በኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነ ሥርዓት የቀዳሚ ምርመራ ድንጋጌዎችና አተገባበራቸው አጭር ዳሰሳ

የወንጀል ክስን በማስረጃ አስደግፎ በማረጋገጥ እና ተከሳሽን ወደ ፍርድ ቤት በማቅረብ ጥፋተኛ ማስደረግ በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ትልቅ ጥረትና ድካም የሚጠይቅ ተግባር ነው፡፡ አንድ ወንጀል ማህበረሰቡ ላይ ሲፈጸም ወንጀሉን የፈጸመን አካል ነቅሶ በማውጣት ለፍርድ በማቅረብ ማስቀጣት የመንግሥት ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ አንድ መንግሥት የሕዝብን  ሥልጣን  ሲቀበል  የማህበረሰቡን  ሰላም  መጠበቅ ከሕዝቡ የተጣለበት  ግደታው  ነው፡፡ ይህንን ሰላም ለመጠበቅ  ደግሞ  ወንጀል  እንዳይፈፀም ይከላከላል፡፡ ከተፈፀመ በኋላ ፈፃሚውን ለሕግ ያቀርባል፣ ወንጀል ለመፈፀሙ ሊያሥረዱ የሚችሉ ማስረጃወችን አብሮ ያቀርባል፡፡

  26444 Hits

ዳኞች፣ ዐቃቤ ሕጎች፣ ጠበቆች እና ፖሊሶች ሊዘነጓቸው የማይገቡ የወንጀል ሥነ ሥርዓት ሕግ መርህዎች

መንግሥት የሃገርን ሰላምና ደህንነት የመጠበቅ እና የማስጠበቅ እንዲሁም የሕዝቦቹን እና የነዋሪዎቹን መሠረታዊ የግለሰብና የቡድን ነፃነት መብት እና ጥቅም የማክበርና የማረጋገጥ ግንባር ቀደም ኃላፊነትና ሚና አለበት፡፡ ይህንን ኃላፊነቱን ለመወጣት ከሚያከናውናቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት መካከል በግልጽ በሚመራ ሥርዓት የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ማዕቀፍን መዘርጋትና ማቋቋም አንዱና ዋነኛው ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ማዕቀፍን ከሚያቋቁሙ ምሰሶዎች መካከል የወንጀል ሕግ፣ የወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕግ እና የማስረጃ ሕግ በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ፡፡

  26785 Hits

የ‹‹ያስቀርባል … አያስቀርብም›› እንቆቅልሽ

ዶ/ር ትዝታ በፌዴራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ጉዳዩዋን ለመከታተል በችሎት ታድማለች፡፡ በሥር ፍርድ ቤት በቤቷ ላይ ያለአግባብ ፍርድ ተሰጥቷል ብላ ስላመነች የተማረ ጠበቃ የይግባኝ አቤቱታ ጽፎላት ጉዳይዋን በራሷ ትከታተላለች፡፡ እንደ እርሷ አስተሳሰብ ጉዳይዋን ከእርሷ ይልቅ የሚረዳው የለም በሚል ከዳኛ ፊት ቀርባ ለማስረዳት ጓጉታለች፡፡ በዛሬው ቀጠሮ ይህ ሐሳቧ እንደሚሳካላት በውጭ የሚያማክራት ጠበቃ ነግሯታል፡፡

  16231 Hits

ሰበር በአዲስ አበባ ፍርድ ቤት ሥልጣን ላይ ያሰመረው ቀጭን መስመር

የአዲስ አበባ ፍርድ ቤት ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ሥልጣናቸውን የተመለከቱ የተለያዩ ክርክሮች ተነስተዋል፡፡ ዋናው ክርክር በተቋቋመበት ወቅት የተነሳው የሕገ መንግሥታዊነት ጭብጥ ነው፡፡ ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 78 እስከ 80 የዳኝነት አካሉን ሲያዋቅር በተለያዩ ደረጃዎች ያሉት የፌዴራልና የክልል ፍርድ ቤቶች እንደሚቋቋሙ በመግለጽ የፍርድ ቤት ሥልጣን ከመደበኛ ፍርድ ቤቶች የሚወሰዱ ጊዜያዊና ልዩ ፍርድ ቤቶች እንደማይቋቋሙ ደንግጓል፡፡

