“ለእግረኛ ቅድሚያ በመከልከል…” ከሕግ አንጻር ሲታይ

በሀገራችን እጅግ አሳሳቢ እና አነጋጋሪ ከሆኑት የወንጀል ድርጊቶች መካከል በአሽከርካሪዎች የሚፈጸመው ወንጀል ቀዳሚውን ሥፍራ ይይዛል ለማለት ይቻላል፡፡ ከትራፊክ ፖሊስ ዕለታዊ ሪፖርት በየዕለቱ እንደምንሰማው በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ እንኳን ያለበትን ሁኔታ ብንመለከት በንብረትና በሰው ላይ፣ ቢያንስ በአንደኛው ላይ አደጋ ሳይደርስ የዋለበት ቀን የለም ለማለት ይቻላል፡፡ የአደጋ ዜናው በ24 ሰዓት፣ በወርና በዓመት ስሌት ሲነገር ስንሰማው እጅግ አሳሳቢ ነገር ነው፡፡ በትርፊክ ፖሊስ የዘወትር ሪፖርት እንደምንሰማውም ብዙውን ጊዜ አደጋው የደረሰው ለእግረኛ ቅድሚያ መከልከል በአሽከርካሪ ጥፋት መሆኑን መዘገቡ የተለመደ ነው፡፡

Continue reading
  12106 Hits

የታክስ ይግባኝ ኮሚሽን እና የአዲስ አበባና ድሬዳዋ ከተሞች ራስን በራስ የማስተዳደር መብት

 

የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 እራስን በራስ የማስተዳደር መብትን ከአዲስ አበባ እና ከድሬዳዋ ከተሞች ላይ የገፈፈ ስለመሆኑ እና የመፍትሔ አቅጣጫዎቹ፡፡  

እራስን በራስ የማስተዳደር መብት የፌዴራል ሥርዓትን በሚከተሉ አገሮች የተለመደ አሰራር ሲሆን በዋናነትም ክልሎች ወይም ራስ ገዝ አስተዳድሮች ከፌዴራል መንግስቱ ተፅእኖ ውጪ የራሳቸው ሕግ አውጪ፤ ሕግ ተርጓሚ (የዳኝነት አካል) እንዲሁም የህግ አስፈፃሚ አካላት ኖሯቸው በcheck and balance መርህ ክልላቸውን ወይም አካባቢያቸውን የሚያስተዳድሩበት ቁልፍ ቃል-ኪዳናቸው ነው፡፡

ይህ እራስን በራስ የማስተዳደር መብት በኢትዮጵያ ሕገ መንግስት አንቀፅ 39(3) ለኢትዮጵያ ብሄር፤ ብሄረተሰቦች፤ ሕዝቦች የሰጠ እንዲሁም በአንቀፅ 49(2) ላይ ደግሞ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ ስልጣን እንዳለው የሚደነግግ  ሲሆን በአንፃሩ የድሬዳዋ አስተዳደር ግን ይሄን መብት ሕገ-መንግስቱ እንደነፈገው የሚታወቅ ግልፅ ሐቅ ነው፡፡

በመሆኑም የዚህ ጽሑፍ ዋናው ትኩረት ከዳኝነት አካላት ውስጥ አንዱ ከሆነው የድሬዳዋ  እና የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድሮች የግብር ይግባኝ ሰሚ ጉባኤን የዳኝነት ስልጣን ከሕገ-መንግስቱ (እራስን በራስ ከማስተዳደር መብት ለአዲስ አበባ ከተማ ከተሰጠ መብት አንፃር)፤ ከፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጁ እና ከተሞቹ ከሚመሩባቸው አዋጆች አንፃር ያሉ የሕግ ጉዳዮችን/ችግሮችን በንፅፅር በወፍ በረር በመዳሰስ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ማመላከት ነው፡፡   

