Recent Blog Posts - Blog - Page 17

የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ሕገ-መንግሥታዊነት

ባለፈው ሳምንት መጨረሻ መንግሥት የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽንን የሚያቋቁም አዋጅ ማፅደቁ ይታወቃል፡፡ አዋጁ በተወካዮች ምክር ቤት ውስጥ የጦፈ ክርክርን አስነስቶ በ33 ተቃውሞ እና በ4 ድምፀ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምፅ ቢፀድቅም በፓርላማ ውስጥ ለአዋጁ ድምፅ ከነፈጉ የሕዝብ ተወካዮች ጀምሮ እስከ ክልል መንግሥታት ድረስ ሰፊ ተቃውሞን አስተናግዷል፡፡ ለተቃውሞው መነሻ የሆነው ዋነው ጉዳይ የማንነትም ሆነ በክልሎች መካከል የሚነሱ አለመግባባቶችን መፍታት የፌዴሬሽን ምክር ቤት እና የክልሎች ሥልጣን ሆኖ ሳለ ሌላ ተቋም የማቋቋም አስፈላጊነት እና ሕገ መንግሥታዊነት ጥያቄ ነው፡፡

  14400 Hits

በኢትዮጵያ በኢንተርኔት ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብት እና ገደቡ

ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብት ለዲሞክራሲያዊ ማህብረሰብ መፈጠር የመሰረት ድንጋይ ነው፡፡ ይህ መብት በጣም ረጅም ጊዜ ያስቆጥረ የሰው ልጅ መብት ሲሆን በዘመናት መካከል በፈላጭቆራጭ ነገስታት እና መሪዎች ጫና ተደርጎበታል፡፡ ለአብነት ያህልም በጥንታዊ ባቢሎናዊያን የልዩነት ሃሳብ (being dissenter) መያዝ ወደ እቶን እሳት ያስጨምር እንደነበር ከመጽሃፈ ዳንኤል  ምዕራፍ 3 ንባብ መረዳት እንችላለን፡፡

  16934 Hits

Stolen Asset Recovery in Ethiopia: Critical Legal Issues and Challenges

Staling public money hurts the poor disproportionately by diverting funds intended for development, undermining a Government’s ability to provide basic services, feeding inequality and injustice, discouraging foreign aid and investment, fundamentally distorts public policy and  leads to the misallocation of resources. What makes things worse is that the offence is usually committed by political parties.  Political parties are often seen as actors who abuse their powerful position to extort bribes, to supply members and followers with lucrative positions in the public sector, or to channel public resources into the hands of party leaders or supporters.  In this regard, the 2016 Republican Presidential candidate Dr. Ben Carson once made a statement, “We have been conditioned to think that only politicians can solve our problems. But at some point, maybe we will wake up and recognize that it was politicians who created our problems.”

  14415 Hits

ስለዊዝሆልድንግ ታክስ

መግቢያ

በታክስ ሥርዓት ላይ ጥናታቸውን የሰሩ ባለሙያወች “the tax system must be dynamic with in the dynamic world ” - ተለዋዋጭ በሆነው ዓለም ውስጥ የታክስ ሥርዓቱ ተለዋዋጭ ካልሆነና ዓለም በፈጠረው ቴክኖሎጅ የሚደረገውን የታክስ ስወራ ተግባር መከላከል፣ መቆጣጠር እንድሁም ድርጊቱ ተፈፅሞ ከተገኘ ሊቀጣ የሚችል ሥርዓት ካልዘረጋ የአንድ ሀገር ህልውና አደጋ ላይ ይወድቃል ይላሉ፡፡ እኔም ይህንን ሀሳብ ከሚጋሩ ባለሙያዎች አንዱ ነኝ፡፡ በመሆኑም አንድት ጠንካራ ሉዓላዊት ሀገር ለመገንባት ዘመናዊ ዓለምን ያማከለ ዘመናዊ የታክስ ሥርዓት መዘርጋት ስፈልጋል፡፡ ይህ ተግባር ደግሞ ገቢን በግልፅነትና ተጠያቂነት፣ በፍትሃዊነትና እኩልነት እንድሁም በዘላቂነት መሰብሰብና ማሳደግ የሚችል ሕግ ከማውጣት ይጀምራል፡፡ ሕግ ማውጣት ብቻ ሳይሆን የወጣውን ሕግ ማስፈፀም የሚችል ተቋም እና ሠራተኛ መገንባት ያስፈልጋል፡፡ ተቋሙ እና እያንዳንዱ ሠራተኛ ደግሞ በየደረጃው የወጡ ሕጎችን ለግብር ከፋዩ ማህበረሰብ የማሳወቅ ሞራላዊ ግደታ አለበት፡፡ ሆኖም ከቅርብ ጊዜ ወድህ በግብር ይግባኝ ኮሚሽን እና በፍ/ቤቶች ቅሬታ እያስነሳያለው የግብር ዓይነት ተቀንሶ የሚያዝ ታክስ/ዊዝሆልድንግ ታክስ ሲሆን ለዚህ ጽሑፍ ዓላማ ከእነዚህ ታክሶች አንዱ የሆነውን እና በንግድ ማህበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞና በተግባር የአፈፃፀም ችግር የሚታይበትን በገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 979/08 አንቀፅ 92 ላይ የተቀመጠውን በሀገር ውስጥ ከሚፈፀሙ ክፍያወች ላይ ተቀንሶ የሚያዝ ግብርን በዝርዝር ለመዳሰስ እምክራለሁ፡፡ ወደ ጉዳዩ ከመግባቴ በፊት ግን ዊዝሆልድንግ ታክስ ምን ማለት እንደሆነ ትርጉም ሰጥቼ ማለፍ እፈልጋለሁ፡፡

