የሰበር ፍርድ ያለማክበር ልማድና ውጤቱ

 

ጸሐፊው በሚከታተለው አንድ የንግድ ችሎት ጉዳይ ጠበቃው የችሎቱን ዳኛ ያማርራል፡፡ የዳኛውን የችሎት አካሄድ እየተቸ በዕለቱ በሰጠው ፍርድ ጠበቃው ለጉዳዩ ጠቃሚ የሆነውን የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ የሕግ ትርጉም የችሎቱ ዳኛ በፍርዱ አለማካተቱ፣ ለጉዳዩ አግባብነት ያለው መሆኑንና ይዘቱንም በፍርዱ ለማንፀባረቅ ፈቃደኛ አለመሆኑ እጅጉን አንገብግቦታል፡፡ እንደ ጠበቃው አነጋገር ‹‹ከሳሾች ባቀረቡት ክስ ለጉዳዩ አግባብነት ያለውን የሰበር ችሎት ቅጹን፣ የመዝገብ ቁጥሩንና ቀኑን አመልክተን አቀረብን፣ በቃል ክርክርም ይህንኑ በአጽንአት እንዲመዘገብልን አመለከትን፤›› ይላል፡፡ ውጤቱን ሲገልጽ ደግሞ ዳኛው በፍርዱ ሀተታውም ሆነ ትንታኔ የሰበር ችሎቱን ፍርድ አልገለጸም፣ የሰጠውም ፍርድ ሰበር ችሎቱ ከሰጠው አስገዳጅ ትርጓሜ ጋር የሚጋጭ በመሆኑ በይግባኝ ከማሳረም ውጭ አማራጭ እንደሌለው ተናገረ፡፡ 

ከሰኔ 1997 .. ጀምሮ በአገራችን የሰበር ችሎት የሚሰጠው ትርጉም በሥር ፍርድ ቤቶች ላይ አስገዳጅ መሆኑ በሁሉም የሕግ ባለሙያዎች ዳኞችን ጨምሮ የታወቀ ነው፡፡ በተግባር ግን ጠበቃው የገጠመውን ዓይነት የፍርድ ቤቶች ልማድ ማስተዋል የተለመደ ነው፡፡ አፈጻጸሙን በተመለከተ ግን አሁንም ያልጠሩ ወይም የማይፈጸሙ አሠራሮች መኖራቸውን የጠበቃው ተሞክሮ ያሳያል፡፡ ለመሆኑ የሥር ፍርድ ቤት ዳኞች የሰበር ሰሚ ችሎት የሰጣቸውን አስገዳጅ ፍርዶች ማወቅ (Judical notice መውሰድ) ይጠበቅባቸዋልን? የሰበር ሰሚ ችሎት አስገዳጅ ፍርዶች ባልታተሙበት ሁኔታ አስገዳጅነት አላቸውን? አንድ የሥር ፍርድ ቤት ዳኛ የሰበር አስገዳጅ ፍርድ ተጠቅሶላት የማይቀበልበት ሁኔታ ይኖራልን? አስገዳጅ የሰበር ትርጉምን ወደ ጎን ማድረግ፣ አለመቀበል ወይም ከተሰጠው ትርጉም ተቃራኒ የሆነ ፍርድ መስጠት ዳኞችን በሥነ ምግባር አያስጠይቃቸውምን? የሚሉት ነጥቦች ምላሽ የሚፈልጉ ናቸው፡፡ በዚህ ጽሑፍ እነዚህን ነጥቦችና ከሰበር ችሎት ፍርድ አስገዳጅነት ጋር የተያያዙ አንዳንድ ነጥቦችን ለማንሳት እንሞክራለን፡፡ 

አዋጅ ቁጥር 454/97 ዓላማውና ይዘቱ

ይህ አዋጅ በአንቀጽ 4 ላይ ‹‹የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከአምስት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት የሚሰጠው የሕግ ትርጉም በየትኛውም ደረጃ ላይ በሚገኝ የፌዴራል ወይም የክልል ፍርድ ቤት ላይ አስገዳጅነት ይኖረዋል፡፡ ሆኖም የሰበር ችሎቱ በሌላ ጊዜ በተመሳሳይ ጭብጥ የተለየ ትርጉም ሊሰጥ ይችላል፤›› ሲል ይደነግጋል፡፡ በዚህ ድንጋጌ መሠረት የሥር ፍርድ ቤቶች ሰበር ችሎቱ የሰጠውን የሕግ ትርጉም የመከተል፣ የመተግበር ግዴታ አለባቸው፡፡

Continue reading
  7410 Hits

የልማድ አቤቱታ የፍርድ ጥራት ላይ ያለው ተፅዕኖ

 


መነሻ ነገር

መኳንንት ከሕግ ትምህርት ቤት ተመርቆ ሲወጣ ግር ያለው ነገር የትምህርቱና የአተገባበሩ ልዩነት ነው፡፡ በአብዛኛው በንድፈ ሐሳብ አስተምህሮና ትንተና ላይ የሚተኮረው ትምህርቱ በተግባር ከሚታየው የፍርድ ቤት ነባራዊ ሁኔታ ጋር አልታረቅ ብሎት ተቸግሯል፡፡ ይህን ችግሩን ያባባሰው ደግሞ ከቤተሰቡ አንዱ የወራሽነት የምስክር ወረቀት ከፍርድ ቤት እንዲሰጠው በማሰብ አቤቱታውን እንዲያዘጋጅለት ሲጠይቀው ነው፡፡ አቤቱታውን አዘጋጅቶ ለቤተሰቡ አባል ቢሰጠውም በአንዱ ክልል ከሚገኘው የወረዳ ፍርድ ቤት የገጠመው ነገር ሌላ ነው፡፡ ቤተ ዘመዱ በፍርድ ቤቱ አቤቱታው በትክክል አለመጻፉ ተነግሮት በፍርድ ቤቱ ደጃፍ ከሚገኙት ራፖር ጸሐፊ ተጽፎ እንዲመጣ ተመከረ፡፡ ሰውየውም የተባለውን ፈጽሞ አቤቱታው ተቀባይነት አግኝቶ የወራሽነት የምስክር ወረቀት አገኘ፡፡ የመኳንንትና የራፖር ጸሐፊው አቤቱታ ልዩነት ቀላል ነበር፡፡ የመኳንንት አቤቱታ ፍሬ ነገሩን በአጭር የሚገልጽ፣ የሕግና የማስረጃ ትንተና የሌለው፣ ግልጽ ዳኝነትን የሚጠይቅ ነበር፡፡ የራፖር ጸሐፊው አቤቱታ ግን ረዥም፣ ውስብስብ የሕግ ቃላትን የሚጠቀም፣ በብዙ የሕግ ድንጋጌ የተዘበዘበ ነበር፡፡ ይህን የተረዳው መኳንንት አምስት ዓመት የተማረበት የሕግ ትምህርት ሥልጠና የማይፈልግና በፍርድ ቤት ተግባራዊ ረብ የሌለው መስሎት ተከዘ፡፡ የተወሰኑ ዓመታትን በሕግ ሙያ አገልግሎት ካሳለፈ በኋላ ግን ለዘመናት የዳበረውን ልምድ መስበር አስቸጋሪ ስለመሰለው ራሱን በተወሰነ ደረጃ ከተለመደው አሠራር ጋር አቀራረበ፡፡ አሁን ለአቤቱታ ርዝመት ጭንቀት የለውም፣ የሕግ ድንጋጌዎችን በዓይነት ለመዘብዘብ፣ የሕግና የማስረጃ ትንታኔዎችን ለማግተልተል ቀዳሚ አይገኝለትም፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ፍርድ ቤቶች የአሠራር ማሻሻያ በማድረግ፣ የሬጅስትራርና ተያያዥ ሥራዎችን የሚሠሩ ሰዎች ከሕግ ትምህርት ቤት የተመረቁ፣ የሕግ ሥልጠና ያገኙ መሆናቸው የተወሰነ ለውጥ ማምጣቱን ያምናል፡፡ ያም ሆኖ አሁንም የአቤቱታ ፎርም፣ ይዘት፣ እና ሕጋዊ ብቃት አሰፋፈር/አተያይ ላይ ምሉዕ ለውጥ አለመምጣቱን መኳንንት ያምናል፡፡ ሰሞኑን ያጋጠመው የሬጅስትራር ሠራተኞች ድርጊት ለዚህ አስረጅ ነው፡፡ መኳንንት ሕጉን ተከትሎ ያዘጋጀውን የመከላከያ መልስ ምንም ዓይነት የሕግ ድንጋጌ ያልጠቀሰ መልስ የሕግ አቤቱታ አይሸትም ሲሉት እጅጉን ተበሳጨ፡፡ ጸሐፊውም ይህን በሰማ ጊዜ ትንተና ባይበዛውም በዚህ ጽሑፍ የአቤቱታን ምንነት፣ መሥፈርት፣ የብቃት አተያይ በአጭሩ ለግንዛቤ በሚመች መልኩ ለመዳሰስ ሙከራ አደረገ፡፡

አቤቱታ ምንድን ነው?

በዕለት ተዕለት የሕይወት ተሞክሮ ለማንኛውም አካል በቃል ወይም በጽሑፍ የሚቀርብ ጥያቄ፣ ማመልከቻ፣ ይግባኝ አቤቱታ ይባላል፡፡ በሕግ ሙያ ግን ‹‹አቤቱታ›› ወይም ‹‹Pleading›› የሚለው ቃል በፍርድ ቤት የሚቀርብ ማመልከቻን ሁሉ የሚያካትት አይደለም፡፡ ፍርድ ቤት ለመዋሉ ማስረጃ የሚጠይቅ፣ የውሳኔ ግልባጭ እንዲሰጠው የሚጠይቅ ወዘተ በሕጉ ቃል አቤቱታ አቅርቧል ለማለት አያስችልም፡፡ ለቃሉ ፍቺ የሚሰጠው ብላክስ የሕግ መዝገበ ቃላት ‹‹Pleading is a formal document in which a party to a legal proceeding (esp. a civil lawsuit) sets forth or responds to allegations, claims, denials or defenses›› በሚል ይገልጸዋል፡፡ በዚህ ትርጉም መሠረት አቤቱታ ማለት በአንድ የሕግ ሙግት ተከራካሪ የሆነ ወገን ሙግት ለመጀመር ወይም ለቀረበ ጥያቄ፣ ዳኝነት፣ ክህደት ወይም መከላከያ መልስ ለመስጠት የሚያቀርበው መደበኛ ሰነድ ነው፡፡ በዚህ ፍቺ መሠረት አቤቱታ መብት የሚጠየቅበት ወይም ለቀረበ ጥያቄ መልስ የሚቀርብበት ነው፡፡

Continue reading
  9606 Hits

ጥንቃቄ የሚፈልገው ዳኞችን የመሾም ሥርዓት

በማንኛውም አገር የመንግሥት አስተዳደር ከሕግ አውጪውና ከሕግ አስፈጻሚው እኩል የዳኝነት አካሉ አደረጃጀት፣ አወቃቀርና ጥንካሬ የሥርዓቱን ዴሞክራሲያዊነት ይወስናል፡፡ የዳኝነት አካሉ ገለልተኛና ነፃ ባልሆነ መጠን የሥርዓቱ ዴሞክራሲያዊነት ዋጋ ያጣል፡፡ የዳኝነት አካሉ መሠረታዊ ሕገ መንግሥታዊ መርሆችን ለማስፈጸም፣ የዜጎች የሰብዓዊ መብቶች እንዲጠበቁና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን ገለልተኛ፣ ግልጽ አሠራርን የሚከተልና ጠንካራ እንዲሆን ያስፈልጋል፡፡ 1987 .. የወጣው ሕገ መንግሥታችን በአንቀጽ 78 እና 79 እነዚህ መሠረታዊ የዳኝነት አካሉ መገለጫዎችን ደንግጓል፡፡ ይሁን እንጂ ሕገ መንግሥቱ ከወጣ 25 ዓመታት በኋላም የዳኝነት አካሉ የአሠራር ግልጽነትና ተጠያቂነት አመርቂ እንዳልሆነ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ይስማማሉ፡፡ ለዚህ ነው የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት 2015 . በሕዝብ ታማኝነት ያለው የዳኝነት አካል ለመሆን ራዕይ ይዞ የሚንቀሳቀሰው፡፡ 15 ቀናት በፊት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፀደቀው የዳኝነት ሹመት ጋር በተያያዘ በሕግ ባለሙያዎች በየዐውዱ የሚደረገው ክርክር የዚህ አንዱ መገለጫ ነው፡፡ ኃይለ ገብርኤል መሐሪ የተባሉ ጸሐፊ ሰኔ 26 ቀን 2008 .. በሪፖርተር ጋዜጣ የአስተያየት አምድ ‹‹ግልጽነት የጎደለው የዳኞች ምልመላ›› በሚል በጻፉት ጽሑፍ የተሾሙት ዳኞች ምልመላ በአጭር ጊዜ የተፈጸመ፣ በቂ ፈተናና ግምገማ ያልተደረገበት፣ የሕዝብ አስተያየት በአግባቡ ያልተወሰደበትና ግልጽነት የጎደለው እንደነበር ይገልጻሉ፡፡ ጸሐፊውን ጨምሮ በፍርድ ቤቶች አካባቢ የሚታዩ ጠበቆችም የዳኞቹ አመላመልና ሹመት ጋር በተያያዘ ሊታዩ የሚገቡ ነጥቦች እንዳሉ ያምናሉ፡፡

የዳኞች አመላመልና አሿሿም የዳኝነት አካሉን ነፃነት ከሚያረጋግጡ ቅድመ ሁኔታዎች ዋናው ነው፡፡ ዳኞችም ከማንኛውም ቀጥተኛም ሆነ ተዘዋዋሪ ተፅዕኖ ነፃ በመሆን ፍትሕ እንዲሰፍን የሚሠሩት ምልመላውና አሿሿሙ ግልጽና ተጠያቂነት ሲኖረው ነው፡፡ የዳኞች አሿሿም የዳኝነት አካሉን ነፃነት ከሚያስገኙ የገለልተኝነት፣ የብቃት፣ የሃቀኝነትና የነፃነት እሴቶች ጋር እጅጉን ይቆራኛል፡፡ የዳኝነት አካሉ በኅብረተሰብ ውስጥ ተገቢውን ቦታ እንዲያገኝ በግልጽነት የዳኞችን የመሾም ሥርዓት ሊያከናውን ይገባል፡፡ ይህ የሚሳካው ደግሞ የዳኞች የአመራረጥና የአሿሿም ዘዴ፣ የሚመረጡ ዳኞች ዕውቀትና ልምድ በጥንቃቄና በኃላፊነት ሲከናወን ነው፡፡ በዚህ ጽሑፍ ከዳኝነት አሿሿም ጋር በተያያዘ ጥንቃቄ የሚፈልጉ አንዳንድ ነጥቦችን ለመመልከት እንሞክራለን፡፡

የዳኝነት አሿሿም ዘዴዎች

የዳኝነት አሿሿም እንደ አገሮቹ የፖለቲካ ባህልና ማኅበራዊ እሴት ይለያያል፡፡ አንድ ወጥ የአሿሿም ሥርዓት የለም፡፡ ማንኛውንም የአሿሿም ሥርዓት የሚከተል አንድ አገር የዳኝነት አካሉ ነፃ እንዲሆን የአሿሿም ሒደቱ ግልጽና ኅብረተሰቡን ያሳተፈ ሊሆን ይገባዋል፡፡ ግልጽነትና የሕዝብ ተሳትፎ በአሿሿም ካለ ጥራትና ብቃት ያላቸው የሕግ ባለሙያዎች ዳኛ ይሆናሉ፡፡ ኅብረተሰቡ በዳኝነት አካሉ ላይ ያለው መተማመን ይጨምራል፡፡

በተለያዩ አገሮች ተፈጻሚ የሚሆኑ የዳኝነት አሿሿም በደምሳሳው በሁለት ሊከፈል ይችላል፡፡ አንዱ በምርጫ የሚከናወን ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ በመሾም ሥርዓት የሚከናወን ነው፡፡

Continue reading
  7977 Hits

በቀጠሮ ቀን ፍርድ ቤት ያለመቅረብ ውጤቶች

 

ተከራካሪ ወገኖች እራሳቸው ወይም በተወካያቸው አማካይነት ፍርድ ቤት በሚወስነው በማንኛውም ቀጠሮ ቀን ፍርድ ቤት መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ከሳሽ አንድ ጊዜ ጉዳዩን ይዞ ከቀረበ በኋላ ተከታትሎ ከዳር ማድረስ መቻል ያለበት ሲሆን ተከሳሽም በእያንዳንዱ ቀጠሮ እየቀረበ የቀረበበትን ክስ በአግባቡ መከላከል መቻል አለበት፡፡ክስ ያቀረበ ሰው በሁሉም ቀጠሮዎች ንዲገኝ የሚጠበቅበት ቢሆንም በተያዘው ቀጠሮ ባለመገኘቱ ምክንያት ያቀረበውን ክስ መዝጋት ጨምሮ እንደ ቀጠሮው ምክንያት ሌሎች ትእዛዞች ሊሰጡ ይችላሉ፡፡ ክሱ ሊዘጋ የሚችለው ሕጉ ለይቶና ዘርዝሮ ባስቀመጣቸው ምክንያቶችና ጋጣሚዎች ብቻ ነው፡፡ የፍርድቤት ክርክር በከሳሽ እና ተከሳሽ ይሁንታ ላይ ተመስርቶ በፈለጉ ቀን የሚቀርቡበት ደስ ካላላቸው ደግሞ የማይቀርቡበት ሂደት አይደለም፡፡

ንድን ጉዳይ ለማየት የተሰየመ /ቤት የተለያዩ ክንዋኔዎችን ለመፈፀም በርካታ ቀጠሮዎች ንደሚሰጥ የታወቀ ነው፡፡ በሙግት ሂደት ፍርድ ቤት የተለያዩ ጉዳዮች መከናወናቸውን ለማረጋገጥ የተለያዩ ቀጠሮዎችን ይሰጣል ይላል የፌደራል ጠቅላይ ፍርድቤት ሰበር ሰሚ ችሎት መዝገብ ቁጥር 14184፡፡ ንድን ጉዳይ ይቶ ውሣኔ ለመወሰን በርካታ ቀጠሮዎችን ፍርድ ቤት ንደሚሰጥ የሚታወቅ ሲሆን ከነዚህ በርካታ ቀጠሮዎች መካከል ንዱ ወይም በሌላኛው ወይም በሁለቱም ለመቅረብ ምክንያት ፍርድ ቤት የተለያዩ ትዕዛዞችን እንደሚሰጥ አትቶታል መዝገቡ፡፡ የቀጠሮ ለመከበር ቀጠሮ ከተሰጠበት ምክንያት ተነጥሎ የሚታይ ባለመሆኑ የቀጠሮውን ምክንያት ከግምት በማስገባት የሚሰጠውም ትእዛዝ የተለያየ ነው፡፡

አንድ የፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ተከራካሪ ወገኖች ክሱ በማንኛውም ደረጃ ላይ ባለበት ጊዜ መቅረብ ባይችሉ ተፈፃሚ ሊሆኑ የሚችሉ ድንጋጌዎች ነዚህን ሁኔታዎች በቅጡ ለመገንዘብ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጋችን የከሣሽ ና/ወይም የተከሣሽ ለመቅረብ (non appearance of parties) ስመልክቶ ያስቀመጠውን ሥርዓት ጠቃላይ የሙግት ሂደት ጋር ገናዝቦ መመልከቱ ጠቃሚ ነው ይላል የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ጉዳዩን በተመለከቱ ፍርዶቹ፡፡

በዚህ ጽሑፍም ፍርድ ቤት ከሚሰጣቸው የተለያዩ ቀጠሮዎች እና ውጤታቸው ጋር በተያዘ የፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጉን ድንጋጌዎች እና የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎችን ለመዳሰስ ተሞክሯል፡፡

Continue reading
  21322 Hits

የቴምብር ቀረጥ የሚከፈልባቸውና የማይከፈልባቸው ግብይቶች

 

መንግሥት ገቢ ከሚሰበሰብባቸው ምንጮች መካከል የቴምብር ቀረጥ አንዱ ነው፡፡ የቴምብር ቀረጥ ቀጥተኛ ያልሆነ ታክስ ሲሆን፣ የሚሰበሰበውም በተወሰኑ ሰነዶች ላይ እንዲለጠፍ ወይም እንዲከፈል በማድረግ ነው፡፡

በአገራችን የቴምብር ቀረጥ የተጣለው ስለ ቴምብር ቀረጥ አከፋፈል በወጣው አዋጅ ቁጥር 110/90 መሠረት ነው፡፡ የዚህ አዋጅ አፈጻጸም በተለያዩ ባለድርሻ አካላት መካከል ያለው አሠራር ተመሳሳይ አይደለም፡፡ በተግባር በሰነዶች የተለያዩ ግብይቶች (Transactions) የሚፈጸሙ ሰዎች፣ የአገር ውስጥ ገቢ ሠራተኞች፣ ባንኮች፣ ፍርድ ቤቶች ወዘተ የየራሳቸው የአዋጁ አረዳድ አላቸው፡፡ የልዩነቱ ምንጭ አዋጁን ካለማወቅ፣ ከአዋጁ ድንጋጌዎች ይልቅ በልማድ መሥራት፣ እንዲሁም የአዋጁን ክፍተት የሚሟሉ መመርያዎችን አለማወቅ እንደሆነ የተለያዩ ጥናቶች አመልክተዋል፡፡ እነዚህን ችግሮች በመቅረፍ የአዋጁ አፈጻጸም የሕግ አውጪውን መንፈስ እንዲከተል ማስቻል የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ነው፡፡

የቴምብር ቀረጥ የሚከፈልባቸው ሰነዶች

የቴምብር ቀረጥ በሰነዶች ላይ የሚጣል ታክስ ቢሆንም፣ ሁሉም ሰነዶች ላይ የሚጣል አይደለም፡፡ አዋጁ በአንቀጽ 3/12 የተለያዩ ሰነዶችን በመዘርዘር የሚከፈሉበትን ጊዜ፣ ሁኔታና መጠን በግልጽ አመልክቷል፡፡ የአዋጁ ዝርዝር ምሉዕ (Exhaustive) በመሆኑ በማመሳሰል ሌሎች ያልተጠቀሱ (ያልተዘረዘሩ) ሰነዶች ላይ የቴምብር ቀረጥ እንዲለጠፍ ወይም እንዲከፈል መጠየቅ አይቻልም፡፡ የቀረጥ ቴምብር የሚከፈለው በመመሥረቻና መተዳደሪያ ደንብ፣ የግልግል ሰነድ፣ ማገቻ፣ የዕቃ ማከማቻ ማረጋገጫ ሰነድ፣ ውል፣ ስምምነትና የእነዚህ መግለጫ፣ የመያዣ ሰነዶች፣ የኅብረት ስምምነት፣ የሥራ (ቅጥር) ውል፣ የኪራይ፣ የተከራይ አከራይና መሰል መብት የማስተላለፊያ ሰነዶች፣ ማረጋገጫ፣ የውክልና ሥልጣንና የንብረት ባለቤትነትን ማስመዝገቢያ ሰነድ ላይ ነው፡፡ ከእነዚህ ሰነዶች ውጭ ባሉ ሰነዶች ላይ የቴምብር ቀረጥ አይከፈልም፡፡

Continue reading
  16993 Hits
Tags:

ስለማስረጃ ሕግ አደረጃጀት

የማስረጃ ሕግ የማስረጃን አግባብነት፣ የማስረጃን ተቀባይነት እንዲሁም የማስረጃን ክብደትና ብቃት የሚገዙ ደንቦችና መርሆዎች ጥርቅም ነው፡፡ ማስረጃ ተሟጋቾች በአቤቱታቸው አማካኝነት ፍርድ ቤት የያዘውን ጭብጥ የሚያረጋግጡበት ዘዴ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ማስረጃ ማለት ፍርድ ቤት የያዘውን አከራካሪ ጉዳይ ወይም ጭብጥ በሚሰማበት ጊዜ ተሟጋቾች የጥያቄውን አግባብነት፣ እውነትነት፣ በምስክሮች፣ በሠነድ፣ ተጨባጭነት ባላቸው ሌሎች ነገሮች፣ ወዘተ… ማስረጃ ለፍርድ ቤቱ የሚያረጋግጡበት አሊያም ውድቅ የሚያደርጉበት ዘዴ ነው፡፡ ማስረጃ ሲባል የአንድን ፍሬ ነገር ህልው መሆን ወይም አለመሆን ለማረጋገጥ ያገለግል ዘንድ ክስ በሚሰማበት ጊዜ ወይም የክርክር ጭብጥ በሚጣራበት ወቅት በተከራካሪ ወገኖች ወይም ክርክሩን በሚያየው ፍርድ ቤት ትዕዛዝ አማካኝነት የሚቀርብ ማናቸውም ዓይነት የአስረጂነት ባህርይ ያለው ነገር ነው፡፡ ማስረጃ በምስክሮች (Witnesses)፣ በዘገባ (Record)፣ በሠነድ (Document)፣ ተጨባጭነት ባላቸው ሊታዩ ሊዳሰሱ በሚችሉ ነገሮች (Concrete Objects) እና በኤግዚቢት መልክ ሊቀርብ ይቸላል፡፡ አቀራረቡም በሕግ በተደነገገው ሥርዓት መሠረት ነው፡፡ የክርክሩን ጭብጥ ፍሬ ነገር እውነት ወይም ሀሰት መሆኑን የማሳመን ኃይል ያለው እንደመሆኑ እና በዚህም ወደ ውሳኔ የሚያደርሰው ስለሆነ ሊገኝም ሊቀርብም የሚገባው በሕግ አግባብ ነው፡፡ ማስረጃው ተቀባይነት ወይም ውድቅ የሚደረገው እንደዚሁም ሊሰጠው የሚገባው ክብደት የሚመዘነውም በሕግ አግባብ ነው፡፡

ከእነዚህ ትርጓሜዎች እንደምንረዳው “ማስረጃ” የሚለው ቃል አንድን ጭብጥ ለማረጋገጥ አሊያም ውድቅ ለማድረግ የሚያስችል በፍርድ ቤት ዘንድ ተቀባይነት ያለው ማናቸውም ዓይነት የማረጋገጫ ዘዴ ነው፡፡ ተጨባጭነት ባለው መልኩ “ማስረጃ” ማለት ፍርድ ቤት የቀረበለትን ጭብጥ ለመወሰን የሚያስችሉትን ሁኔታዎች የማረጋገጫ ዘዴ ነው፡፡

በአጠቃላይ የማስረጃ ሕግ በፍትሐብሔርም ሆነ በወንጀል ጉዳዮች ለፍርድ ቤት ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ የትኞቹ ተቀባይነት እንዳላቸው የትኞቹ ደግሞ ተቀባይነት እንደሌላቸው የሚደነግግ ሕግ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ተቀባይነት ያላቸው ማስረጃዎች ምን ዓይነት ክብደት እንደሚሰጣቸው በማስረጃ ሕግ ይደነገጋል፡፡ ይህ ሕግ በፍርድ ሂደት የማስረጃ ተቀባይነትን፣ ተገቢነትን፣ ክብደትን እና ብቃትን እንዲሁም የማስረዳት ሸክምን የሚገዙ መርሆችና ደንቦች ተካተው የሚገኙበት የሕግ ክፍል ነው፡፡ ስለ ማስረጃ በጥቅሉ ስንናገር ማናቸውም የቀረበን አከራካሪ ጉዳይ መኖር ወይም አለመኖር ሊያስረዳ የሚችል ነገር ሲሆን ቀጥተኛ ማስረጃን፣ ሠነድን፣ ገላጭ ማስረጃዎችን፣ የእምነት ቃልንና ፍ/ቤት ግንዛቤ የሚወሰድባቸውን ነገሮች ሊጨምር ይችላል፡፡ የማናቸውም ማስረጃ ሕግ አስፈላጊነትና ግብ ለጭብጡ አግባብነት ያላቸውን ነገሮች ለፍርድ ቤቱ በማሳየት ዕውነቱን ማስረዳትና ለሙግቱ ትክክለኛ ፍርድ እንዲሰጥ ማመቻቸት ነው፤ በመሆኑም የማስረጃን ተቀባይነት የሚወስኑት የማስረጃ ሕግ ደንቦች ወይም ድንጋጌዎች ምክንያታዊ መሆን አለባቸው፡፡ የማስረጃ ሕግ ድንጋጌዎቹ ምክንያት የለሽ ከሆኑ መደንገጋቸው ትርጉም የለሽ ይሆናል፤ ድንጋጌዎቹም ያስፈለጉበትንም ግብ አይመቱም፡፡

የማስረጃ ሕግ ዓላማ

የማስረጃ ሕግ አስፈላጊነትና ዓላማ ለጭብጡ አግባብነት ያላቸውን ነገሮች ለፍርድ ቤቱ በማሳየት ዕውነቱን ማንጠርና ለሙግቱ ትክክለኛ ፍርድ እንዲሰጥ ማመቻቸት እንደሆነ ከላይ ተመልክቷል፡፡ በዘመናዊ የፍትሕ አሠራር ፍ/ቤት በሰዎች መካከል የሚፈጠር ክርክርን የሚያስተናግደውና ውሳኔ የሚያስተላልፈው ሌሎች ሕጋዊ ነገሮች እንደተጠበቁ ሆነው በማስረጃ ሕግ መርሆችና ድንጋጌዎች በመመራት ነው፡፡ በእነዚህ መርሆችና ድንጋጌዎች ተመርቶ የተሰጠ ውሳኔ ፍትሕን ያረጋግጣል፡፡ የተደራጁና ምሉዕ የሆኑ መሠረታዊና ሥነ-ሥርዓት ሕጐች ቢኖሩ እንኳን የማስረጃ አወሳሰን መርሆዎች ብቃት ከሌላቸው የውሳኔው ጥራት በገለልተኛነት የተሰጠ መሆኑ አከራካሪ ሊሆን ይችላል፡፡ በመሆኑም የማስረጃ ሕግ ዋንኛው ዓላማ እውነትን አብጠርጥሮ ማውጣት፣ እርግጠኝነቱ ያልታወቀን ነገር፤ በጥቅሉም አከራካሪ ጉዳይን በፍርድ ቤት ማረጋገጥ እና ፍትሕን ማስፈን ነው፡፡

Continue reading
  14948 Hits
Tags:

ስለ ሸሪኣ ፍርድ ቤቶች መልስ የሚሹ ጉዳዮች

 

በተደራጀ እና በብሔራዊ ሕግ ዕውቅና አይሰጣቸው እንጂ በኢትዮጵያ የሸሪኣ ሕግን መሠረት በማድረግ ውሳኔ መስጠት የቅርብ ታሪክ አይደለም፡፡ በታወቀ ሁኔታ እና በመንግሥት ድጋፍ የሸሪኣ ፍርድ ቤቶች የተቋቋሙት ግን በ1934 ዓ.ም. ነው፡፡ ከዚያ ብዙም ሳይቆይ ሕጉ ከሁለት ዓመት በኋላ ተሻሻለ፡፡

ቀጥሎም አገሪቱ በፌደራል ሥርዓት መተዳዳር ከጀመረች በኋላ በ1992 ዓ.ም. እንደ አዲስ የፌደራል ሸሪኣ ፍርድ ቤቶች ተቋቋሙ፡፡ በፌደራል ብቻ ሳይወሰኑ በክልሎቹም እንዲሁ ተቋቋሙ፡፡ ለዚህ ደግሞ ዋና መሠረቱ አሁን በሥራ ላይ ያለው ሕገ መንግሥት ነው፡፡ በአንዳንድ ክልሎች፣ ከመደበኛው ፍርድ ቤት ጎን ለጎን በችሎትነት ሲቋቋሙ በፌደራል ደረጃ ግን ራሳቸውን ችለው የመጀመሪያ ደረጃ፣ ከፍተኛ እና ጠቅላይ ሸሪኣ ፍርድ ቤቶች በመባል ተቋቁመዋል፡፡

የፌደራሉን በአስረጂነት ብንወስድ በየእርከኑ ለሚገኙት ሸሪኣ ፍርድ ቤቶች ተጠሪ ያላቸው ሲሆን የሚያስተዳድራቸውም የጠቅላይ ሸሪኣ ፍርድ ቤት ዋና ቃዲ (ፕሬዚደንት) ነው፡፡ ከዚያ፣ በጥቅሉ ግን ተጠሪነቱ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ነው፡፡ የሚተዳደሩበትን በጀትም በተመለከተ ምንጩ በዋናነት ከመንግሥት ነው፡፡ ዳኞችም በእስልምና ምክር ቤት አቅራቢነት በፌደራል የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ይሾማሉ፡፡ የሚተዳደሩትም እንደሌሎች የመደበኛ ፍርድ ቤት ዳኞች ሁሉ ነው፡፡

ዳኛ ለመሆን ደግሞ በዋናነት መስፈርቱ የሸሪኣ ሕግ ዕውቀት መኖር ነው፡፡ ፍርድ ቤቶቹ በተሠጣቸው የዳኝነት ሥልጣን ላይ ውሳኔ ለመወሰን የሸሪኣ ሕግን ይጠቀማሉ፡፡ ስለሆነም፣ ለሕጉ ምንጭ የሆኑትን ቁርኣንን፣ ሀዲስን እንዲሁም ዑለማዎች የተስማሙባቸውን ውሳኔዎች (ኢጅማ)፣ ከሌሎች መርሆች ጋር ማመሳስልን (ቂያስ) እንደ ነገሩ ሁኔታ ጥልቅና ግላዊ ነገር ግን ምሁራዊ ምርምሮችን (ኢጂቲሃድን) ሊጠቀሙ ይችላሉ፡፡

Continue reading
  12343 Hits

አላግባብ/በስህተት የተከፈለን የጡረታ አበል ለማስመለስ የሚቀርብ ክስን የሚያስቀረዉ የይርጋ ዘመን ምን ያህል ነዉ?

መግቢያ

የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት በሰበር ችሎት ዉሳኔዎች ቅጽ 14 መግቢያ እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፤ “ለተመሣሣይ ጉዳዮች በጣም የተራራቁ ዉሣኔዎችን በመስጠት ይታይ የነበረዉን ችግር በመቅረፍና የዉሣኔዎችን ተገማችነት በማረጋገጥ ረገድ የሰበር ዉሣኔዎች አስገዳጅ መሆን ከፍተኛ ዉጤት አስገኝቷል ማለት ይቻላል፡፡ አልፎ አልፎ በዉሣኔዎች ጥራትና ስርጭት ሊታዩ የሚችሉ ችግሮች ሥርዓቱ እየተጠናከረ ሲሄድ የሚፈቱ ሲሆን አነዚህን ችግሮች ለማቃለል እኛም ጥረት በማድረግ ላይ እንገኛለን፡፡ ጥረታችን ሊሳካ የሚችለዉ በዉሣኔዎቹ ላይ በሕግ ምሁራንና ባለሙያዎች ገንቢ የሆኑ ትችቶችና አስተያየቶች ሲቀርቡ ነዉ”፡፡ እኔም ይህን ግብዣ በመቀበል የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ችሎት ሕዳር 21 ቀን 2005 ዓ.ም. በሰጠዉ ዉሳኔ ላይ ትችቴን ከዚህ በመቀጠል አቀርባለሁ፡፡ ዉሳኔዉ የተሰጠዉ በማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ እና ታዬ አበራ መካከል ባለዉ ክርክር በሰበር መዝገብ ቁጥር 72341 ነዉ፡፡ በዚህ መዝገብ ከተነሱት ዋነኛ ጉዳዮች ዉስጥ፤ አላግባብ የተከፈለ ጡረታን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በይርጋ ይታገዳል ወይ፤ ከታገደስ የይርጋ ዘመኑ ምን ያህል ነዉ የሚሉት ይገኙበታል፡፡

የጉዳዩ መነሻ

አቶ ታዬ አበራ ከግንቦት 01 ቀን 1984 ዓ.ም. ጀምሮ በየወሩ የጡረታ አበል ይወስዱ ነበር፡፡ ከሰኔ 01 ቀን 1989 ዓ.ም. ጀምሮ ደግሞ በመንግስት መስሪያ ቤት ተቀጥረዉ ደመዎዝ ተከፍሏቸዋል፡፡ አቶ ታዬ የጡረታ አበላቸዉን መዉሰዳቸዉንም እንደቀጠሉበት ነዉ፡፡ የመንግስት ሰራተኞች ጡረታ አዋጅ ቁጥር 209/1955 አንቀጽ 30(2) እና በመንግስት ሰራተኞች ጡረታ አዋጅ ቁጥር 345/1995 አንቀጽ 46(1) መሰረት፡ የአገልግሎት የጡረታ አበል በመቀበል ላይ ያለ ባለመብት እንደገና በመንግስት መሥሪያ ቤት ተቀጥሮ ደመዎዝ ማግኘት ከጀመረ አበሉ ይቋረጣል፡፡ በመሆኑም በማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ የተጠየቀዉ ዳኝነት እነዚህን ያጠቃልላል፡፡ 1) ከሰኔ 01 ቀን 1989 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ነሐሴ 30 ቀን 1995 ዓ.ም. ድረስ በየወሩ ብር 105.00 የወሰዱት ለሰባ አምስት ወራት ያህል ተባዝቶ የሚመጣዉን ዉጤት ብር 7575.00፤ 2) ከሐምሌ 01 ቀን 1996 ዓ.ም. እስከ ሀምሌ 01 ቀን 1998 ድረስ በየወሩ ብር 115.50 የወሰዱት ታስቦ የሚመጣዉን ድምር ብር 4045.50፤ 3) ወጪና ኪሳራ እንዲሁም ከሕጋዊ ወለዱ ጋር እንዲከፍሉ፡፡ የማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ ለመጀመሪያ ጊዜ ክስ የተመሰረተዉ በጥቅምት 18 ቀን 2003 ዓ.ም. ነዉ፡፡

የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዉሳኔ

Continue reading
  9209 Hits

የእንደራሴነት ሕግ (Agency Law) ዋና ዋና ነጥቦች

መግቢያ

 

ሰዎች ኑሮአቸውን ስኬታማ ለማድረግ በሚፈጽሙት የእለት ተእለት ተግባራቸው ከሌሎች የማህበረሰቡ ክፍሎች ጋር ዘርፈ ብዙ መስተጋብሮችን የሚፈጽሙ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ይሁንና እነኚህን መስተጋብሮች  በተለያዩ ምክኒያቶች በራሳቸው ለመፈጸም የማይችሉ በሆነ ጊዜ ሥራዎችን ሌላ ሰው እንዲያከናውንላቸው ፍላጎት ሊያድርባቸው እንደሚችል የሚያሻማ አይደለም፡፡

በዚሁ መሠረት ይህንኑ ሥራቸውን ማን፣ መቼ፣ በምን ሁኔታ እና በድካም ዋጋ ክፍያ ወይም ያለ ክፍያ  ሊሠራላቸው እንደሚገባ የመወሰን ነጻነት ሊኖራቸው የተገባ ነው፡፡  

ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ለማለት ባይቻልም አብዛኛው ስለ እንደራሴነት ወይም ውክልና ግንኙነት ጠቅለል ያለ መጠነኛ ግንዛቤ ይኑረው እንጂ በኢትዮጵያ ፍትሕ ሥርዓት ትግበራ መሣሪያ ከሆኑት ሕጎች አንዱ ስለሆነው የፍትሐብሔር ሕግ በልዩ ትኩረትም ስለ እንደራሴነት በቂ እና ጥልቅ ግንዛቤ ይኖረዋል ተብሎ ግምት አይወሰድም፡፡ በዚህም ምክንያት በሥራውም ሆነ በንብረቱ ላይ ሌሎችን ለመወከል የሚወስዳቸውን ጥንቃቄ  ለማወቅ፣ ያሉትን መብቶች እና ስለሚወክለው ሰውም ሆነ የተወከለው ሰው ከሦስተኛ ወገን ጋር ስለሚገባው ግዴታ ያሉበት ኃላፊነቶች ለይቶ ለማወቅ የሚቸገር በመሆኑ በጥቅሙ  እና በመብቱ ላይ ከፍ ያለ ጉዳት ሲደርስበት እንታዘባለን፡፡

Continue reading
  9722 Hits
Tags:

በጣልቃ ገብ እና የተያዘ ወይም የተከበረ ንብረት ይለቀቅኝ  አቤቱታ ላይ የዳኝነት ይከፈላል?

 

ለዚህ ጽሑፍ  መነሻ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 41 አንድ ሰው በተጀመረ ክርክር መብቴ ይነካል፤ ወደ ክርክሩ ጣልቃ ገብቼ ልከራከር ብሎ ሲጠይቅ እና በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 418 ለፍርድ ማስፈፀሚያ የተያዘ ወይም የተከበረ ንብረት ይለቀቅልኝ በማለት አቤቱታ ሲያቀርብ የዳኝነት ይከፈላል ወይስ አይከፈልም የሚለው ጉዳይ ነው፡፡

የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ መሠረት አድረገው የሚደረጉ ክርክሮች ቅድሚያ የዳኝነት ሊከፈልባቸው እንደሚገባ በቁጥር 215 ተቀምጧል፡፡ ለዚህ ጽሑፍ በማዕከልነት የቀረበው በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 41 መሠረት ጣልቃ ሲገባ እና በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 418 መሠረት ለአፈፃፀም የተያዘ ወይም የተከበረ ንብረት ይለቀቅልኝ በማለት አቤቱታ ሲቀርብ የዳኝነት ይከፈላል ወይስ አይከፈልም የሚለው ጉዳይ ነው፡፡ ጉዳዩን በተመለከተ በባለሙያዎች ሁለት ዓይነት አቋምና አሠራር ሲንፀባረቅ ይታያል፡፡ የሁለቱን  አቋምና አሠራር ከነምክንያታቸው መመልከቱ ልዩነቱን በማጥበብ ወደ አንድ የተቀራረበ አሠራር ሊያመጣ ስለሚችል ለያይቶ መመልከቱ ተመራጭ ነው፡፡

የመጀመሪያው አቋምና አሠራር በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 41 እና 418 መሠረት አቤታቸውን የሚያቀርቡ ወገኖች የዳኝነት ሊከፍሉ አይገባም የሚለው ነው፡፡ የአቋሙ አራማጆች መከራከሪያቸው በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 41 አንድ ሰው ቀድሞ በተጀመረው ክርክር መብቴ ወይም ጥቅሜ ይነካል በማለት አቤቱታውን የሚያቀርበው የቀደሙት ተከራካሪ ወገኖች የዳኝነት በከፈሉት ጉዳይ ላይ ነው፡፡ ጉዳዩ ዳኝነት የተከፈለበት ሆኖ እያለ በድጋሚ ጣልቃ የሚገባውን ሰው ዳኝነት ክፈል ማለት ያላግባብ ለአገልግሎቱ ሁለት ጊዜ ማስከፈል ነው፡፡ በተጨማሪም ጣልቃ የሚገባው ያለፍላጎቱ በተጀመረው ክርክር ጥቅሙና መብቱ ሊነካበት ስለሚችል በመገደድ ስለሆነ ተገዶ በገባበት ክርክር የዳኝነት ክፍል ማለቱ የሥነ ሥርዓት ሕጉ ዓላማ ባለመሆኑ የዳኝነት ሊከፍል አይገባም፡፡ አቤቱታውን ብቻ በማቅረብ ወደ ክርክሩ በመግባት መብትና ጠቅሙን ማስከበር አለበት በማለት ምክንያታቸውን ያስቀምጣሉ፡፡

በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 418 የሚቀርቡ አቤቱታዎች የዳኝነት ሊከፈልባቸው አይገባም በማለት መከራከሪያቸውን የሚያቀርቡት አቤቱታውን ተከትሎ ሊሰጥ የሚችለውን ውሳኔ ይዘት በመመልከት ነው፡፡ የሚጠየቀው ዳኝነት ለአፈፃፀም የተያዘ ወይም የተከበረ ንብረት ይለቀቅልኝ የሚል በመሆኑ የሚሰጠው ውሳኔ ሊለቀቅ ይገባል ወይም አይገባም የሚል እንጅ መብት የሚሰጥ ውሳኔ ባለመሆኑ ዳኝትነት መከፈል የለበትም፡፡ ፍርድ ቤቱ አቤቱታው ሲቀርብለት ለአፈፃፀም ምክንያት የሆነውን ውሳኔ በሚሽር መልኩ ውሳኔ መስጠት አይችልም፡፡ ውሳኔው ንብረቱ ለአፈፃፀም ይውላል ወይስ አይውልም፤ ሊለቀቅ ይገባል ወይስ አይገባም የሚለው ላይ ስለሆነ መብት በማይሰጥ ውሳኔ ላይ ዳኝነት ማስከፈሉ ተገቢ አይደለም በማለት ይከራከራሉ፡፡

Continue reading
  10713 Hits