Continue reading
  13257 Hits

የውርስ ጉዳይን የተመለከቱ የይርጋ ገደቦች


በሀገራችን የንግድ ሕግ ሥርዓት መሠረት ነጋዴነት ምን መብቶችና ግዴታዎች አሉበት? ለመሆኑ አንድ ነጋዴ በሥሙ ያወጣውን የንግድ ፈቃድ ለሌላ ሰው ማከራየትና በኪራይ ውል ማስተላለፍ ይችላል? አከራይቶ ቢገኝስ በወንጀል ሊያስከስሰውና ሊያስቀጣው ይችላልን? የነጋዴነት መብቶችና ግዴታዎች በየትኞቹ ህግጋት ይገዛል? የነጋዴዎችን መብትና ግዴታዎች በዋናነት የሚመለከቱት ሕግጋት በአዋጅ ቁጥር 166/1952 የወጣውና ከመስከረም 1 ቀን 1953 ዓ.ም ጀምሮ በሥራ ላይ የዋለው የንግድ ሕግ፣ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅና ደንብ እና ግብርን የሚመለከቱ ሕጎች ሲሆኑ ሌሎች ህግጋትም እንደ የውል ሕግ፣ የኪራይ ሕግ፣ የአሠሪና ሠራተኛ ሕግ፣ የወንጀል ሕግ.... በነጋዴዎች ላይ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የሚያስከትሉት መብትና ግዴታዎች ይኖራሉ፡፡ በዚህ አጭር ጽሁፍ ስለ ነጋዴዎች መብትና ግዴታዎች በዝርዝር ለመጻፍ የማይቻል በመሆኑ ጽሁፉ ለመዳሰስ የሚሞክረው በነጋዴነት የተመዘገበ የንግድ ፈቃድ የተሰጠው ሰው የንግድ ፈቃዱን ለሦስተኛ ወገን በኪራይ ውል ማስተላለፍ ህጋዊ መብት አለው ወይስ የለውም? የሚለውን ጭብጥ ነው፡፡


ጽሁፉን በተጨባጭ የፍርድ ቤት ጉዳይ ለመደገፍ ይቻል ዘንድ የሚከተለውን አንድ ጉዳይ እንመልከት፡-
አቶ ተፈራ… (ስሙ ለጽሑፉ ሲባል የተቀየረ) ባለትዳርና የልጆች አባት ሲሆን በባለቤቱ ሥም በቅድመ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት አገልግሎት በሚል ዘርፍ በአፀደ ሕጻናት አገልግሎት የንግድ ፈቃድ የወጣበትን ድርጅት ለማስተዳደር የውክልና ስልጣን የተሰጠው በመሆኑ በራሱ እየሠራበት እያለ በጤና እና በሌሎች ምክንያቶች ድርጅቱን የማስተማር ልምድ ካለው ሰው ጋር በኪራይ ለማሠራት ተስማምተው በጽሑፍ የኪራይ ውል አስተላለፈው፡፡ ይሁንና ተከራይው ግለሰብ ድርጅቱን እንደ ባለቤቱ/ወኪሉ ሆኖ ለመምራት ባለመቻሉ የተማሪዎች ቁጥር እየቀሰነበትና ኪሣራ እየደረሰበት በመምጣቱ በመሐከላቸው አለመግባባት በመፈጠሩ በፍትሐብሔሩ አለመግባባት ጉዳዩ ወደ ፍ/ቤት ደረሰ፡፡ ተከራይው ግለሰብ የንግድ ፈቃዱን ተከራይቶ መሥራቱን ለተቆጣጣሪ አካላት መረጃ በመስጠቱ አቶ ተፈራ በፖሊስ ለምርመራ እንደሚፈለግ ጥሪ ደርሶት የወንጀል ምርመራ ተደረገበት፡፡ ጉዳዩ በምርመራ ብቻ ሳያበቃ በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ቁጥር 686/2002 ድንጋጌዎችን በመተላለፍ የንግድ ፈቃድን ማከራየት ወንጀል ፈጽመሃል በማለት በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክስ ቀርቦበት በወንጀል ተከሳሽ ሳጥን ለመቆም በቃ፡፡ ተከሳሽ ክሱ ደርሶት ስለ ድርጊቱ በፍርድ ቤቱ ሲጠየቅ ድርጅቱን ማከራየቱን ሳይክድ፣ ያከራየሁት መብቴን ተጠቅሜ የድርጅቱን መልካም ዝና እንጅ የንግድ ፈቃዱን ብቻ ነጥዬ ለሌላ ሰው ያላከራየሁ በመሆኑ ጥፋተኛ አይደለሁም በማለት ክርክሩን አቅርቧል፡፡ ከንግድ ሕጉና ከንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጁ አንጻር ተከሳሽ በወንጀል ጥፋተኛ ሊሆን ይችል ይሆን? በህጉ መሠረት የንግድ ፈቃድን ማከራየት የንግድ መደብርን ከማከራየት ተለይቶ የሚታይ ነውን? በተከሳሽ ላይ የቀረበውን ክስና የክርክሩን ውጤት ወደኋላ እናቆየውና በቅድሚያ ለጉዳዩ አግባብነት ያላቸውን የህጉን ድንጋጌዎች እንመልከት፡፡


