The Quest to modernize: Is acceding to the New York Convention the right thing for Ethiopia?

It would be appropriate to begin by saying few words about the New York Convention for the Recognition and Enforcement of Foreign Arbitral Awards which came into being in 1948. By the way, our Civil Procedure Code was enacted in 1948 E.C; while the convention was passed in 1948 G.C. Now, simply put, it is a very popular convention in the international arbitration community and is used to enforce an arbitral award (both commercial and non-commercial) in another country.

  11023 Hits

Contemporary Violations of Human Rights in Ethiopia in light of Tripartite Human Rights Obligations

“The world can never be at peace unless people have security in their daily lives.”

UNDP. 1994. Human Development Report 1994.

When governments or non-state actors do horrible, cruel and unjust things to their citizens we are now likely to describe those actions as violations of human rights instead of simply saying that they are unjust, immoral, or barbaric. Human rights are not just illusions they are certain basic entitlements tied to all human beings irrespective of any status.

  12695 Hits
Tags:

በቂ ምክንያት ሳይኖር ዳኛ ከችሎት ይነሳልኝ በሚል የሚቀርብ ማመልከቻ ላይ ስለተቀመጠው ቅጣት

ለዚህ ጽሑፍ ምክንያት የሆነኝ ከታች እንደተገለጸው አንድ ተከራካሪ ወገን በፍ/ቤት ክርክር በሚያቀርብበት ወቅት ሊያጋጥሙት ከሚችሉ ጉዳዮች አንዱ ከችሎት ይነሳልኝ (ችሎት ይቀየርልኝ) በሚል የሚቀርብ አቤቱታ ሲሆን ዳኞች ከችሎት የሚነሱባቸውን ምክንያቶችና ባለጉዳዮች ምን ማድረግ እንዳለባቸው በአዋጅ ቁጥር 25/88 ከአንቀጽ 27 እስከ 30 ባሉት ድንጋጌዎች የተመለከተ ሲሆን የዚህ ጽሑፍ ዋነኛ አላማ እነዚህን ምክንያቶች ማብራራት ሳይሆን ማመልከቻው ውድቅ ቢደረግ አመልካቹ (ተከራካሪው) ሊቀጣ የሚችለውን አዋጁ በአንቀጽ 30 ላይ ያስቀመጠውን የገንዘብ መቀጫ አግባብነትና ፍትሃዊነት ላይ ሃሳብ ለመስጠት ነው፡፡

  11189 Hits

Effect of Irregularities in Public Contract Awarding

Government contract placing is not left to the whim of the individual power holders at the various hierarchies of the government structure. What officials of the government do with the public expenditure should be transparent, and those wielding the power should be accountable to the general public for each and every activity that they do and have it done on behalf of the public. In order to promote efficiency and value-for-money, effectiveness, transparency and probity in the process of government contract formation and to make officials involved in public procurement processes accountable, and thereby curb wide and expansive corrupt practices in their territories, governments have been trying hard to come up with the best possible modern procurement rules. However, irregularities still face almost all public contracts awarding particularly when it is for public construction project. The finding shows that the effects of irregularities in public contract awarding are 1) keeping a public contract awarding with arithmetic error correction when such irregularities are insignificant, 2) reviewing and setting aside a public contract awarding when such irregularities are significant and can affect the outcome of the procurement, 3) avoiding a public contract awarding at all when it is unlawful, 4) disputes between procuring entity and bidders, and 5) civil, administrative and disciplinary, and criminal Liabilities against an employee of procuring entity and/or bidders.

  12086 Hits

‘ኮማንድ ፖስት’ ለአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተሰጠ ልዋጭ ስም?

