኪራይ ሕግ፣ የአሠሪና ሠራተኛ ሕግ፣ የወንጀል ሕግ.... በነጋዴዎች ላይ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የሚያስከትሉት መብትና ግዴታዎች ይኖራሉ፡፡ በዚህ አጭር ጽሁፍ ስለ ነጋዴዎች መብትና ግዴታዎች በዝርዝር ለመጻፍ የማይቻል በመሆኑ ጽሁፉ ለመዳሰስ የሚሞክረው በነጋዴነት የተመዘገበ የንግድ ፈቃድ የተሰጠው ሰው የንግድ ፈቃዱን ለሦስተኛ ወገን በኪራይ ውል ማስተላለፍ ህጋዊ መብት አለው ወይስ የለውም? የሚለውን ጭብጥ ነው፡፡


ጽሁፉን በተጨባጭ የፍርድ ቤት ጉዳይ ለመደገፍ ይቻል ዘንድ የሚከተለውን አንድ ጉዳይ እንመልከት፡-
አቶ ተፈራ… (ስሙ ለጽሑፉ ሲባል የተቀየረ) ባለትዳርና የልጆች አባት ሲሆን በባለቤቱ ሥም በቅድመ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት አገልግሎት በሚል ዘርፍ በአፀደ ሕጻናት አገልግሎት የንግድ ፈቃድ የወጣበትን ድርጅት ለማስተዳደር የውክልና ስልጣን የተሰጠው በመሆኑ በራሱ እየሠራበት እያለ በጤና እና በሌሎች ምክንያቶች ድርጅቱን የማስተማር ልምድ ካለው ሰው ጋር በኪራይ ለማሠራት ተስማምተው በጽሑፍ የኪራይ ውል አስተላለፈው፡፡ ይሁንና ተከራይው ግለሰብ ድርጅቱን እንደ ባለቤቱ/ወኪሉ ሆኖ ለመምራት ባለመቻሉ የተማሪዎች ቁጥር እየቀሰነበትና ኪሣራ እየደረሰበት በመምጣቱ በመሐከላቸው አለመግባባት በመፈጠሩ በፍትሐብሔሩ አለመግባባት ጉዳዩ ወደ ፍ/ቤት ደረሰ፡፡ ተከራይው ግለሰብ የንግድ ፈቃዱን ተከራይቶ መሥራቱን ለተቆጣጣሪ አካላት መረጃ በመስጠቱ አቶ ተፈራ በፖሊስ ለምርመራ እንደሚፈለግ ጥሪ ደርሶት የወንጀል ምርመራ ተደረገበት፡፡ ጉዳዩ በምርመራ ብቻ ሳያበቃ በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ቁጥር 686/2002 ድንጋጌዎችን በመተላለፍ የንግድ ፈቃድን ማከራየት ወንጀል ፈጽመሃል በማለት በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክስ ቀርቦበት በወንጀል ተከሳሽ ሳጥን ለመቆም በቃ፡፡ ተከሳሽ ክሱ ደርሶት ስለ ድርጊቱ በፍርድ ቤቱ ሲጠየቅ ድርጅቱን ማከራየቱን ሳይክድ፣ ያከራየሁት መብቴን ተጠቅሜ የድርጅቱን መልካም ዝና እንጅ የንግድ ፈቃዱን ብቻ ነጥዬ ለሌላ ሰው ያላከራየሁ በመሆኑ ጥፋተኛ አይደለሁም በማለት ክርክሩን አቅርቧል፡፡ ከንግድ ሕጉና ከንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጁ አንጻር ተከሳሽ በወንጀል ጥፋተኛ ሊሆን ይችል ይሆን? በህጉ መሠረት የንግድ ፈቃድን ማከራየት የንግድ መደብርን ከማከራየት ተለይቶ የሚታይ ነውን? በተከሳሽ ላይ የቀረበውን ክስና የክርክሩን ውጤት ወደኋላ እናቆየውና በቅድሚያ ለጉዳዩ አግባብነት ያላቸውን የህጉን ድንጋጌዎች እንመልከት፡፡


በንግድ ሕጉ ስለ ነጋዴዎችና ስለ ንግድ መደብሮች በሚለው ክፍል በአንቀጽ 5 ሥር ስለ ነጋዴነት ትርጉም ሲገልጽ “ነጋዴዎች” የሚባሉት ሰዎች የሞያ ሥራቸው አድርገው ጥቅም ለማግኘት ሲሉ በህጉ የንግድ ሥራዎች ተብለው የተቆጠሩትን ሥራዎች የሚሠሩ ሰዎች መሆናቸውን ተደንግጓል፡፡ በንግድ ሕጉና በንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጁ መሠረት የንግድ ሥራዎች ተብለው ከተዘረዘሩት ሥራዎች መካከል ለምሳሌ፡- ጥሬ ዕቃዎችን ወይም ምርቶችን ገዝተው/አምርተው የሚሸጡ፣ ህንጻዎችን/ዕቃዎችን የሚያከራዩ፣ የሆቴል፣ የምግብ ቤት፣የቡና ቤት፣ የመጠጥ ቤት፣የመኝታ ቤት… አገልግሎት የሚሰጡ፣ የትምህርት አገልግሎት የሚሰጡ፣ የላኪነትና አስመጭነት፣ የጉምሩክ አስተላላፊነት…ወ.ዘ.ተ ሥራ በንግድ መዝገብ ተመዝገበውና የንግድ ፈቃድ አውጥተው የሚሠሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ሰዎች የሚለው እንደአግባብነቱ የተፈጥሮ ወይም የሕግ ሰውነት የተሰጣቸውን ሁሉ የሚወክል ነው፡፡ 
በንግድ ህጉ አንቀጽ 100 በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ የንግድ ሥራ የሚሠራ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ወይም የውጭ አገር ሰው ወይም የንግድ ማህበር በመዝገብ መግባት እንዳለበት በአስገዳጅነት ተደንግጓል፡፡ በአንቀጽ 105 እንደተደነገገው አንድ ነጋዴ ለመመዝገብ ማመልከቻ ሲያቀርብ ከሚገልጻቸው መረጃዎች መካከልም የቤተዘመድ ስሙ፣ የተወለደበት ቀንና ቦታ፣ ዜግነቱ፣ የግል አድራሻው፣ የጋብቻ ሁኔታ፣ የንግዱ ዓላማ፣ የንግዱ ሥም፣ ሥራ አስኪያጅ ካለው ስሙንና ሥልጣኑን ይገኙበታል፡፡ እነዚህ ሁኔታዎች በንግድ መዝገብ የመግባታቸው አስፈላጊነት የንግድ ሥራ ፈቃድ በግለሰቡ ማንነት የተወሰነ እንዲሆን ታስቦ ይሆን? የሚል ጥያቄ ያስነሳል፡፡ በንግድ ህጉ አንቀጽ 112 መነገድን ስለመተው በተደነገገው መሠረት ደግሞ ማንኛውም የተመዘገበ ነጋዴ የተመዘገበውን የንግድ ሥራውን በማናቸውም ምክንያት በተወ ጊዜ ወይም የንግዱን መደብር በአከራየ ጊዜ በሁለት ወር ውስጥ ከመዝገቡ እንዲሰረዝ ማመልከቻ ማቅረብ እንደሚገባው ተደንግጓል፡፡


የነጋዴነት ሥራ የቫት(የተጨማሪ እሴት ታክስን ጨምሮ) ከግብር ክፍያና በሽያጭ መመዝገቢያ ማሽን ደረሰኝ ግብይት የማከናወን ግዴታ ፣ ከሦስተኛ ወገኖች ወይም የብድርና ሌላ ውል ተዋዋዮች መብት፣ ከወንጀል ኃላፊነት፣ ከሠራተኞች መብት እና ከሌሎች ጉዳዮች ጋር ዘርፈ ብዙ የመብትና ግዴታ ግንኙነት ያለው መሆኑ ይታወቃል፡፡ ከዚህ አንጻርም የንግድ ፈቃድን በማከራየት የንግዱ ሥራ ቢሠራ በአገልግሎቱ ጥራት፣ በተገልጋይው መብት፣ በንግዱ ቁጥጥር፣ በግብር ክፍያ፣ በተጠያቂነትና በሌሎች ሁኔታዎች ላይ የሚያመጣው አሉታዊ ውጤት ይኖረዋልን? የሚለውን ሥጋቶች ለመከላከል የንግድ ፈቃዱን ላልተፈቀደለት ሰው በኪራይ እንዳይተላለፍ በሕግ መከልከሉ መፍትሔ ይሆናል የሚል ሃሳብ ያጭራል፡፡


በአሁኑ ወቅት በሥራ ላይ ያለው የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ቁጥር 686/2002 ከመውጣቱ በፊት ከ13 ዓመታት በላይ በሥራ ላይ በነበረው አዋጅ ቁጥር 67/1989 ማንኛውም ሰው በንግድ መዝገብ ሳይመዘገብ የንግድ ሥራ መሥራት እንደማይችል፣ የንግድ ድርጅት ለሌላ ሰው በሚተላለፍበት ጊዜ የቀድሞው ፈቃድ ተመላሽ ተደርጎ ድርጅቱ የተላለፈለት ሰው በስሙ ፈቃድ ማውጣት እንዳለበት የተደነገገ ሲሆን በአዋጁ መሠረት በወጣው ደንብ ቁጥር 13/1989 መሰረትም ከአዋጁ በተመሳሳይ ሁኔታ ነጋዴው የቅርብ ጊዜ ፎቶ ግራፉንና ሌሎች ዝርዝር ሁኔታዎችን አሟልቶ መመዝገብ እንዳለበት በአስገዳጅነት ተደንግጓል፡፡ 

Continue reading
  12119 Hits

በክልል የተገደበው የመዘዋወር ነፃነት

 

 