በንግድ ሕጉ ስለ ነጋዴዎችና ስለ ንግድ መደብሮች በሚለው ክፍል በአንቀጽ 5 ሥር ስለ ነጋዴነት ትርጉም ሲገልጽ “ነጋዴዎች” የሚባሉት ሰዎች የሞያ ሥራቸው አድርገው ጥቅም ለማግኘት ሲሉ በህጉ የንግድ ሥራዎች ተብለው የተቆጠሩትን ሥራዎች የሚሠሩ ሰዎች መሆናቸውን ተደንግጓል፡፡ በንግድ ሕጉና በንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጁ መሠረት የንግድ ሥራዎች ተብለው ከተዘረዘሩት ሥራዎች መካከል ለምሳሌ፡- ጥሬ ዕቃዎችን ወይም ምርቶችን ገዝተው/አምርተው የሚሸጡ፣ ህንጻዎችን/ዕቃዎችን የሚያከራዩ፣ የሆቴል፣ የምግብ ቤት፣የቡና ቤት፣ የመጠጥ ቤት፣የመኝታ ቤት… አገልግሎት የሚሰጡ፣ የትምህርት አገልግሎት የሚሰጡ፣ የላኪነትና አስመጭነት፣ የጉምሩክ አስተላላፊነት…ወ.ዘ.ተ ሥራ በንግድ መዝገብ ተመዝገበውና የንግድ ፈቃድ አውጥተው የሚሠሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ሰዎች የሚለው እንደአግባብነቱ የተፈጥሮ ወይም የሕግ ሰውነት የተሰጣቸውን ሁሉ የሚወክል ነው፡፡ 
በንግድ ህጉ አንቀጽ 100 በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ የንግድ ሥራ የሚሠራ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ወይም የውጭ አገር ሰው ወይም የንግድ ማህበር በመዝገብ መግባት እንዳለበት በአስገዳጅነት ተደንግጓል፡፡ በአንቀጽ 105 እንደተደነገገው አንድ ነጋዴ ለመመዝገብ ማመልከቻ ሲያቀርብ ከሚገልጻቸው መረጃዎች መካከልም የቤተዘመድ ስሙ፣ የተወለደበት ቀንና ቦታ፣ ዜግነቱ፣ የግል አድራሻው፣ የጋብቻ ሁኔታ፣ የንግዱ ዓላማ፣ የንግዱ ሥም፣ ሥራ አስኪያጅ ካለው ስሙንና ሥልጣኑን ይገኙበታል፡፡ እነዚህ ሁኔታዎች በንግድ መዝገብ የመግባታቸው አስፈላጊነት የንግድ ሥራ ፈቃድ በግለሰቡ ማንነት የተወሰነ እንዲሆን ታስቦ ይሆን? የሚል ጥያቄ ያስነሳል፡፡ በንግድ ህጉ አንቀጽ 112 መነገድን ስለመተው በተደነገገው መሠረት ደግሞ ማንኛውም የተመዘገበ ነጋዴ የተመዘገበውን የንግድ ሥራውን በማናቸውም ምክንያት በተወ ጊዜ ወይም የንግዱን መደብር በአከራየ ጊዜ በሁለት ወር ውስጥ ከመዝገቡ እንዲሰረዝ ማመልከቻ ማቅረብ እንደሚገባው ተደንግጓል፡፡


