Excise taxes are an example of what have been traditionally called indirect taxes: taxes that are imposed on a transaction rather than directly on a person or corporation. Excise taxes are narrow-based taxes, as compared with broad-based taxes on consumption such as a general sales tax, a value-added tax, or an expenditure tax. Excise taxes can be collected at various stages, including the point of production, the wholesale level, or the retail level. They are also known as selective sales taxes or differential commodity taxes.
“Violations of human rights are both a cause and a consequence of trafficking in persons.”
UN human rights office of the High Commissioner, fact sheet 36
Introduction
Traditionally, People in Ethiopia feel that living abroad is life changing and take it as a privilege. In country sides there is customarily mainstreamed saying that “እልፍ ቢሉ፤እልፍ ይገኛል/ Eliff bilu elf yignagal” meaning that if somebody changes a living place she or he will get a decent life counted in thousands. That’s why many peoples in Ethiopia left their home and searching jobs abroad via illegal means and fall in the hands of satanic and barbaric traffickers in turn witnessed dozens of sufferings.
በማንኛውም አገር የመንግሥት አስተዳደር ከሕግ አውጪውና ከሕግ አስፈጻሚው እኩል የዳኝነት አካሉ አደረጃጀት፣ አወቃቀርና ጥንካሬ የሥርዓቱን ዴሞክራሲያዊነት ይወስናል፡፡ የዳኝነት አካሉ ገለልተኛና ነፃ ባልሆነ መጠን የሥርዓቱ ዴሞክራሲያዊነት ዋጋ ያጣል፡፡ የዳኝነት አካሉ መሠረታዊ ሕገ መንግሥታዊ መርሆችን ለማስፈጸም፣ የዜጎች የሰብዓዊ መብቶች እንዲጠበቁና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን ገለልተኛ፣ ግልጽ አሠራርን የሚከተልና ጠንካራ እንዲሆን ያስፈልጋል፡፡ በ1987 ዓ.ም. የወጣው ሕገ መንግሥታችን በአንቀጽ 78 እና 79 እነዚህ መሠረታዊ የዳኝነት አካሉ መገለጫዎችን ደንግጓል፡፡ ይሁን እንጂ ሕገ መንግሥቱ ከወጣ ከ25 ዓመታት በኋላም የዳኝነት አካሉ የአሠራር ግልጽነትና ተጠያቂነት አመርቂ እንዳልሆነ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ይስማማሉ፡፡
ማንኛውም ሰው በማህበራዊ ኑሮ ውስጥ በሚገጥመው መስተጋብር የተለያዩ ጥያቄዎች ወይም መብቶች (Claims) ሊኖረው ይችላል፡፡ ከዚህ ንድፈ ሃሳብ በመነሳት ታዲያ በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውም በርካታ የመብት ጥያቄዎች መነሳታቸው ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው! እንደሚታወቀው የግንባታ ዘርፍ ብዙ ባለድርሻ አካላትን ማሳተፋ ብቻ ሳይሆን የሚገርመው በተለያየ ሙያ ያሉ ሰዎች መሳተፋቸውም ጭምር ነው፡፡ ይህም በመሆኑም በርካታ የመብት ጥያቄዎች መነሳታቸው የግድ ነው፡፡ ከዚህ ብሂል በመነሳት አንዳንዶች ከውል በመነጨ ጉዳይ የውል የመብት ጥያቄ ሲያነሱ ሌሎች ደግሞ ሕጉ አስቀድሞ ባስቀመጠው ቅድመ ሁኔታ መሠረት ውል ሳይኖር አላፊነት በመኖሩ ምክንያት መብታቸውን ከውል ውጭ ሲጠይቁ ይስታዋላል፡፡
የሥነ-ሥርዓት ሕግ ሰዎች መሠረታዊ የሆኑ የፍትሕ አቤቱታዎች ሲቀርቡ የሚመሩበትን እና መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች በሚመለከታቸው የፍትሕ አካላት የሚወስኑበትንና ተፈፃሚ ሊሆኑ የሚችሉበትን ሥርዓት የሚያሳይ ጽንሰ ሀሳብ ነው። የሥነ-ሥርዓት ሕግ መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች በምንና እንዴት ባለ አኳኋን ወደ ተግባር ሊፈፀሙ እንደሚችሉ የሚዘረዝር የሕግ ክፍል ነው። የእነዚህን መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች ይዘትና አይነት ተንትኖ የሚያቀረበው የሕግ ክፍል መሠረታዊ ሕግ (Substantive Law) ተብሎ የሚጠራ ነው። መሠረታዊ ሕግ የሰው ልጆችን መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች በግልፅ የሚደነግግ በመሆኑ ጠቀሚታው ከፍተኛ እንደሆነ ይታመናል። ይሁን እንጅ እንዚህ ዝርዝር መብቶችና ግዴታዎች በተግባር ተፈፃሚ እንዲሆኑ ካልተደረገ የመኖራቸው ጉዳይ ትርጉም የለሽ ይሆናል ማለት ነው። እነዚህ መደበኛና ልዩ መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች እንዲፈፀሙ የማድረጉ ሐላፊነት የሥነ-ሥርዓት ሕግ ቢሆንም ውጤታማ የሥነ-ሥርዓት ሕግ ከሌለ ግን መብቶችንና ግዴታዎችን የማስፈፀሙ ዓላማ እረብ የለሽ ይሆናል። ለዚህም ነው የሥነ-ሥርዓት ሕግ ከመሠረታዊው ሕግ ባላነሰ አስፈላጊና ጠቃሚ ነው የሚባለው።
The applicability of international frameworks, in general, depends initially on the status a given country gives to international instruments in its legal system. Its commitment begins with the clear statement it makes regarding the status and application of those ratified instruments. This is why usually States determine in their domestic legislations status related issues such as incorporation, hierarchy, implementation mechanisms, implementing institutions, etc of international instruments. This topic briefly discusses the status and applicability of juvenile justice related international instruments, particularly the ACRWC and the CRC, in Ethiopia.
