Recent Blog Posts - Blog - Page 26

በኮንስትራክሽን ውሎች አፈጻጸም ወቅት ለሚስተዋሉ ጉዳቶች (Risks) ተጠያቂ ማን ነው?

“All courses of action are risky, so prudence is not in avoiding danger (it’s impossible), but calculating risk and acting decisively. Make mistakes of ambition and not mistakes of sloth. Develop the strength to do bold things, not the strength to suffer.” 

Niccolo Machiavelli, The Prince

  18294 Hits
Tags:

Letters of Credit in General

Letter of credit transactions have been developed since the Middle Ages in connection with the trade of goods at the international level. Individuals and companies have found themselves dealing with partners of whom they know little, located in distant countries with often insecure political and economic situations. Furthermore, the dynamism of the economy creates a need for financing that requires a guarantee of payment at a time and for an amount that must be certain. Diversity in geographical nature, weather, climate, production system, and globalization in culture and fashion has made the countries dependent on each other for the daily necessities. Similarly, one continent is largely dependent on the products of other continents. In addition, diversity in human appetite and attitude, unequal development of technology, desire for luxury, and the development of communication systems and tale-communication revolutionarily increase the necessity of transnational, transcontinental business activities.

  24854 Hits

የልማድ አቤቱታ የፍርድ ጥራት ላይ ያለው ተፅዕኖ

መኳንንት ከሕግ ትምህርት ቤት ተመርቆ ሲወጣ ግር ያለው ነገር የትምህርቱና የአተገባበሩ ልዩነት ነው፡፡ በአብዛኛው በንድፈ ሐሳብ አስተምህሮና ትንተና ላይ የሚተኮረው ትምህርቱ በተግባር ከሚታየው የፍርድ ቤት ነባራዊ ሁኔታ ጋር አልታረቅ ብሎት ተቸግሯል፡፡ ይህን ችግሩን ያባባሰው ደግሞ ከቤተሰቡ አንዱ የወራሽነት የምስክር ወረቀት ከፍርድ ቤት እንዲሰጠው በማሰብ አቤቱታውን እንዲያዘጋጅለት ሲጠይቀው ነው፡፡ አቤቱታውን አዘጋጅቶ ለቤተሰቡ አባል ቢሰጠውም በአንዱ ክልል ከሚገኘው የወረዳ ፍርድ ቤት የገጠመው ነገር ሌላ ነው፡፡ ቤተ ዘመዱ በፍርድ ቤቱ አቤቱታው በትክክል አለመጻፉ ተነግሮት በፍርድ ቤቱ ደጃፍ ከሚገኙት ራፖር ጸሐፊ ተጽፎ እንዲመጣ ተመከረ፡፡ ሰውየውም የተባለውን ፈጽሞ አቤቱታው ተቀባይነት አግኝቶ የወራሽነት የምስክር ወረቀት አገኘ፡፡ የመኳንንትና የራፖር ጸሐፊው አቤቱታ ልዩነት ቀላል ነበር፡፡

  14062 Hits

የሰበር ፍርድ ያለማክበር ልማድና ውጤቱ

ጸሐፊው በሚከታተለው አንድ የንግድ ችሎት ጉዳይ ጠበቃው የችሎቱን ዳኛ ያማርራል፡፡ የዳኛውን የችሎት አካሄድ እየተቸ በዕለቱ በሰጠው ፍርድ ጠበቃው ለጉዳዩ ጠቃሚ የሆነውን የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ የሕግ ትርጉም የችሎቱ ዳኛ በፍርዱ አለማካተቱ፣ ለጉዳዩ አግባብነት ያለው መሆኑንና ይዘቱንም በፍርዱ ለማንፀባረቅ ፈቃደኛ አለመሆኑ እጅጉን አንገብግቦታል፡፡ እንደ ጠበቃው አነጋገር ‹‹ከሳሾች ባቀረቡት ክስ ለጉዳዩ አግባብነት ያለውን የሰበር ችሎት ቅጹን፣ የመዝገብ ቁጥሩንና ቀኑን አመልክተን አቀረብን፣ በቃል ክርክርም ይህንኑ በአጽንአት እንዲመዘገብልን አመለከትን፤›› ይላል፡፡ ውጤቱን ሲገልጽ ደግሞ ዳኛው በፍርዱ ሀተታውም ሆነ ትንታኔ የሰበር ችሎቱን ፍርድ አልገለጸም፣ የሰጠውም ፍርድ ሰበር ችሎቱ ከሰጠው አስገዳጅ ትርጓሜ ጋር የሚጋጭ በመሆኑ በይግባኝ ከማሳረም ውጭ አማራጭ እንደሌለው ተናገረ፡፡ 