የነጋዴነት ሥራ የቫት(የተጨማሪ እሴት ታክስን ጨምሮ) ከግብር ክፍያና በሽያጭ መመዝገቢያ ማሽን ደረሰኝ ግብይት የማከናወን ግዴታ ፣ ከሦስተኛ ወገኖች ወይም የብድርና ሌላ ውል ተዋዋዮች መብት፣ ከወንጀል ኃላፊነት፣ ከሠራተኞች መብት እና ከሌሎች ጉዳዮች ጋር ዘርፈ ብዙ የመብትና ግዴታ ግንኙነት ያለው መሆኑ ይታወቃል፡፡ ከዚህ አንጻርም የንግድ ፈቃድን በማከራየት የንግዱ ሥራ ቢሠራ በአገልግሎቱ ጥራት፣ በተገልጋይው መብት፣ በንግዱ ቁጥጥር፣ በግብር ክፍያ፣ በተጠያቂነትና በሌሎች ሁኔታዎች ላይ የሚያመጣው አሉታዊ ውጤት ይኖረዋልን? የሚለውን ሥጋቶች ለመከላከል የንግድ ፈቃዱን ላልተፈቀደለት ሰው በኪራይ እንዳይተላለፍ በሕግ መከልከሉ መፍትሔ ይሆናል የሚል ሃሳብ ያጭራል፡፡


በአሁኑ ወቅት በሥራ ላይ ያለው የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ቁጥር 686/2002 ከመውጣቱ በፊት ከ13 ዓመታት በላይ በሥራ ላይ በነበረው አዋጅ ቁጥር 67/1989 ማንኛውም ሰው በንግድ መዝገብ ሳይመዘገብ የንግድ ሥራ መሥራት እንደማይችል፣ የንግድ ድርጅት ለሌላ ሰው በሚተላለፍበት ጊዜ የቀድሞው ፈቃድ ተመላሽ ተደርጎ ድርጅቱ የተላለፈለት ሰው በስሙ ፈቃድ ማውጣት እንዳለበት የተደነገገ ሲሆን በአዋጁ መሠረት በወጣው ደንብ ቁጥር 13/1989 መሰረትም ከአዋጁ በተመሳሳይ ሁኔታ ነጋዴው የቅርብ ጊዜ ፎቶ ግራፉንና ሌሎች ዝርዝር ሁኔታዎችን አሟልቶ መመዝገብ እንዳለበት በአስገዳጅነት ተደንግጓል፡፡ 

Continue reading
  15136 Hits

በክልል የተገደበው የመዘዋወር ነፃነት

1. የመዘዋወር ነፃነት አለም አቀፋዊ አንድምታው

የሰው ልጅ ሰው ሆኖ በመፈጠሩ ከሚያገኛቸው አያሌ የተፈጥሮ መብቶች ውስጥ ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነት በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡ የሰው ልጆችን ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነት ከሐይማኖት፤ ከባህል እና ከሌሎች የተፈጥሮ ህግጋት ጀምርን ስንመለከተው ፅኑ መሰረት ያለው ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ በአለማችን ታሪክ ይህ ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብት በአንዳንድ የታሪክ አጋጣሚዎች ላይ ተገድቦ የነበረ ቢሆንም በአብዛኛው ግን ሰዎች ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብታቸው ሲከበር ቆይቷል፡፡ ይሄንን ተፈጥሮአዊ መብት በመጠቀም የተለያዩ የአውሮፓ ሰዎች አዲስ ግኝትን፤ የመካከለኛውና የሩቅ ምስራቅ ሀገሮች ደግሞ ንግድን በማጧጧፍ ለሀገራቸው እና ለአህጉራቸው ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አበርክተዋል፡፡ ይህንን ጥቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት እንደ ማግና ካርታ (Magna Carta) አይነት ጥንታዊ ሰነዶች ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብትን አውጀዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በታላቋ ሮም የነገሱ አብዛኛው ነገስታት ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነትን ሲያከብሩ መቆየታቸውን የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡

Continue reading
  11198 Hits

ተደራሽ ግን ርካሽ ዳኝነት - የኦሮሚያ ወረዳ ፍርድ ቤቶች ምልከታ



በዳኛው ገጠመኝ እንጀምር። የአንዱ የኦሮሚያ ወረዳ ፍ/ቤት ዳኛ ለተዘዋዋሪ ችሎት በሕዝብ ትራንስፖርት እየሄደ ነበር። መኪናው ውስጡ ሞልቶ ረዳቱ ከላይ ለመጫን ይቃጣዋል። መኪናው ላይ የተፃፉ ጥቅሶች እንቅጩን ይናገራሉ።

"ታሪፍ እንጂ ትራፊክ የለም፣ ጠጋ ጠጋ በሉ" 
"የሰው ልጅ ክቡር ነው፣ ትርፍ ሰው የለም ግቡ"
"ሞላ የሰው ስም ነው፣ገባ ገባ በሉ"

ወዘተ። 

እና ዳኙዬ ተጣብቆ ቆሞ ከቦታው ደረሰና ችሎት ስራውን ይጀምራል። መኪና ውስጥ ወንበር ላይ ተቀምጦ የነበረ ባለ ጉዳይ ውጭ ቆሞ ከጓደኛው ጋር "ቆሞ የመጣው ሶዳ (አማቻችን) እዚህ ደርሶ ወንበር አገኘ" እያለ ይሳለቃል። ችሎት ተደፈረ? ፖሊስ የለም። የቀበሌ ታጣቂ እንኳን የለም።

 
ሰውየው ተራ ደርሶት ተጠራና ይገባል። ዳኛው ከንግግሩ ላይ ንዴት ይነበባል። ሰውየው ግን ቀላል ፎጋሪ አይደለም "ቅድም እኮ ዳኛ መሆንህን ባውቅ እነሳልህ ነበር" ብሎ ፈገግ አለ። ከፈገግታው ጥፊ ይሻላል። ችሎት ተደፈረ? የለም የለም! ይህ የዳኛው እውነተኛ ገጠመኝ ነው።