  14611 Hits

 አንድ አንድ ነጥቦች ስለ ቼክ እና በተግባር የሚያጋጥሙ የሕግና የአሰራር ችግሮች

ቼክ በተግባር በሰፊው ከሚሰራባቸውና በሕግ ከተቀመጡት ንግድ ሰነዶች አንዱና ዋነኛው ነው፡፡  በቼክ ላይ እምነት የሚታጣበት ከሆነ የንግድ ዝውውር ደህንነት (security of transaction) ላይ ሊያሳድር የሚችለው ተፅዕኖ እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡ የንግድ ሥራው እያደገ በመጣ ቁጥር በቼክ የሚደረጉ የንግድ ልውውጦች የሚጨምሩ እንደሚሆን የሚታመንና በተግባርም የሚታይ ነው፡፡ የቼክ ዝውውር እየጨረ እንደመጣም መገመት አያዳግትም፡፡ እየጨመረ የመጣውን የቼክን ዝውውር አስተማማኝነት ለማሳደግ ሕጎች ሥርዓቱን ሊቆጣጠሩት ይገባል፡፡ በዚህም መሠረት በእኛ ሀገር የንግድ ሕጉ እና የወንጀል ሕጉ ይህንኑ የቼክ ጉዳይ በዋናነት ይህን ሥርዓት ዘርግተው ይገኛሉ፡፡ ባብዛኛው የቼክ ጉዳይ የሚያከራክር ጉዳይ የሌለበት ቢሆንም አልፎ አልፎ ግን አከራካሪ ጉዳዮች መታየታቸው አልቀረም፡፡ ይህ ጽሑፍ ዓላማውም በቼክ ዙሪያ ያሉትን አስፈላጊ የሕግ ድንጋጌዎችንና አስገዳጅ የፍርድ ውሳኔዎችን ማሳወቅና በተወሰነ መልኩም ቢሆን ለአከራካሪ ጉዳዮች የጸሐፊውን እይታ ማንፀባረቅ ነው፡፡

  24418 Hits
Tags:

ሰበር ለመታረቅ በተደረገ ስምምነት ላይ የያዘው አቋም ሲፈተሽ

ኢትዮጵያ ውስጥ የዳኝነት ሥልጣን ያላቸው ፍርድ ቤቶች ብቻ አይደሉም፡፡ ይህን ሥልጣን የተጎናፀፉ ብዙ አካላት አሉ፡፡ ለአብነት ያህል ለመጥቀስ፡- በፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር ውስጥ የሚገኘው የአስተዳደር ፍርድ ቤት ከሥራ መሰናበት፣ ደመወዝ መቁረጥና የመሳሰሉትን ጥያቄዎች አስመልክቶ በመንግሥት ሠራተኛውና  በፌዴራል መንግሥት መሥሪያ ቤት መካከል የሚነሳ አለመግባባት ላይ ዳኝነት ይሰጣል፡፡ ሕገ መንግሥቱን መተርጎም ላይ አለመግባባት ከተፈጠረ ዳኝነት የመስጠት ሥልጣን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ነው፡፡ በግብር ጉዳዮች ላይ የግብር ይግባኝ ሰሚ ኮሚሽን የዳኝነት ሥልጣን አለው፡፡ የማኅበራዊ ዋስትና መብትና ጥቅም  ጥያቄዎች ላይ የዳኝነት ሥልጣን ለማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ ተሰጥቷል፡፡ የከተማ ቦታ ማስለቀቅና የካሳ ጉዳዮች ላይ የዳኝነት ሥልጣኑ በየከተማ አስተዳደሮች ለሚቋቋሙ ጉባዔዎች ተሰጥቷል፡፡ የንግድ ውድድር ጨቋኝ የሆኑ ድርጊቶችና ያልተገባ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ደግሞ ዳኝነት የሚሰጥ የንግድ አሠራርና የሸማቾች ጥበቃ ባለሥልጣን የሚባል ተቋም አለ፡፡ ወታደራዊ ፍርድ ቤቶችም አሉ፡፡ ይሁን እንጂ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ያለውን የዳኝነት ሥልጣን ያህል የተጎናፀፈ ፍርድ ሰጪ አካል ኢትዮጵያ ውስጥ የለም ለማለት ያስደፍራል፡፡ የዚህን ችሎት የዳኝነት ሥልጣን ሊወዳደር ወይም ሊበልጥ የሚችል ፍርድ ሰጪ አካል ኢትዮጵያ ውስጥ ካለ፣ የሕገ መንግሥት ትርጓሜ ላይ ዳኝነት የመስጠት ሥልጣን ያለው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ብቻ ነው፡፡