  11772 Hits

በኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነ ሥርዓት የቀዳሚ ምርመራ ድንጋጌዎችና አተገባበራቸው አጭር ዳሰሳ

የወንጀል ክስን በማስረጃ አስደግፎ በማረጋገጥ እና ተከሳሽን ወደ ፍርድ ቤት በማቅረብ ጥፋተኛ ማስደረግ በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ትልቅ ጥረትና ድካም የሚጠይቅ ተግባር ነው፡፡ አንድ ወንጀል ማህበረሰቡ ላይ ሲፈጸም ወንጀሉን የፈጸመን አካል ነቅሶ በማውጣት ለፍርድ በማቅረብ ማስቀጣት የመንግሥት ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ አንድ መንግሥት የሕዝብን  ሥልጣን  ሲቀበል  የማህበረሰቡን  ሰላም  መጠበቅ ከሕዝቡ የተጣለበት  ግደታው  ነው፡፡ ይህንን ሰላም ለመጠበቅ  ደግሞ  ወንጀል  እንዳይፈፀም ይከላከላል፡፡ ከተፈፀመ በኋላ ፈፃሚውን ለሕግ ያቀርባል፣ ወንጀል ለመፈፀሙ ሊያሥረዱ የሚችሉ ማስረጃወችን አብሮ ያቀርባል፡፡

  27752 Hits

ዳኞች፣ ዐቃቤ ሕጎች፣ ጠበቆች እና ፖሊሶች ሊዘነጓቸው የማይገቡ የወንጀል ሥነ ሥርዓት ሕግ መርህዎች

መንግሥት የሃገርን ሰላምና ደህንነት የመጠበቅ እና የማስጠበቅ እንዲሁም የሕዝቦቹን እና የነዋሪዎቹን መሠረታዊ የግለሰብና የቡድን ነፃነት መብት እና ጥቅም የማክበርና የማረጋገጥ ግንባር ቀደም ኃላፊነትና ሚና አለበት፡፡ ይህንን ኃላፊነቱን ለመወጣት ከሚያከናውናቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት መካከል በግልጽ በሚመራ ሥርዓት የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ማዕቀፍን መዘርጋትና ማቋቋም አንዱና ዋነኛው ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ማዕቀፍን ከሚያቋቁሙ ምሰሶዎች መካከል የወንጀል ሕግ፣ የወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕግ እና የማስረጃ ሕግ በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ፡፡

  27821 Hits

የ‹‹ያስቀርባል … አያስቀርብም›› እንቆቅልሽ

ዶ/ር ትዝታ በፌዴራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ጉዳዩዋን ለመከታተል በችሎት ታድማለች፡፡ በሥር ፍርድ ቤት በቤቷ ላይ ያለአግባብ ፍርድ ተሰጥቷል ብላ ስላመነች የተማረ ጠበቃ የይግባኝ አቤቱታ ጽፎላት ጉዳይዋን በራሷ ትከታተላለች፡፡ እንደ እርሷ አስተሳሰብ ጉዳይዋን ከእርሷ ይልቅ የሚረዳው የለም በሚል ከዳኛ ፊት ቀርባ ለማስረዳት ጓጉታለች፡፡ በዛሬው ቀጠሮ ይህ ሐሳቧ እንደሚሳካላት በውጭ የሚያማክራት ጠበቃ ነግሯታል፡፡

  17215 Hits

ሰበር በአዲስ አበባ ፍርድ ቤት ሥልጣን ላይ ያሰመረው ቀጭን መስመር

የአዲስ አበባ ፍርድ ቤት ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ሥልጣናቸውን የተመለከቱ የተለያዩ ክርክሮች ተነስተዋል፡፡ ዋናው ክርክር በተቋቋመበት ወቅት የተነሳው የሕገ መንግሥታዊነት ጭብጥ ነው፡፡ ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 78 እስከ 80 የዳኝነት አካሉን ሲያዋቅር በተለያዩ ደረጃዎች ያሉት የፌዴራልና የክልል ፍርድ ቤቶች እንደሚቋቋሙ በመግለጽ የፍርድ ቤት ሥልጣን ከመደበኛ ፍርድ ቤቶች የሚወሰዱ ጊዜያዊና ልዩ ፍርድ ቤቶች እንደማይቋቋሙ ደንግጓል፡፡