  33047 Hits

ደረሰኝ አለመቁረጥ እና የወንጀል ተጠያቂነት

(‘ደረሰኝ የማይሰጥ ከሆነ አይክፈሉ')

ደረሰኝ  ምን ማለት ነው?

የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 አንቀጽ 19፣120 እና 131(1)(ለ) እንዲሁም የፌደራል የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 979/2008 አንቀጽ 82 ላይ የተደነገጉ ድንጋጌዎችን ጣምራዊ ንባብ እና ሌሎች አግባብነት ያላቸው ሕጎች  መሠረት በማድረግ የደረሰኝ ትርጉም እና ምንነት፣ የደረሰኞች ዓይነቶች እና ደረሰኝ የመስጠት ግዴታ ያለባቸው ግብር ከፋዮችን እነማን እነደሆኑ እንዲሁም ደረሰኝ መሰጠት ያለበት መች እንደሆነ በወፍ በረር መልኩ ለመዳሰስ እሞክራለሁኝ፡፡

  22811 Hits

በኢትዮጵያ የክስረት ሕግ ነጋዴ ከሰረ የሚባለው መቼ ነው? ከክሥረት ጋር የተያያዙ ወንጀሎችን ከወንጀል ሕጉ አንፃር

የንግድ ሥራ ኢትዮጵያውያን ከ 11 ኛው ምዕት አመት በፊት ባህር አቋርጠው ድንበር ሳይገድቧቸው ቤትና ሀገር ያፈራውን ከሌላው ለሙሙላትና ለመቀያየር አሁን የምንጠቀምበት አይነት ገንዘብ ከሌለበት ጊዜ ጀምሮ ንግድን ስራዬ ብለው ሲሰሩት ነበር። ረጅም ጉዞ በሚደረግብት የጥንቱ ንግድ ግን ሁሉ አልጋ በአልጋ አልነበረም። ያላሰቡት ሽፍታ ከመንገድ ሁሉን ከነጋዴው መዝረፍ፣ የተቀየሩት ንብረቶች ፈላጊ በማጣት ነጋዴውን አትራፊ ከመሆን ይልቅ አክስሮት፣ ለአባዳሪዎች እንግልትና ሲሳይ ይዳርገው ነበር። የከሰረ ነጋዴ በማህበረሰቡ ዘንድ የሚቆጠረው በስራው የገጠመው ዕድለቢስነት በመሆን ሳይሆን መቅሰፍት የወረደበት ተደርጎ ነው። የከሰረን ነጋዴ በጎሪጥ መመልከት፣ ብድር እንኳ ቢጠይቅ ማንም የማያበድረው በመሆኑ የተነሳ አንዴ ወድቆ የማይነሳ ምሳር የበዛበት የሚሆንበት አጋጣሚ አለ።

  2825 Hits

በፍርድ ከሄደች በቅሎየ ያለፍርድ የሄደች ጭብጦየ (ለውጥ የሚሹ የፍርድ ቤት ጉዳዮች)