  10078 Hits

የኦሮሚያ ልዩ ጥቅም ከአዲስ አበባ ምን ሊሆን ይችላል

በሀገራችን በቅርብ ጊዜየቶች ውስጥ በተደጋጋሚ እየተነሱ ከሚገኙ ጉዳዮች እና የሕግ እና የፓለቲካ ተዋንያንን እያነጋገር ያለው አንዱ ጉዳይ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከአዲስ አበባ ከተማ ሊኖረው ይገባል በሚል በኢፌድሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 49 (5) የተቀመጠውን ልዩ ጥቅም የተመለከተው ድንጋጌ ነው፡፡በሕገ-መንግሥቱ ላይ የተቀመጠውን ድንጋጌ አንዳንድ ሰዎች እንደሚያነሱት በሀገሪቷ ውስጥ ያሉትን ሰለማዊ የሆኑ ህዝቦች አብረው ሲኖሩ የነበሩትን ግንኙነት ለማበላሸት እና ልዩነትን ለማጉላት በሚል የተቀመጠ ድንጋጌ አድርገው የሚመለከቱ ሲሆን ሌሎች ደግሞ ይህ ድንጋጌ በሀገሪቷ ውስጥ የነበረውን ተጨባጭ የህዝቦች ችግር ለመፍታት በሚል የገባ ችግር ፈቺ እና ምክንያቲያው ድንጋጌ እንደሆነ አድርገው ይገልጹታል፡፡ በዚህ ሕገ-መንግሥታዊ ድንጋጌ ላይ ሕገ-መንግሥቱ ለሕገ-መንግሥት አርቃቂ ጉባኤ ቀርቦ በሚታይበት ወቅትም ቢሆን የተለያዩ ሀሳቦች የተነሰቡት እና በሃላም ላይ ድንጋጌው ተቀባይነት አግኝቶ የጸደቀበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ በዚህ ጽሁፍ ውስጥ በሕገ-መንግሥቱ ላይ የተደነገገው የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ልዩ ጥቅም በአዲስ አበባ አለው የሚለው ድንጋጌ ይዘት ላይ ምን እንደሆነ እና ምን እንዳልሆነ፤ እነዚህን ልዩ ጥቅሞች በስራ ላይ ለማዋል በሚታሰብበት ውቅት ታሳቢ ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጉዳዮች በመግለጽ ለውይይት የሚሆን መነሻ ሀሳብ ማቅረብ ነው፡፡

  15732 Hits

The Curious Case of Construction & Business Bank

Businesses want to become big. They want their presence to be felt in every corner of the world. Investors explore different avenues to do this by injecting capital, selling equities, reinvesting their profits, opening different branch offices, acquiring other firms or merging with other entities. By the same token, corporations may also use these tactics to either dominate the market or protect their infant industry from other big entities.

  11468 Hits

Corporate Social Responsibility as a New Way of Advertisement

Traditionally, corporations were responsible only to their owners; their primary objective was profit maximization. Corporations’ responsibility towards the community and the environment in which they operate was overlooked. Hence, Corporations’ responsibility towards the community and the environment, which is commonly known as corporate social responsibility, is a recent development in the area of corporate governance.

  12398 Hits
Tags:

"በሕግ አግባብ"ያለአግባብ ስለመታሰር

ካሳ አልባ የፍትሕ ሥርዓቱ ተጎጂዎች

እንዲያው አያድርገውና በወንጀል ተጠርጥረው ጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆብዎ አስቸጋሪውን የወንጀል ምርመ

  15185 Hits