  15791 Hits

 አንድ አንድ ነጥቦች ስለ ቼክ እና በተግባር የሚያጋጥሙ የሕግና የአሰራር ችግሮች

ቼክ በተግባር በሰፊው ከሚሰራባቸውና በሕግ ከተቀመጡት ንግድ ሰነዶች አንዱና ዋነኛው ነው፡፡  በቼክ ላይ እምነት የሚታጣበት ከሆነ የንግድ ዝውውር ደህንነት (security of transaction) ላይ ሊያሳድር የሚችለው ተፅዕኖ እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡ የንግድ ሥራው እያደገ በመጣ ቁጥር በቼክ የሚደረጉ የንግድ ልውውጦች የሚጨምሩ እንደሚሆን የሚታመንና በተግባርም የሚታይ ነው፡፡ የቼክ ዝውውር እየጨረ እንደመጣም መገመት አያዳግትም፡፡ እየጨመረ የመጣውን የቼክን ዝውውር አስተማማኝነት ለማሳደግ ሕጎች ሥርዓቱን ሊቆጣጠሩት ይገባል፡፡ በዚህም መሠረት በእኛ ሀገር የንግድ ሕጉ እና የወንጀል ሕጉ ይህንኑ የቼክ ጉዳይ በዋናነት ይህን ሥርዓት ዘርግተው ይገኛሉ፡፡ ባብዛኛው የቼክ ጉዳይ የሚያከራክር ጉዳይ የሌለበት ቢሆንም አልፎ አልፎ ግን አከራካሪ ጉዳዮች መታየታቸው አልቀረም፡፡ ይህ ጽሑፍ ዓላማውም በቼክ ዙሪያ ያሉትን አስፈላጊ የሕግ ድንጋጌዎችንና አስገዳጅ የፍርድ ውሳኔዎችን ማሳወቅና በተወሰነ መልኩም ቢሆን ለአከራካሪ ጉዳዮች የጸሐፊውን እይታ ማንፀባረቅ ነው፡፡

  26818 Hits
Tags:

ሰበር ለመታረቅ በተደረገ ስምምነት ላይ የያዘው አቋም ሲፈተሽ

ኢትዮጵያ ውስጥ የዳኝነት ሥልጣን ያላቸው ፍርድ ቤቶች ብቻ አይደሉም፡፡ ይህን ሥልጣን የተጎናፀፉ ብዙ አካላት አሉ፡፡ ለአብነት ያህል ለመጥቀስ፡- በፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር ውስጥ የሚገኘው የአስተዳደር ፍርድ ቤት ከሥራ መሰናበት፣ ደመወዝ መቁረጥና የመሳሰሉትን ጥያቄዎች አስመልክቶ በመንግሥት ሠራተኛውና  በፌዴራል መንግሥት መሥሪያ ቤት መካከል የሚነሳ አለመግባባት ላይ ዳኝነት ይሰጣል፡፡ ሕገ መንግሥቱን መተርጎም ላይ አለመግባባት ከተፈጠረ ዳኝነት የመስጠት ሥልጣን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ነው፡፡ በግብር ጉዳዮች ላይ የግብር ይግባኝ ሰሚ ኮሚሽን የዳኝነት ሥልጣን አለው፡፡ የማኅበራዊ ዋስትና መብትና ጥቅም  ጥያቄዎች ላይ የዳኝነት ሥልጣን ለማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ ተሰጥቷል፡፡ የከተማ ቦታ ማስለቀቅና የካሳ ጉዳዮች ላይ የዳኝነት ሥልጣኑ በየከተማ አስተዳደሮች ለሚቋቋሙ ጉባዔዎች ተሰጥቷል፡፡ የንግድ ውድድር ጨቋኝ የሆኑ ድርጊቶችና ያልተገባ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ደግሞ ዳኝነት የሚሰጥ የንግድ አሠራርና የሸማቾች ጥበቃ ባለሥልጣን የሚባል ተቋም አለ፡፡ ወታደራዊ ፍርድ ቤቶችም አሉ፡፡ ይሁን እንጂ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ያለውን የዳኝነት ሥልጣን ያህል የተጎናፀፈ ፍርድ ሰጪ አካል ኢትዮጵያ ውስጥ የለም ለማለት ያስደፍራል፡፡ የዚህን ችሎት የዳኝነት ሥልጣን ሊወዳደር ወይም ሊበልጥ የሚችል ፍርድ ሰጪ አካል ኢትዮጵያ ውስጥ ካለ፣ የሕገ መንግሥት ትርጓሜ ላይ ዳኝነት የመስጠት ሥልጣን ያለው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ብቻ ነው፡፡

  10976 Hits