Continue reading
  10479 Hits

የተሻሻለው የአማራ ክልል የገጠር መሬት አዋጅ እና አከራካሪው የይርጋ ድንጋጌ

የአማራ ክልል የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 133/98 የተካው የተሻሻለው የገጠር መሬት አዋጅ ቁጥር 252/2009 ቀደም ሲል በሕግ ደረጃ ሽፋን ያላገኙ አዲስ ነገሮችን ይዞ እንደወጣ ይታወቃል፡፡ አዲስ ከሚባሉ ነገሮች አንዱ በገጠር መሬት ላይ በሚነሱ ክርክሮች ላይ የይርጋ መቃወሚያ ተፈፃሚ ሊሆን እንደማይችል ያስቀመጠው ነገር ነው፡፡ ይህ የይርጋ ድንጋጌ በሕጉ የተካተተ አዲስ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ገና ከጅምሩ አከራካሪ ጉዳይ እየሆነ መጥቷል፡፡ አከራካሪነቱም በባለሙያዎች መካከል ሁለት ጫፍ የያዙ አቋም እንዲኖር ከማድረግ አልፎ አዲስ የክርክር ምክንያትም እየሆነ ነው፡፡ አዋጁ ስራ ላይ ከዋለ ጀምሮም የገጠር መሬትን ተከትሎ የሚቀርቡ ክሶች ላይ የይርጋ መቃወሚያ ተፈፃሚነት የለውም በሚል  ብዙ ዶሴዎች ከተዳፈኑበት አቧራቸውን እያራገፉ በክስ መልክ  እየቀረቡ ነው፡፡ ፍርድ ቤቶችም በባለሙያዎች መካከል በይርጋው ተፈፃሚነት ላይ  ባለ ሁለት ጫፍ የያዘ አቋም ምክንያት ከወዲሁ ተገማችነታቸውና ወጥነታቸው አደጋ ላይ እየወደቀ ነው፡፡ ስለዚህም በጉዳዩ ዙሪያ  የሚነሱ አቋሞችን እና ምክንያቶችን በማየት ሃሳቡን መመልከቱ አስፈላጊ እና ትኩረት የሚያስፈልገው ነው፡፡ የፁሁፉ ዋና ትኩረትም በተሻሻለው የገጠር መሬት አዋጅ ላይ የተቀመጠጠው የይርጋ ድንጋጌ ወሰን አለው ወይስ የለውም የሚል ይሆናል፡፡

Continue reading
  46516 Hits

የፍርድ ቤት ወይስ የችሎት ስልጣን? (Jurisdiction of Courts or Divisions)

 

ይህን ለመጻፍ ያስገደዱኝን እና የገጠመኙን ሁኔታዎች በቅድሚያ ላብራራ፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ሰራተኛ አሰሪው በነበረው ድርጅት ላይ ህገ-ወጥ የስራ ውል መቋረጥ ተፈጽሞብኛል በማለት ላቀረበው ክስ አሰሪው ድርጅት በተከሳሽ ከሳሽነት ክስ ማስጠንቀቂያ ሳይሰጠኝ ሰራተኛው የስራ ውሉን ስላቋረጠ ካሳ እንዲከፍለኝ የሚልና ሰራተኛው ስራ ላይ በነበረ ጊዜ ለስራው አገልግሎት የተሰጠውን ላፕቶፕ ኮምፒውተር ሳይመልስ በመቅረቱ ንብረቱን እንዲመልስ ወይም የንብረቱን ግምት ብር 23,000 (ሃያ ሶስት ሺ) እንዲከፍለኝ በማለት ክስ አቀረበ፡፡ ጉዳዩን ሲያይ የነበረው የፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት የስራ-ክርክር ችሎትም በድርጅቱ የላፕቶፕ ንብረትን በተመለከተ የቀረበውን የተከሳሽ ከሳሽነት ክስ ይህ ችሎት (ልብ በሉ ፍ/ቤቱ አይደለም) የማየት ስልጣን ስለሌለው ጉዳዩን በዚሁ ፍ/ቤት በፍትሐብሄር ችሎት ክስ የማቅረብ መብታቸውን ጠብቄ አቤቱታውን ውድቅ አድርጌዋለሁ በማለት ብይን ሰጥቷል፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታም ተከራይ ከአከራዩ ድርጅት ሶስት ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ ክፍሎችን በተለያየ ጊዜ የተከራየ ሲሆን በቅድሚያ ለተከራያቸው ሁለት ክፍሎች የውል ሰነድ ያለው ሲሆን ለሶስተኛው ክፍል ግን ከቃል ስምምነት ባለፈ በጽሁፍ የተደረገ ውል የለም፡፡ ነገር ግን ለሶስተኛው ክፍልም ቢሆን ለአራት ወራት ያህል በየወሩ ከተከራይ የኪራይ ገንዘብ የተቀበለበትን ደረሰኝ በማስረጃ አያይዟል፡፡ ይህንንም የኪራይ ውልና የኪራይ ክፍያ ደረሰኝ መሰረት በማድረግ አከራይ ላልተከፈለው እና ተከራይ ለተገለገለበት ጊዜ የኪራዩ ክፍያ ይከፈለኝ በማለት በፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት ክስ ያቀረበ ሲሆን ጉዳዩን ሲመረምር የነበረው የፍ/ቤቱ የኪራይ ችሎትም (ልብ በሉ ፍ/ቤቱ አይደለም) የኪራይ ውል ሰነድ ያላቸውን  ክፍሎች አስመልክቶ ጉዳዩን የማየት ስልጣን ያለኝ ሲሆን የኪራይ ውል የሌለውን ሶስተኛውን የቢሮ ኪራይ ክፍያ ክስ በተመለከተ ግን ጉዳዩን የማየት ስልጣን ያለው በዚሁ ፍ/ቤት የንግድና ልዩ ልዩ ችሎት ስለሆነ በዚህ ችሎት ክስ የማቅረብ መብታችሁን ጠብቄ በሶስተኛው ቢሮ ላይ ያቀረባችሁትን ክስ ዘግቼዋለሁ በማለት ብይን ሰጥቷል፡፡