ማሪዮን ጆንስ፣ ማሪያ ሻራፖቫ፣ ክላውዲያ ፔከንስታይ እና ላንስ አርምስትሮንግን የሚያመሳስላቸው አንዱ በስፖርቱ ዓለም ገናና ስም የነበራቸው መሆኑ ነው፡፡ ማሪዮን ጆንስ የኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ ናት፡፡ አርምስትሮንግ ደግሞ በብስክሌት ግልቢያ የሚያህለው አልነበረም፡፡ ማሪዮን ጆንስ አጭሩን ርቀት በሚያስገርም ፍጥነት ታጠናቅቅ ነበር፡፡ የአሸናፊነት ምልክትም ሆና ለብዙ ዘመን ቆይታለች፡፡ አርምስትሮንግም እንዲሁ፡፡ ከችሎታውና ብቃቱ የተነሳ ስፖንሰሩ ለመሆን ያልተሯሯጠ ኩባንያ አልነበረም፡፡
An interesting article, published on Jimma University Journal of Law, entitled “the immediate appealability of a court order against arbitration: it should be allowed and even made compulsory”, argues that an immediate appeal against a court order which is against arbitration must be allowed; article 320/3/ of the Civil Procedure Code should be amended to take the special nature of arbitration into account.
የማንነት ጥያቄ ምንድን ነው? የድንበር አከላለል ለውጥ (የድንበር ውዝግብ) ጥያቄስ ምንድን ነው? የኢትዮጵያ ሕግስ እንዴት ነው የሚጠብቃቸው? የዚህ ማስታወሻ ዓላማ እነዚህን ጉዳዩች ስለሚመለከቱት የሕግ ክፍሎች በማጥናትና ስለአተረጓጎማቸው አስተያየት በማቅረብ እነዚህን ጥያቄዎች መመለስ ነው፡፡ ከእነዚህ ባሻገር ይህ ማስታወሻ ስለ ትግራይ ሕዝብ መልክዓ ምድራዊ አሰፋፈር ታሪካዊ ዳሰሳ ባጭሩ አድርጓል፡፡
በዚህ ጽሑፍ ስለ ግብር ስወራ ምንነት፣ በተለያዩ የግብር ዓይነቶች ሥር የግብር ስወራ ስለሚያቋቋሙ ድርጊቶች፣ ለግብር ስወራ መነሻ ሊሆኑ ስለሚችሉ ምክንያቶች እንዲሁም የመከላከያ መንገዶቹ ለመዳሰስ እሞክራለሁ፡፡ ይህንን ጽሑፍ ለመጻፍ መነሻ የሆነኝ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የጉምሩክና ታክስ ወንጀል ችሎት ዳኛ ሆኜ ስሠራ በነበርኩበት ጊዜ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ለግብር ስወራ የወንጀል ክሶች ለማስረዳት ሲያቀርባቸው በነበሩ የታክስ ኦዲቶች ላይ የሚጠቀሱ ግኝቶች ናቸው፡፡ የተለያዩ የግብር ስወራ ወንጀሎች ፈጽመዋል በማለት ተከሰው በፍርድ ቤት ሲቀርቡ ለነበሩ ተከሳሾች ይቀርብ የነበረው ማስረጃ፣ በታክስ ኦዲተሮች የሚሠራ የታክስ ኦዲት ግኝቶች ዝርዝር የሚገልጽ የጽሑፍ ማስረጃ እንዲሁም ይህንኑ የታክስ ኦዲት የሠሩ ባለሙያዎች በሙያ ምስክርነት ቀርበው የሚሰጡት የምስክርነት ቃል በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