በሀገራችን ኢትዮጵያ የፀጥታ ችግር በተለያዩ ጊዜያትና ቦታዎች ሲከሰት መንግሥት በሕግ የተቀመጠለትን መደበኛውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመጠቀም ፈንታ በስም የተለየ ነገር ግን በአተገባበር ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር ተመሳሳይነት ያለውን የሕግ ማስከበር መንገድ ‘ኮማንድ ፖስት’ በሚል ስያሜ እያዘወተረ እየተጠቀመ ይገኛል፡፡ ከዚህም በመነሳት ህብረተሰቡም ይህንኑ ኮማንድ ፖስት የተባለውን ስያሜ እኩል ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር አገናኝቶ ሲጠቀም ይስተዋላል፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት ኮማንድ ፖስት መንግሥት በመደበኛ የሕግ ማስከበር መንገድ ሕግን ማስከበር ሲቸገር እየተጠቀመው የሚገኝና በተግባርም የግለሰቦችን መብት የሚገድቡ ክልከላዎችን ጭምር በማውጣት በተግባር ተጠያቂ እያደረገ በመስተዋሉ ነው፡፡ ብዙን ጊዜ ይህንን አዋጅ ሲያውጅ የሚስተዋለው በፌደራል ደረጃ የተዋቀረ ‘ብሔራዊ የፀጥታ ም/ቤት’ የሚባል አካል እነደሆነ ይደመጣል፡፡ ይህ አካል አዋጁን ያውጅ ዘንድ በሕገ-መንግሥቱ ሥልጣን የተሰጠው አካል እንዳይደለ መረዳትም ይቻላል፡፡

  11551 Hits

ወደኋላ ሄዶ ተግባራዊ የሚያደርጉ የታክስና ጉምሩክ ሕግ ድንጋጌዎች ሕገ መንግሥታዊነት

 . ወደኋላ ሄዶ ተግባራዊ የሚያደርጉ የታክስና ጉምሩክ ሕግ ድንጋጌዎች ሕገ መንግሥታዊነት 

የታክስና የጉምሩክ ሕጎች ስንል ምን ማለታችን ነው? ከሕገ መንግሥቱ ጋር ያላቸው ዝምድናስ ምን ይመስላል ?

በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/08 አንቀጽ 2(36) መሠረት የታክስ ሕግ ማለት የጉምሩክ ሕግን ሳይጨምር የታክስ አስተዳደር አዋጅ፣ የፌደራል የገቢ ግብር አዋጅ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ፣ የኤክሳይስ ታክስ አዋጅ፣ የቴምብርና የተርን ኦቨር ታክስ አዋጅ፣ ታክስ/ቀረጥ/ክፍያ ለመጣል የሚወጣ ሕግ እንድሁም እነዚህን አዋጆች መሠረት በማድረግ የሚወጡ ደንብና መመሪያዎችን ያካትታል፡፡ የጉምሩክ ሕግ ማለት ደግሞ በጉምሩክ አዋጅ ቁጥር 859/06 አንቀጽ 2(39) መሠረት የጉምሩክ አዋጁን፣ አዋጁን ተከትለው የሚወጡ የጉምሩክ ደንብና መመሪያዎችን እንድሁም የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን /የአሁኑ ገቢዎች ሚኒሰቴር/ የሚያስፈፀማቸውን ሌሎች ሕጎች ያካትታል፡፡

  13394 Hits

ንብረት የማፍራት እና ፍትሐዊ ዳኝነት የማግኘት መብት: ከወቅታዊው የሕገ-ወጥ መሬትና ንብረት ማስመለስና ማፍረስ ጋር በተያያዘ

አሁን አሁን በተለያዩ የሃገራችን ክልሎች በተለይ ደግሞ በአዲስ አበባ ዙርያ በሚገኙ የኦሮሚያ ልዩ ከተሞች ላይ ከዕለት ወደዕለት በዜጎች የመዘዋወር መብት፤ንብረት የማፍራት፤ የእኩልነት እና ፍትህ የማግኘት ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በሕግ ማስከበር ሰበብ ሲጣሱ ማዬት የዕለት ተዕለት ተግባራዊ ኩነት እየሆነ መጥቷል፡፡