ለመሆኑ በአዎጅ የተቋቋሙ ፍ/ቤቶች እንጂ ችሎቶች ይህን መሰሉ ስልጣን አላቸው? የፍትሐብሔር የሥነ-ሥርዓት ሕጉ ዓላማስ ከዚህ አኳያ እንዴት ይመዘናል የሚለውን በጥቂቱ እንደሚከተለው አቀርባለሁ፡- የፌደራል ፍ/ቤቶችን ያቋቋመው አዎጅ ቀ. 25/88 በፌደራል ደረጃ የሚኖሩት ፍ/ቤቶች የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት፣ ከፍተኛ ፍ/ቤት እና ጠቅላይ ፍ/ቤት መሆናቸውን ሲገልጽ የእነዚህ ፍ/ቤቶችም በመጀመሪያ ደረጃ ስልጣንም ሆነ በይግባኝ ደረጃ ጉዳዮችን ተቀብለው አይተው እና አከራክረው ወሳኔ ሊሰጡ የሚችሉባቸውን ጉዳዮች በዝርዝር ደንግጓል፡፡

ይህ አዎጅ ይህንንም ሲገልጽ እነዚህ የፌደራል ፍ/ቤቶች ጉዳየን ለማየት እንዳለቸው ስልጣን የተፋጠነ ፍትህን ለመስጠት እንዲያስችል እያንዳንዱ ፍ/ቤት ቢያንሰ ሶስት ችሎቶች እነዚህም የፍትሐብሄር፣ የወንጀል እና የስራ-ክርክር ችሎቶች ሊኖሩት እንደሚገባ (በፌ/ፍ/ቤቶች አዎጅ 25/88 አ.ቁ 20(1) ፣23(1)) ሲደነግግ እንደሚቀርቡለት የጉዳዮች ብዛትና ዓይነት በስሩ እንደ ነገሩ ሁኔታ ሊይዛቸው የሚችሉ ችሎቶችን ፍ/ቤቱ በራሱ አስተዳደራዊ ውሳኔ የማብዛት መብት አለው (በተሻሻለው ፌ/ፍ/ቤቶች አዎጅ 454/97 አ.ቁ 23(1))፡፡