1. የመዘዋወር ነፃነት አለም አቀፋዊ አንድምታው

የሰው ልጅ ሰው ሆኖ በመፈጠሩ ከሚያገኛቸው አያሌ የተፈጥሮ መብቶች ውስጥ ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነት በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡ የሰው ልጆችን ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነት ከሐይማኖት፤ ከባህል እና ከሌሎች የተፈጥሮ ህግጋት ጀምርን ስንመለከተው ፅኑ መሰረት ያለው ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ በአለማችን ታሪክ ይህ ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብት በአንዳንድ የታሪክ አጋጣሚዎች ላይ ተገድቦ የነበረ ቢሆንም በአብዛኛው ግን ሰዎች ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብታቸው ሲከበር ቆይቷል፡፡ ይሄንን ተፈጥሮአዊ መብት በመጠቀም የተለያዩ የአውሮፓ ሰዎች አዲስ ግኝትን፤ የመካከለኛውና የሩቅ ምስራቅ ሀገሮች ደግሞ ንግድን በማጧጧፍ ለሀገራቸው እና ለአህጉራቸው ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አበርክተዋል፡፡ ይህንን ጥቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት እንደ ማግና ካርታ (Magna Carta) አይነት ጥንታዊ ሰነዶች ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብትን አውጀዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በታላቋ ሮም የነገሱ አብዛኛው ነገስታት ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነትን ሲያከብሩ መቆየታቸውን የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡

ይሁን እንጅ አለማችን በታሪኳ ካጋጠሟት ጠባሳ ታሪክ በቀዳሚነት የሚጠቀሰው የሁለተኛው የአለም ጦርነት እና ከዚህ ጦርነት ጋር በተያያዘ ከተከሰቱ እጅግ አስከፊ የመብት ጥሰቶች መካከል ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነት ይጠቀሳል፡፡ አንድ ችግር ሲፈጠር ለችግሩ መፍትሄ መስጠት ወይም መንገድ ማበጀት የሰው ልጅ ተፈጥሮአዊ ባህሪው በመሆኑ በሁለተኛው የአለም ጦርነት ወቅት የተፈጠሩ የመብት ጥሰቶችን በማስመልከት የተለያዩ እርምጃዎች ተወስደው ነበር፡፡ ከተወሰዱ እርመጃዎች መካከል አለም አቀፍ የሰበዓዊ መብት ተቋማትን መመሰረትና አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ሰነዶችም ማዘጋጀት ይጠቀሳሉ፡፡ በዚህም መሰረት በተቋም ደረጃ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሲቋቋም በሰብዓዊ መብት ሰነድ ደረጃ ደግሞ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድንጋጌ (Universal Declaration of Human Rights) እና ዓለም አቀፍ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ስምምነት (International Covenant on Civil and Political Rights) በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ፡፡ የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድንጋጌ በአንቀፅ 13[1] ላይ በግልፅ ለመዘዋወር ነፃነት እውቅና የሰጠ ሲሆን የዓለም አቀፍ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ስምምነት ደግሞ በአንቀፅ 12 ላይ ተመሳሳይ ድንጋጌ አስቀምጧል፡፡ በተለይ ዓለም አቀፍ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ስምምነት በአንቀፅ 12 ላይ በመርህ ደረጃ ይህ መብት ገደቦች የሌሉበት ቢሆንም በልዩ ሁኔታ በህግ በተደነገጉ ቀድመ ሁኔታዎች አማካኝነት ሊገደብ የሚችልበት ሁኔታዎች አሉ፡፡ እነዚህ ሁኔታዎች ከብሔራዊ ደህነት፤ ከህዝብ ሞራል እና ጤና ጋር የሚያያዙ ናቸው፡፡ እነዚህን ቅድመ ሁኔታዎችን መሰረት አድርጎ የሚወጣ ህግ ከአድሎ ነፃ የሆነ እና የትኛውንም ህዝብ በተለይ የሚጎዳበት አግባብ ሊኖር እንደማይገባው ይደነግጋል፡፡ በአጠቃላይ አለማችን አሁን በደረሰችበት የአእምሮ ማሰብ አድማስ ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነት የሰው ልጅ ከተሰጡ መሰረታዊ መብቶች ውስጥ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ከመሆኑ አንፃር የአለማችን የህግ ሰዎችም ሆኑ ፖለቲከኞች በአስፈላጊነቱ ዙሪያ ሙሉ ለሙሉ ይስማማሉ ማለት ይቻላል፡፡ በመሆኑም በአለም አቀፍ የልማዳዊ ህግ መስፈርቶች መሰረት ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነት የአለም አቀፍ የልማድ ህግነት ደረጃ ደርሷል ማለት እንችላለን፡፡ በመሆኑም ማነኛውም ሀገር፤ በሀገር ውስጥ ያለ አስተዳደራዊ ክልል እንዲሁም ማነኛውም መንግስታዊ ያልሆነ ተቋም ይህንን መብት የማክበር እና የማስከበር ግዴታ አለበት፡፡

Continue reading
  8407 Hits