  14910 Hits
Tags:

ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብሮ መኖር፤ አንድምታዎቹ እና ተግዳሮቶቹ

በተሻሻለው የኢትዮጲያ የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 1 መሰረት ህጋዊ ጋብቻ በተለያዩ ሰነ-ስረዓቶች ሊፈፀም ይችላል፡፡ እነሱም በክብር መዝገብ ሹም ፊት፣በሐይማኖት እና በባህል መሰረት የሚፈፀሙ የጋብቻ አይነቶች ናቸው፡፡ በተጨማሪም ጋብቻ ከላይ በተጠቀሱት በአንዳቸው ስነ-ስርዓቶች ቢፈፀም እንኳን ውጤቱም አንድ መሆኑን የዚሁ ህግ አንቀፅ 40 ያትታል፡፡ ህጋዊ ጋብቻ በተጋቢዎቹ ላይ ሁለት ዓይነት ውጤት ይኖረዋል፡፡ የመጀመሪያው በተጋቢዎች ግለዊ ግንኙነት ላይ የሚኖረው ውጤት ሲሆን፤ በስሩም የመከባበር ፣ የመተጋገዝና የመደጋገፍ ግዴታ ፣ ቤተሰብን በጋራ የመስተዳደር እና በጋራ አንድ ላይ የመኖር ግዴታዎችን ያቅፋል፡፡ ሁለተኛው ውጤት ደግሞ ጋብቻ በተጋቢዎች ንብረት ላይ የሚኖረው ውጤት ነው፡፡ ይህም ተጋቢዎች  ጋብቻቸውን በሚፈፅሙበት ጊዜ በግል የነበሯቸው ንብረቶች ወይም ከጋብቻ በኋላ በውርስ እና በስጦታ በየግላቸው ያገኙዋቸው ንብረቶች የግል ንበረታቸው ሆነው ሲቀሩ ከዚህ ውጪ ያሉ ንብረቶች በሙሉ የጋራ  ንብረት ይሆናሉ፡፡

  20978 Hits

በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ መሠረት በተሰጠ የፍርድ ውሳኔ ላይ የሚቀርብ የአፈጻጸም ክስ በይርጋ ቀሪ ስለሚሆንበት የሕግ አግባብ

መግቢያ

አፈጻጸም ማለት አንድ መብቱ በፍርድ ውሳኔ እንዲከበር ለፍርድ ቤት ክስ ያቀረበ ሰው የፍርድ ውሳኔ አግኝቶ በፍርዱ መሰረት ሳይፈጸምለት ሲቀር ፍርዱ የተፈረደበት ወገን እንደ ፍርዱ እንዲፈጽም የሚገደድበት የሕግ ሥርዐት ነው፡፡ ይህ ስርዐት የሚመራውም በፍትሐብሔር ሥነ- ሥርአት ሕግ ቁጥር 375 ጀምሮ በተደነገጉ ድንጋጌዎች መሰረት ሲሆን በእነዚህ የሕግ ማእቀፎች ተንተርሶ መብቱ እንዲፈጸምልት ሚጠይቅ ወገን የፍርድ ባለመብት ሲባል እንዲፈጽም የሚገደደው ደግሞ የፍርድ ባለእዳ ተብሎ ይጠራል፡፡

  16884 Hits

ቀለብ የመስጠጥ ግዴታ ፅንሰ ሀሳብ በተሻሻለው የኢትዮጵያ የቤተሰብ ሕግ

ግዴታ ህጋዊ ግንኙነት ሲሆን መሰረታዊ መርሁም የሚያካተው አንድ ዕዳ ያለበት ሰው ወይም ባለዕዳ ለአበዳሪው ዕዳውን የሚፈጽምበት ሂደት ነው፡፡ በዚህ ግንኙነት ውስጥ ባለዕዳው ለአበዳሪው አንድን ነገር ለማድረግ ፣ ለመስጠት ወይም ላለማድረግና ላለመስጠት የሚያደርገው ህጋዊ ግዴታ ነው፤ በተቃራኒው ደግሞ አበዳሪው ከባለዕዳው የሚገባውን እና በሕግ የተፈቀደለትን ጥቅም የሚያገኝበት ሁነት ነው፡፡ ግዴታዎች ከሁለት ምንጮች ይቀዳሉ፤ የመጀመሪያው ከውል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ከሕግ ነው፡፡ ከውል የሚመነጭ የግዴታ አይነት በተዋዋይ ወገኖች ስምምነት ላይ የሚመሰረት ሲሆን ስምምነቱም በተዋዋይ ወገኖቹ ላይ እንደ ሕግ እንደሚያገለግል የፍትሐብሔር ህጉ አንቀጽ 1731 ያትታል፡፡ ሁለተኛው የግዴታ ምንጭ ደግሞ ከሕግ የሚመዘዝ ነው፤ የዚህ አይነት ግዴታዎች በቀጥታ ከሕግ  የሚመነጩ ሲሆን ግዴታውም በባለዕዳው እና አበዳሪ ሰዎች ሊቀየር ፣ ሊሻሻል እንዲሁም ሊቀር አይችልም፡፡

  17942 Hits