ፍርድ ቤት የበደል ስር የሚቆረጥበት ፤ ተበዳይ የሚካስበት፤ አጥፊ የሚቀጣበትና መንግስት ከህግ በታች መሆኑ የሚረጋገጥበት መድረክ ነው፡፡ ፍርድ ቤት ፍትህ ከረቂቅነት ከፍ ብላ የምትታይ ፣ የምትሰማ እና የምትዳሰስ ህልው መሆኗ የሚታወቅበት አደባባይ ነው፡፡ ፍርድ ቤት የሰለጠነ ህዝብ የኔ የሚለውን ህግ የሚያስከብርበት መሳሪያ ነው፡፡ ህይወቱ ፣ ንብረቱና የኔ የሚላቸው እሴቶቹ ሁሉ ጥበቃ ያላቸው ስለመሆኑ የሚተማመንበት ዋሱ ነው ፍርድ ቤት፡፡

  14392 Hits
Tags:

ስለ ንብረት የዋጋ ግምት ጥቂት ነጥቦች

ለፍርድ ቤቶች በሚቀርቡ ክርክሮች ላይ የንብረትን ትክክለኛ የዋጋ ግምት ማወቅ የግድ አስፈላጊ የሚሆንባቸው ጊዜያቶች አሉ፡፡ ለመሆኑ የንብረት የዋጋ ግምት ማወቅ ለምን ያስፈልጋል? የንብረት የዋጋ ግምት ተገምቶ እንዲቀርብ የሚጠይቁ ሕጎች የትኞቹ ናቸው? የንብረት የዋጋ ግምት የመገመት ኃላፊነት በሕግ የተሰጠው ለማን ነው? በአሠራር ደረጃ የንብረት የዋጋ ግምት በማን እና እንዴት እየተገመተ ይገኛል? የንብረት ዋጋ ግምትን አስመልክቶ የሚታዩ ችግሮች ምንድን ናቸው? የንብረት የዋጋ ግምት ሲሰራ በመሠረታዊነት ሊካተቱ የሚገባቸው ነጥቦችስ ምንድን ናቸው? የሚሉና ሌሎች ተያያዥ ነጥቦች በዚህ ፅሁፍ በጥቂቱ እንዳስሳለን፡፡  

  20865 Hits

በፍትሐብሔር ጉዳይ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ላይ ብቻ በሚደረግ የክርክር ሥነ-ሥርዓታዊ ሂደት የተከራካሪዎች አለመቅረብ ውጤት፡ ሕጉና ትግበራ

“Law is nothing else, but the best reason of wise men applied for ages to the transaction and business of mankind” Abraham Lincoln

መነሻ ክስተት

ነገሩ እንዲህ ነው! የሙያ ባልደረቦቼ ደንበኞቻቸው ተከሳሽ በሆኑባቸው የፍትሐብሔር የፍርድ ሂደት ላይ መከላከያ መልሳቸውን ሲያቀርቡ በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 244(2) (ለ) መሠረት “ክስ የቀረበበት ጉዳይ አስቀድሞ በፍርድ የተወሰነ” መሆኑን እና (ሠ) መሠረት የቀረበው ክስ “በይርጋ የታገደ” መሆኑን ጠቅሰው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያቸውን በዋናው ክርክር ላይ ካላቸው መልስ ጋር አያይዘው አቅረበው ነበር፡፡ ነገር ግን ፍ/ቤቶች በቀረበው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ላይ ክርክር ለመስማት በተያዘ ቀነ ቀጠሮ ከሳሾች ሳይገኙ በመቅረታቸው ምክንያት ጉዳዩን እየመረመሩ የነበሩት ፍ/ቤቶች ተከሳሾች የቀረበባቸውን ክስ እንደሚክዱ ከጠየቁ በኃላ በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 73 መሠረት ክስ ለመስማት በተያዘ ቀነ-ቀጠሮ ከሳሾች ባለመቅረባቸው እና ተከሳሾች ክደው በመከራከራቸው መዝገቡን ዘግተናል በማለት ትዕዛዝ ሰጥተዋል፡፡

  24252 Hits

Active Participation of Children in Hostilities

Although there is no particular armed conflict or civil unrest in Ethiopia, it’s becoming common to see persons under 15 carrying a gun in different parts of the country. Although these pictures has been looked as fun by so many people, it becomes more serious when the children carrying the gun used some flags and have some connection with organized groups and parties in the country. Based on this assessment, there is a worry that in any case of an armed struggle or any hostilities there would be some kind of resentment to use those children under the age of 15 to actively participate in situations of conflicts. Thus, the following short legal analysis is made to inform any concerned party about the legal ramification of their activity in using children under the age of 15 to execute their military or any hostility related missions.

  10704 Hits