Continue reading
  16459 Hits

‘ጠባቂ የሌለው ጠበቃ’ ጥቂት ስለ ኢትዮጵያ የሕግ ባለሞያዎች ማህበር

መነሻ ነጥብ

የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያዎች ማህበር በ1958 ዓ.ም.በእድርና እቁብ አይነት ቅርጽ የተመሰረተ ድርጅት ነው፡፡ በሰዓቱ ከአርባ የማይበልጡ አባላት የነበሩት ሲሆን አባሎቹም በከተማይቱ አዲስ አበባ የጥብቅና አገልግሎት የሚሰጡ ነበሩ፡፡ ይህ ማህበር የተደራጀና የአባላቱን እንዲሁም የተከበረ ሙያ የሆነውን የጥብቅና ሙያ ለማስጠበቅና ለመጠበቅ ሳይሆን በማህበርተኞች መካከል ለሚፈጥሩ ማህበራዊና ሰዋዊ ችግሮች ለመረዳዳት ተብሎ የተመሰረተ ተቋም ነበር፡፡ ይህ ስብስብ በተመሰረተ በአመቱ ማለትም በ1959 ዓ.ም. በቀድሞው አጠራር የሀገር ግዛት ሚኒስቴር ተመዝግቧል፡፡ ከአብዮቱም በኋላ የኢትዮጵያ የጠበቆች ማህበር የሚለውን ስያሜ የያዘ ሲሆን በማህበሩ ውስጥ ጠበቆች፣ የሕግ መምህራን፣ ዳኞች፣ የሕግ ጉዳይ ፀሐፊዎች እና ሌሎችም አባል ሆነው ይሰሩ ነበር፡፡ ስሙን ቀይሮ የመጣው ማህበር የግብርና የዓላማ ለውጦችንም በማድረግ ደረጃውን የጠበቀ የጥብቅና ሙያ እንዲኖር ግንባር ቀደም ዓላማው አድርጎ ተነሳ፡፡ በወቅቱም ልክ አሁን እንዳለው ተመሳሳይ አሰራር የጥብቅና ፍቃድ በማሳየትና የአባልነት ክፍያ በመክፈል አባል መሆን ይቻል ነበር፡፡

Continue reading
  13821 Hits

የልዩ ምርመራ ኦዲት ግኝቶችና የወንጀል ውጤታቸው

 

 

“I CAN’T DEFINE TAX EVASION, BUT I KNOW IT WHEN I SEE IT.”

— FRED T. GOLDBERG JR.

Continue reading
  19051 Hits

የረዳት አብራሪው ኃይለመድህን አበራ የወንጀል ክስ ጉዳይ በየትኛው አገር ፍ/ቤት መታየት አለበት?

 

 

መግቢያ

ቼክ ጥሬ ገንዘብን ተክቶ በመገበያያነት አገልግሎት ላይ የሚውል የሚተላለፍ የንግድ ወረቀት አይነት ነው። በሀገራችን በቼክ መገበያየት እጅግ የተለመደ ተግባር ሲሆን ቼክም ሌሎች የሚተላለፉ የንግድ ሰነዶች ካላቸው እውቅናና ተቀባይነት በላቀ አገልግሎት ላይ እየዋለ ያለ እና በህብረተሰቡም ዘንድ እውቅና ያለው ሰነድ ነው። በሰነዱ ላይ ህብረተሰቡ የጣለው እምነትና በስፋት አገልግሎት ላይ መዋሉም በሰነዱ ላይ በተለያዩ ጊዜያት እና በስፋት የፍርድ ቤት ክርክሮች እንዲነሱ አንዱ ምክንያት እንደሆነ እሙን ነው። ታዲያ በዚህ ሰነድ በስፋት አገልግሎት ላይ መዋልና በሕጋችን ውስጥ ሰነዱን አስመልክቶ የተቀመጡ ድንጋጌዎችን ማሻሻል እና ክፍተቱን መሙላት አስፈላጊና ለሰነዱ ቀጣይነትም አስተማማኝ ዋስትና ነው።

በዚህ አጭር ጽሑፍ ውስጥም በተለይም ቼክን በተመለከተ በስፋት የሚያጋጥመውንና በሕጋችን ሽፋን የተሰጠውን   የቼክ የክፍያ ይቁም ትዕዛዝ (Stop Payment Order) በተመለከተ ጥቂት ምልከታ ለማድረግ ነው። በጉዳዩ ላይ በስፋት አንባቢዎች ግንዛቤን ከፈለጉ ጸሐፊው የኢትዮጵያ የባንክ እና የሚተላለፉ የንግድ ሰነዶች ሕግ በሚል የታተመውን መጽሀፍ ማንበብ እንደሚችሉ በዚሁ ለመግለጽ እወዳለሁ።

Continue reading
  17676 Hits
Tags: