ሕግ የማታከብረው ከተማ

 

 

በከተማችን ሰማይ ላይ የሰፈረ መንፈስ አለ የሆነ ህጻኑን ወጣቱን አዛውንቱን የሚፈታተን መንፈስ፡፡ በራዲዮ ቢራ፣ በቴሌቭዥን ቢራ፣ በቢልቦርዶች ገፅ ላይ ቢራ ሆኗል ከተማው፡፡ 
ዛሬ ዛሬ ቢሮ ከሚለው ስም ይልቅ ቢራ የሚለውን ስም መስማት የተለማመደ ሆኗል፡፡ እኔም በእለት ተእለት እንቅስቃሴም ውስጥ በሁለት ነገሮች እርግጠኛ ነኝ ከእሁድ በስተቀር ቢሮ እንደምገባና አንድ የቢራ ማስታወቂያ ጆሮየ እንደሚሰማ፡፡ ከወዳጅ ዘመዶቼ ይልቅ አዲሱ ዓመት መልካም እንዲሆንልኝ አብዝተው የተመኙልኝም የቢራ ማስታወቂያዎች ናቸው፡፡ ቢራ ስትጠጣ አዲሱ መት የሰላም የጤና የብልፅግና ይሆንልሀል ዓይነት ፉገራ እየፎገሩኝ፡፡ ይህን ያህል ቢራ የሕይወታችን ገፅታ ሆኗል፡፡ ስለቢራ ላለመስማት ብር ብሎ ከመጥፋት ውጭ አማራጭ የለም በመዝናናታችን መኃል፣ በመንገዶቻችን ዳርቻ፣ በስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎቻች ቢራ አለ፤ ቢራ መኖሩ አይደለም ችግሩ፣ ችግሩ ቢራ አብዝቶ መኖሩና እየተነገረበት ያለው መንገድ ነው፡፡ ቢራ የማኅበራዊ የሥነልቦናዊና ኢኮኖሚያዊ ሕይታችን ጋሬጣ ሊሆነ በሀገሪቱ ሰማይ ላይ አንዣቧል፡፡

ህፃናት አማራጭ በሌለው የቤት ውስጥ የቲቪ መዝናኛቸው ቢራ የደስታ የመልካም ጓደኝነት መሠረት መሆኑ ዘወትር እየተነገራቸው ነው፡፡ ሕፃናት ከቻሉ ተደብቀው ካልሆነ 18 ዓመት ሲሞላቸው የደስታ ምንጭ እንደሆነ አብዝቶ የተሰበከውን ቢራ ለመጠጣት ለማለም ተገደዋል፡፡ ህጻናት ከብራና እና ከቢሮ ይልቅ ቢራ ምን እንደሆነ በተሻለ ለማወቅ ተገደዋል፡፡ ወጣቶች በቢራ እንጂ በሌላ መንገድ መዝናናት የማይቻል እንኪመስል አብዝተው በቢራ ይዝናናሉ፡፡ አሽከርካሪዎች ቢራ ጠጥተው እልፎችን ከህይወት መስመር በማስወጣት ላይ ናቸው፡፡ በየቀኑ በመልካምነት፣ በእውቀት፣ በሥራ እና በእምነት ከሚጠቀመው ይልቅ በቢራ የሚጠመቁት በዝተዋል ሀገሪቱ በቢራ ጠመቃ ላይ ነች፡፡ ቢራ የሚጠምቁት፤ የሚያስጠምቁትና የሚያሳልፉት አሳላፊዎች ደግሞ በሀገሪቱ የአርዓያነት ምልክት ተብለው የሚወሰዱ ግለሰቦች እና ተቋማት ናቸው፡፡ 

የሀገሪቱ ሕግ ግልጽ ነው (የማስታወቂያ አዋጅ ቁጥር 759/2004) ህፃናት ባሉበት አካባቢ፤ በትምህርት ቤት፤ በህክምና ጣቢያዎች፤ በቲያትር ቤቶች እና በስታዲያሞች 100 ሜትር ራዲየስ ውስጥ የአልኮል መጠጥ ማስተዋወቅ ክልክል ነው፡፡  የጎልማሳ ደሰታው እንቢ ማለት ነው እንጂ መጽሐፍ ከተማይቱ በራሱ በርካታ ሕጎች ላይ እንቢ ባይ ሆናለች፡፡ የከተማይቱ ስታዲየሞች ግማሽ ክፍል የተሸፈነው በቢራ ማስታወቂያ ቢል ቦርዶች ነው፡፡ ለአንድ ዓመትም ቢሆን ለመሰባሰባችን ለአንድነታችን እና የሀገር ፍቅር መግለጫችን የነበረው እግር ኳሳችን ሳይቀር ስፖንሰር የተደረገው በአልኮል መጠጥ ነው ጭራሽ በቅርቡ በቢራ የተሰየመ አውሮፕላን ስፖርተኞችን ይዞ ሲሼልስ ገብቷል፡፡ ከሰው ልጅ ምንጭነታችን ይልቅ፤ ከነጭ አሸናፊ ጀግንነታችን ይበልጥ፤ የራሳችን ማንነት ያለን ኩሩ ሕዝብ ከመሆናችን ልቆ ቢራ ከፊታችን ቀድሟል፡፡ ጠጭነት ETHIOPIAN ከሚለው የኩራት ስም ልቆ የጥንካሬ ምንጭ የሆነውን ስፖርት ስፖንሰር አድርጎ ሲሼልስ ገብቷል፡፡ ስፖርት ባለበት ቢራ አለ ምናልባትም ቢራ መጠጣት ስፖርተኛ የሚያደርግ እስኪመስል ቢራና ስፖርት ተቆራኝተዋል፡፡ ታዋቂ የምንናላቸው አዋቂዎቻችንን ስለ ቢራ አብዝተው ይሰብኩናል፡፡ በቴሌቭዥናችን ውስጥ ከአምስቱ ማስታወቂያዎች አንዱ የቢራ ማስታወቂያ ነው፡፡ የሆነ ቴሌቭዥኑ የጠላ መጥመቂያ ጋን እስኪመስል ድረስ ቢራ ቢራ ይሸታል፡፡ የከተማው ረዣዥም ህንፃዎች ግማሽ አካል በቢራ ማስታወቂያ ፖስተሮች የተሸፈነ ነው፡፡ አይዶሉ፤ ቲያትሩ፤ ፊልሙ፤ ሙዚቃው ቢራ ቢራ ይላሉ የቢራ መንፈስ ሀገሪቱ ሞልቷታል፡፡ እንግዲህ ቢራን የአልኮል መጠጦች ወኪል አድራጌው እንጂ ቢራ ስል የአልኮል መጠጥ ማለቴ ነው፡፡ 

Continue reading
  9673 Hits
Tags:

አንዳንድ ምልከታዎች ስለ መገናኛ ብዙኃን እና የሐሰት ዘገባዎች

 

መግቢያ

ሀሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት እጅግ መሠረታዊ መብት ከመሆኑ የተነሳ የተለያዩ ሀገራት ሕጋዊ ጥበቃ የሚያደርጉለት ሲሆን በአለማችን ላይ በአንባገነንነታቸው የሚታወቁ መንግሥታት ሰይቀሩ መብቱ ሳይሸራረፍ በሀገራቸው እንደሚጠበቅ ይከራከራሉ። በዚህ ጽሑፍ ሀሳብን በነፃነት መግለጽ መብት በሰፊው ከሚተገበርበት ስለ መገናኛ ብዙኃን መብት እንመለከታለን። በመጀመሪያው ክፍል የመገናኛ ብዙኃን ለምን የሐሰት ዘገባዎችን ይሠራሉ በተለይም በመንግሥት ይዞታ የሚገኙ ወይም ዋነኛ የፋይናንስ ምንጫቸው በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ ከመንግሥት የሆነ የሚለውን እናያለን። በመቀጠል የመገናኛ ብዙኃን የሰሩት ፕሮግራም እውነታን ያዘለ ሆኖ ሳለ የእርምት ወይም መልስ የመስጠት መብት ያለው አካል ሐሰተኛ ማስተባበያ ይዞ ቢቀርብ የማስተላለፍ ግዴታ አለባቸው ወይስ የለባቸውም የሚለውን እንመለከታለን። በመጨረሻም ነፃ ሚዲያ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ከሀገራችን ሕጎች አንፃር አጭር ዳሰሳ እናካሔዳለን።

የመገናኛ ብዙኃን ለምን የሐሰት ዘገባዎችን ይሠራሉ

በተለያዩ ግዜያት ሚዲያዎች የሐሰት ዘገባ ሲሰሩ ይስተዋላሉ። ይህ ተግባር በተለይ የዴሞክራሲ ሥርዓት ባልዳበረባቸው ሀገራት በብዛት ይደጋገማል። ሀገራችንም በተለያዩ አለም አቀፍ ተቋማት በዚህ ረገድ ክስ ይቀርብባታል። ለሚዲያ ሐሰተኛ ዘገባዎች በዋናነት ነፃ አልመሆናቸው ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛል። ለዚህም ነው የመገናኛ ብዙኃን እና የመረጃ ነፃነትን ለመደንገግ የወጣው አዋጅ ቁጥር 590/2000 በመግቢያው ላይ የመገናኛ ብዙኃን የአሠራር ነፃነት ላይ መሰናክል የነበሩ መዋቅራዊ እና ተቋማዊ ችግሮችን ማስወገድ ሀሳብን በነፃነት ለመግለጽ እና የመገናኛ ብዙኃንን ነፃነት ለማዳበር መሠረት እንደሚሆን የሚያስቀምጠው። ይህ የሐሰት ዘገባ በግል ከተያዙ መገናኛ ብዙኃን ይልቅ በመንግሥት ይዞታ ሥር ባሉ ወይም ከመንግሥት የፋይናንስ ድጋፍ በሚደረግላቸው ሚዲያዎች ላይ በብዛት ይስተዋላል።  ይህን አስመልክቶ የናዚ የፕሮፖጋንዳ ሚኒስቴር የነበረው ጄሴፍ ጊበን ሲናገር ውሸትን በብዛት ማምረት ከቻልክ ይህንንም ማስቀጠል የምትችል ከሆነ ሕዝቡ በመጨረሻ ያምናል። ይህም ውሽት ሊቀጥል የሚችለው መንግሥት ውሽቱ በሕዝቡ ላይ ከሚያስከትለው ፖለቲካዊ፣ ኢኪኖሚያዊ እንዲሁም ወታደራዊ መዘዝ ሕዝቡን መከልከል ሲችል ነው። ሰለዚህ ለእንዲህ ዓይነት መንግሥት የሚበጀው የአለውን ሁሉ ኃይል አሟጦ የልይነትን ሀሳብን /dissenting ideas/ መደፍጠጥ ነው። ሰለሆነም እውነት የውሸት የባህሪ ጠላቱ ሰለሆነ በአምክንዮ እውነት የአንድ አገዛዝ ዋነኛ ጠላት ነው በማለት ሀሳቡን ያስቀምጣል።

Continue reading
  7070 Hits
Tags:

ኢትዮጵያ ውስጥ በሚሠሩ ፊልሞች ላይ የሚታዩ የሕግ ግንዛቤ ክፍተቶች

 

መግቢያ

ፊልሞችን ሰርቶ ለሕዝብ ማቅረብ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 29 ላይ የተቀመጠው ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት አንደኛው መገለጫ ነው፡፡  ሀሳብን የመግለፅ መብት ከመንግሥት ገደብ (Limitation) ሊጣልበት የሚችለውም ውስን በሆነ ምክንያት እንደሆነ ይሄ ሕግ መንግሥት የሚያስቀምጠው ጉዳይ ነው (አንቀጽ 29/6 መመልከት ይቻላል)፡፡ አዋጅ ቁጥር 533/2007 እና ከዛ በፊት የወጡ ሕጎችም ትልቅ ጥበቃ ሊደረግለት የሚገባውን ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ሊገደብ የሚችልበትን አግባብ ያስቀምጣሉ፡፡ ሀሳብን የመግለፅ መብት በሕግ የሚገደበውም ሦስት መሠረታዊ ፍላጎቶችን (Interests) ለመጠበቅ ሲባል ብቻ ነው፡፡ እነዚህም፡-

1.     የሰዎችን ክብርና መልካም ስም፣

2.    የሕዝብን ሞራልና የወጣቶችን ደህንነት እና

Continue reading
  9486 Hits
Tags:

የማይደፈረውን ፍርድ ቤት መድፈር

 

 

በአንጌሳ ኢቲቻ የተጻፈውን ‹‹ችሎት መድፈር፡- ሕጉና የአሠራር ግድፈቶች›› የሚለውን ሳነብ እ.አ.አ በታኅሣስ 2013 በተመሳሳይ ርዕስ የጻፍኩትን ለአንባብያን ለማካፈል ወደድኩ፡፡ በዚህ ጽሑፌ ፍርድ ቤት መድፈር ምን ማለት ነው? የኢትዮጵያ ሕግ ስለ ፍርድ ቤት መድፈር ምን ይላል? የሕጉ ዓለማስ ምንድነው፣ የወንጀሉ አወሳሰን ልዩ ባህርይስ እንዴት ይታያል፣ በአፈጻጸም የሚታዩ ችግሮች ምንድናቸው የመሚለውን እዳስሳለሁ፡፡

በወቅቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ይዞት የወጣው ከፍርድ ቤት ጋር የተያያዙ ሁለት ዜናዎች አንባቢውን በተለይም የሕግ ባለሙያዎችን የሚያስገርም ነበር፡፡ የመጀመሪያው ዜና አንድ የፖሊስ አባል የፌዴራል ፍርድ ቤት ዳኛን በማመናጨቅና ፍርድ ቤት በመድፈር ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው መታሠራቸውና ሌሎቹ ፖሊሶች ጉዳይ በቀጠሮ ላይ መሆኑ ነው፡፡ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሁለተኛ ፍትሐብሔር የቤተሰብ ችሎት ውስጥ የተፈጸመው ይህ ወንጀል ለየት የሚያደርገው ሕግን ለማስከበር አስፈጻሚውን በሚወክለው በፖሊስ መፈጸሙ ብቻ አይደለም፡፡ ፖሊሶቹ ያሳዩት ባህርይና ኃላፊዎቹ የሰጡት መልስ የበለጠ አስገራሚ ነበር፡፡ ፖሊሶቹ በጊዜው የዳኝነት ሥራ ስታከናውን የነበረችይቱን ዳኛ ‹‹አንመጣም›› ‹‹አንቀርብም›› ‹‹ስቀርብ ትፈትሽኛለሽ›› ‹‹ነገርኩሽ እኮ›› ወዘተ. በማለት ፍርድ ቤቱን ዝቅ የሚያደርግ፣ በኅብረተሰቡ ውስጥ ያለውን መተማመን የሚያሳጣና ሌሎች ዳኞችን የሚያሳቅቅ ነው፡፡ የፍርድ ቤት መድፈር በአብዛኛው በተከራካሪ ወገኖች፣ በቤተ ዘመዶቻቸው፣ በጋዜጠኞች ወዘተ. ተፈጸመ ተብሎ መስማት የተለመደ ነው፡፡ ችሎቱን ለማስከበር በተሰማሩት የፖሊስ አባላት መፈጸሙ ግን የበለጠ ግርምት ይፈጥራል፡፡ በጊዜው የፖሊስ ኃላፊው ‹‹ልጆቹ ጥፋት ያጠፉት ልጆች ስለሆኑ ነውና ይቅርታ ይደረግላቸው›› የሚለው ደግሞ፣ የፖሊስ ተቋሙ በፍትሕ አደባባይ፣ የሚበሳጭና የሚናደድ ተከራካሪ በሚኖርበት፣ ኅብረተሰቡ በብዛት አንዱን ነቅፎ ለሌላው ወግኖ በሚቆምበት ቦታ የሚመድባቸውን ፖሊሶች የትምህርትና የልምድ ሁኔታ ጥያቄ ውስጥ የማያስገባ ነው፡፡ ሁለተኛው ዜና የከፍተኛው ፍርድ ቤት ትዕዛዝ በአዲስ ክፍለ ከተማ መሬት ልማት ማኔጅመንት የመጣሱ ዜና ነው፡፡ በፍርድ ቤት በተያዘ አንድ ጉዳይ ፍርድ ቤቱ እንዳይፈርስ የእግድ ትዕዛዝ የሰጠበትን የንግድ ቤት የእግድ ትዕዛዙ ደርሶት ክፍለ ከተማው ቤቱን የማፍረሱ ዜና እጅጉን አስደንጋጭ ነው፡፡

እነዚህ ሁለት ዜናዎች በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ የተጋረጡትን ፈተናዎች አመላካች ናቸው፡፡ ፍርድ ቤቶች ከሦስቱ የመንግሥት አካላት አንዱ እንደመሆናቸው ሕገ መንግሥታዊ ጥበቃና ኃላፊነት ተሰጥቷአቸዋል፡፡ ፍርድ ቤቶች አስፈጻሚውን የመቆጣጠር ሕገ መንግሥታዊ ግዴታ ያለባቸው ሲሆን አስፈጻሚውን ለመቆጣጠር ባልቻሉ መጠን ህልውናቸው ላይ አደጋ ይፈጥራል፡፡ በሁለቱ ዜናዎች ፍርድ ቤቱ የተደፈረው በአስፈጻሚው አካል እንደመሆኑ መጠን የፍትሕ ተቋሙ ተመሳሳይ ጥሰቶች እንዳይኖሩ ተግቶ ሊሥራ እንደሚገባው አመላካች ነው፡፡ በአስፈጻሚው አካል ክብር ያልተሰጠው ፍርድ ቤት በተራ ዜጋው ክብር ይሰጠዋል ማለት አስቸጋሪ ነው፡፡ ተመሳሳይ ድርጊቶች በፍርድ ቤቶች ወይም በዳኞች ላይ የሚፈጸሙ ከሆነ ፍርድ ቤቶች በኅብረተሰቡ ውስጥ ያላቸውን ክብርና መተማመን ማጣታቸው አይቀርም፡፡ የራሱን መብት የማያስከብር ፍርድ ቤት የሌላውን ዜጋ መብት እንዲያስከብር መጠበቅ ሞኝነት መሆኑ ነጋሪ አይፈልግም፡፡

Continue reading
  9488 Hits

ዳኛ  እግዜር! ዳኛ ከችሎት ይነሳ!

 

 

ሀገሬው የዳኝነትን ሥራ (ፍትሕ መስጠት) ሃሳባዊ በማድረግ ደረጃውን ከፍ ሲያደርገውዳኛ እግዜር!” ይላል፡፡ ከሳቴ ብርሃን የአማርኛ መዝገበ ቃላትም ዳኛ ማሪያም! ተሙዋጋች በዳኛ ፊት ቆሞ ሲአመለክት ዳኛ እግዚአብሔር! ያሳይህ ዳኛ ማርያም ወይም ሲሙአገት ጭብጥ የያዘውን አስመስካሪውን ዳኛ የምስክሮቹን ቃል ለማሳሰብ ተዘከረኝ ዳኛ ማሪያም ይላል በማለት ይገልፀዋል፡፡ እንደ ፕልቶ ያሉ ሃሳባውያን (idealist) ፈላስፎችፍትሕሃሳባዊ ተፈጥሮ ያለው፣ ከሰብዓዊ ባህርይ ውጪ የሆነ እና አሁን ባለው ዓለም (physical world) ሳይሆን በጊዜ እና በቦታ ባልተገደበው ሃሳባዊ ዓለም የሚገኝ እንደመሆኑ ስሙ ብቻ የሚታየውን ሃሳብ ቅርፅ ወዳለው ድርጊት በሕግ መልክ ሆነ በሌላ ዘዴ ወደ ዚህኛው ዓለም ሊመልሱት እና ሊፈፅሙት የሚችሉት እውነተኛው ሃሳብ የሚታያቸው ሰዎች ናቸው ይላል፡፡ እንግዲህ ሀገሬውዳኛ እግዜርሲል በፍትሕ ላይ ሃሳባዊ መሆኑ ነው፡፡ፍትሕ ከፈጣሪ  ነውብሎ ለሚያምን ማህበረሰብ ሰው በፈራጅነት ቦታ ቁጭ ብሎ ሲያገኘው  በአገረኛ ዘዬ ኧረ! ዳኛ እግዜር! ቢል አይገርምም፡፡ ሌላው ሀገሬው በፍትሕ ላይ ሃሳባዊ ለመሆኑ መገለጫ የሚሆነው ለዳኛ ሲሰጠው የነበረው ልዩ ቦታ ነው፡፡ የአንድ ማህበረሰብ ወግ እና ሥርዓት የሚቀዳው ካለው አካባቢያዊ የእምነት እና አስተሳሰብ መሠረት አድርጎ ነው፡፡ ለማሳያ ያህል  ከፍትሐ ነገስቱ አንድ ነገር አንጠልጥለን እንውጣ፡፡

ፍትሐ ነገስቱ አንቀጽ 43 ዳኛ የፍርድን ልዩነት የሚያውቅ፣ አዕምሮው ያማረለት፣ ከድንቁርና የራቀ በአዕምሮውም መራቀቅ የጭንቅና የተሰወረውን ወደ ፍርድ ፍፃሜ መግለፅ የሚደርስ ይሁን፤ ነፃነት ያለው ይሁን፤ ራሱን ለማስተዳደር ሥልጣን ያለው ያልሆነ ሰው ሌሎችን ሊያስተዳድር አይቻለውምና፤ ዳኞች በፍርድ ጊዜ የማያደሉ ፊት አይተው መማለጃ (ጉቦ) የማይቀበሉ ይሁኑ፤ መማለጃ (ጉቦ) እውነትን እንዳያዩ የብልሆችን ዓይን ያሳውራልና፤ የቀናውንም ፍርድ ይለውጣልና በማለት ይገልፀዋል፡፡  

ፍትሐ ነገስቱ ከአፄ ዘርዐያቆብ ንግስና ዘመን 1444 . ጀምሮ የኢትዮጵያ ሁለተኛው ሕገ መንግሥት ተረቆ በአዋጅ ሥራ ላይ እስከዋለበት 1948 . ድረስ  ለብዙ ዘመናት በሥራ ላይ የዋለ እንደመሆኑ ማህበረሰባዊ ቅቡልነቱ አጠያያቂ አይደለም፡፡ ህዝቡ ለዳኛ የሚሰጠው ስብዕናም ከፍትሐ ነገስቱ የተቀዳ እና ከትውልድ ትውልድ በቅብብሎሽ መልኩ የመጣ ነው፡፡ በአብዛኛው የማህበረሰብ ክፍል ለዳኛ ስብዕና  ያለው ግልፅ መረዳት (pereception) የሚመነጨው ፍትሕን ወደ ተግባር ሊያወርዱት የሚችሉት የተለየ ሥነ-ምግባር እና ያማረ ረቂቅ የሆነ አእምሮ ያለቸው ስዎች መሆን አለባቸው ከሚለው እሳቤ ነው፡፡ ሀገሬው ዳኞች ከመረመሩ ይናገራል ምድሩ፤ ይገኛል ነገሩ በማለት ያዳንቅ የነበር እና ዳኛው የረገጠውን ዲካ (ዱካ) እኔም ረገጥኩት በማለት ሀሴት ያደርግ የነበረው ለዳኝነት ሙያ  በነበረው ልዩ ምልከታ  እንጅ ዳኛ የተለዬ ፍጡር ስለነበር አልነበረም፡፡

Continue reading
  10588 Hits

ስለ ይርጋ ጥቂት ነጥቦች

 

 

ይርጋ ምንድን ነው? ይርጋ ዓላማው (ጠቀሜታው) ምንድን ነው? ይርጋ ጉዳቱስ ምንድን ነው? ይርጋ የሚያስጠብቀው የማንን መብት ነው? የይርጋ መሠረታዊ መርሆዎች ምንድን ናቸው? ይርጋን የሚመለከቱ የሕግ ድንጋጌዎች ምን ይመስላሉ? በይርጋ የማይታገዱ ጉዳዮች ምንድን ናቸው? የሚሉና ሌሎች ተያያዥ ነጥቦች በዚህ ጽሑፍ ይዳሰሳሉ፡፡  

የይርጋ ምንነት

ይርጋ የሚለው ቃል መነሻውረጋከሚለው የአማርኛ ቃል ጋር የተያያዘ ሲሆንረጋየሚለውን ቃል ደራሲ ተሠማ ኃብተ ሚካኤልከሠቴ ብርሀን ተሰማበተሰኘውና 2002 .. በድጋሚ ባሳተሙት የአማርኛ መዝገበ ቃላት ላይየሰው ሀሳቡ ከመውጣት ከመውረድ በሀሳብ ከመዞር ከመባከን ከመናወጥ ጠጥ (ፀጥ) አለበሚል ትርጓሜ ተሠጥቶታል፡፡ ከዚህ በመነሳትም ይርጋ የሚለውን ቃል በአንድ ጉዳይ ላይ ክስ የማቅረብ ወይም መብት የመጠየቅ ጉዳይን አስመልክቶ በጉዳዩ ላይ ክስ የሚያቀርብበት ሰው ስለጉዳዩ ያለውን ሀሳብ ከመውጣት ከመውረድ በሀሳብ ከመዞርና ከመባከን ከመናወጥ ከረጋ (ፀጥ) ካለ በኋላ ሊከሰስ ወይም ሊጠየቅ እንደማይገባ ያመለክታል በሚል ልንወስደው እንችላለን፡፡ በሌሎች ፅሁፎች ላይም ይርጋ ማለት አንድ መብቱ ወይም ጥቅሙ የተነካበት ሰው በሌላ ሰው ላይ ክስ፣ አቤቱታ ወይም የይገባኛል ጥያቄ እንዲያቀርብ በሕግ ተለይቶ የተቀመጠ የክስ (አቤቱታ) ማቅረቢያ ጊዜ ነው፡፡ በሕግ የተቀመጠው የክስ ማቅረቢያ ጊዜ ካለፈ በኋላም በዚያው ጉዳይ ላይ በጣም በውስንና ጥቂት ምክንያቶች ካልሆነ በስተቀር ክስ የማቅረብ መብት ቀሪ ይሆናል፡፡

Continue reading
  35609 Hits

If the doctrine of precedent did not exist, it would have to be invented

A law that that has been in force since 2005 (Federal Courts Proclamation 454/2005) declares that interpretations of law, rendered by the Cassation Division of the Federal Supreme Court (hereinafter referred to as CDFSC), are binding on all federal and state courts. However, according to the same law, this does not prevent the CDFSC from providing a different interpretation in the future.

The binding nature of precedents is a fascinating topic. After learning that this was raised in one of the electoral debates in 2010, I have decided to put my thoughts in writing. Several questions should be addressed if one is to have a clear position on the matter.

Should interpretations of law provided by higher courts be binding on lower courts? If so, should lower courts be obliged to follow only interpretations of the CDFSC or should they also follow the interpretation of law given by the ordinary appellate divisions of the federal supreme and high courts? If at all it is desirable that courts follow interpretations of law provided by higher courts, how do you make sure that that is so--is it by passing a proclamation which declares precedents to be legally binding? Is it desirable that the CDFSC is not bound by its previous interpretation?

There is one characterization of law which has already become a cliché: that in law two plus two is not necessarily four. To a large extent it is a characteristic which is unfortunate, particularly in the area of commerce. To a limited extent, however, the ambiguity, uncertainty which this characterization is meant to portray is desirable and unavoidable. To the extent that it is undesirable, therefore, attempts should be made to ensure that legal consequences of alternate courses of actions are predictable; that the sum of two and two is predictable whether it is 4 or 999.9. The question is: how do you ensure that the sum of two and two is the same whether it is Mekelle or Hawassa. Obviously having the same text of law is not the solution.

That is where the system of appellate review and the hierarchical structure of courts play important roles. One self-evident purpose of appeal is to correct errors made by lower courts. If that was the sole objective of the system we would have many federal supreme courts.

Continue reading
  11933 Hits
Tags:

Some Reflections on the Classification of Goods under the Ethiopian Civil code

In different legal systems of the world, properties are classified into different categories such as personal and real, private and public, movable and immovable, absolute and qualified, corporeal and incorporeal, etc. The distinction between these types of property is significant for a variety of reasons. Firstly, classification ensures the proper application of the law. This is because the legal regime that governs goods depends on their nature and accordingly their legal treatment substantially varies. For instance, one's rights on movables are more attenuated than one's rights on immovable (or real property). The statutes of limitations or prescriptive periods are usually shorter for movable than immovable property. Besides, real property rights are usually enforceable for a much longer period of time and, in most jurisdictions, real estate and immovable are registered in government-sanctioned land registers. More essentially, the manner for transfer of the possession or ownership of things depends on their nature. For example, the possession of ordinary corporeal chattels (movable things) may be transferred upon delivery. On the contrary, possession of immovable things requires more additional formalities like registration. In short, classification of property has a paramount importance in facilitating legal regulation of property rights and economic transactions.


When we come to the Ethiopian legal system, the classification of things is not that much clear. The law simply employs the term “good” which is primarily meant to refer the subject matter of property rights in most civil law countries as a bench mark to classify properties. Accordingly, under 1126 of the civil code it is provided that all goods are either movable or immovable. As Ethiopia is largely a civil law country, the use of the terms movable and immovable like other continental systems seems appropriate. Hence, the law recognizes goods as movable or immovable. The term “all” in this provision seems to signify that any thing to be regarded as good or any thing which is regarded as good must have either movable or immovable nature. In other words, a thing to be considered as subject matter of property right, i.e. good, in our legal system, it must fall in either of the class of immovable or movable things as defined by the law itself. However, as it is clearly provided in the Amharic version of the same provision, those goods which may be immovable or movable shall have material existence. The otherwise understanding suggests that at least in principle things to be considered as subject matter of property they must be tangible (corporeal); that can be perceived in our senses particularly that can be touched. Therefore, in the first glance the law seems to exclude incorporeal (intangible) things from the realm of property. Nevertheless, it puts exceptional instances in the subsequent articles where incorporeal things become goods after being assimilated with corporeal chattels (movable goods). In short, even if the law by definition excludes incorporeal things from the scope of property, it has also devised a mechanism where they may be regarded as goods, that is, by assimilating them with movable chattels.


Once the law classified goods as movable or immovable it also suggested what the terms should connote. Thus, under art.1127 it stipulates that corporeal chattels are things which have a material existence and can move themselves or be moved by man with out losing their individual character. Therefore, goods to be corporeal (tangible) movable thing, they must, first, be able to move by themselves or by the force of human beings. Second, when they are moving by themselves or are moved by human power they must not loss their natural (individual) feature, that is, their displacement or movement shall not result in the destruction of the whole or part of them or change of their physical feature. For instance, a marble which is already used for building may be movable, i.e. may be detachable from the building by using force. However, since in most cases, this result in some sort of destruction up on it, the marble may not be included in corporeal chattels. One top of this the law doesn’t seem clear when it says   “…with out losing their individual character”. What is the extent of losing individual character? Is any insignificant change capable of changing the nature of the thing? In our example above, what if the marble in the process of technical detachment slight crack occurred, will it be movable or remains an immovable? In the opinion of the writer, the intention of the legislator doesn’t seem to include slight changes but only those changes that outwardly affected the individual character, meaning, in our instance, any crack shall change the nature of normal marble may be that turns it to particles. In other words, as long as the change is not substantial, the nature of the thing shall not be changed.


On the other hand, article 1130 tries to describe immovables saying that ‘lands and buildings shall be deemed to be immovables’. Thus, unlike other legal systems, our civil code instead of defining immovables in general terms, it gives which things shall be regarded as immovables and it provided land and building as things that are deemed immovable. However, what about other things such as bridges and dams which are by nature immovable in the ordinary meaning of the term? Is the listing exhaustive or illustrative? In this regard two arguments may be raised; firstly, since the law doesn’t clearly say that ‘only’ land and buildings shall be deemed immovables, other things which are immovable by nature [in the literal meaning of the term] shall also be regarded as immovable in law. By contrast, it may be argued that the listing is exhaustive and no other thing shall be deemed immovable except land and buildings. To supplement the second argument, it may be said that in as long as the law doesn’t put the extent of ‘building’ (what things are referred as building?), we shall interpret it broadly  so as to include dams, bridges, fences  and the like in addition to houses. The general jurisprudence is just making land and any permanent establishment on land which can’t be moved from one location to another with out causing destruction upon it as immovable. In line with this, in whatever way the law is interpreted, it must include things such as fences, dams, bridges and the like as immovable goods so far as they are physically attached with the land and in a manner where it is impossible to displace them with out affecting their individual character.


Another point that the reader must also note is that when the law is referring to immovables it is only corporeals which have material existence by virtue of Art. 1126. As to incorporeal immovables like servitude, and others which are inseparable from the corporeal immovable such as land from which they develop as a right, though the law recognizes them under various provisions like art.1359 ff, it excluded them under article 1130 while describing what things are deemed immovable. Therefore, it doesn’t mean that these incorporeal immovables aren’t immovables because art 1130 is simply the follow up of art 1126 which sticks in classifying goods which have material existence (corporeals) only by excluding those which don’t have physical existence.

Continue reading
  14186 Hits
Tags:

The Invisible Hand - Why Ethiopia Needs Anti-Unfair Competition

The Wednesday’s news report, on Reporter News Paper Amharic version, about insurance companies restricting the commission paid to insurance agents is a dreadful, despicable thing. It shows what happens once a government fails to effectively and successfully to restrain firms.

I deliberately make this short essay provocative. I want the concerned parties to sit down and devise a long term plan to regulate unfair competition. Silence from all governmental bodies has a dire consequence in the future; everybody must be wary of its outcome: paralyzing the economy, huge amount of public and private corruption, suffocating entrepreneurs and new entrants, and creates unaccountable, strange and ill-transparent but powerful corporations.

Everything will be made behind the curtain and under the table. Invisible hands, to use the terms of Adam Smith, will pop out from every angle. Then, what is left for you and me? Nothing! We will be an escape goat to greedy people. The ambition to create a multi-cultural, consumer, middle income society will be like chasing a flying bird or following a wind.    

My readers should not be carried away by my sentiments. They must give me a chance to explain. However, I am always open for rebuttal. Firstly, competition law aims to eradicate abuse of dominant position, get rid of collusion/cartels, eliminates concentration of undertaking/mergers (modern competition laws intend to remove state aid and administrative monopolies.)

Fundamentally, competition law proposes fair society. Competition laws watches over economic efficiency and consumer welfare. For example, Article 1 of Chinese Anti-Monopoly law states:

Continue reading
  7840 Hits
Tags:

ሳንሱር እና ሕግ፡ ከትናንት እስከዛሬ

የሰው ልጅ ሐሳቡን ለሌላው መግለጽ መጀመሩ ሰዎች የጋራ ባሕርያትን ይዘው ወደ አዲስ ስልጣኔ፤ ወደ አዲስ ሕይወት እንዲወጣ አድርጎታል፡፡ ነገር ግን የዚህ ትስስር ድንበር የለሽ መሆን ጉዳት አለው በማለት፤ በተለያዩ ወቅቶች በተለያዩ ምክንያቶች መረጃን የመለዋወጡ ሂደት ገደብ እንዲኖረው ይደረጋል፡፡ ገደብ እንዲደረግ የሚያስገድዱት ዋነኛ ምክንያቶች ሦስቱን ዋነኛ ተቋማት መጠበቅ በሚል ሐሳብ ስር ይጠቃለል፡፡ 


እነዚህም ተቋማት ቤተሰብ፣ ቤተ እምነት እና ቤተ መንግሥት ናቸው፡፡ ቤተሰብን መጠበቅ ስንል ቤተሰብ የኅብረተሰብ መሠረት በመሆኑ ቤተሰብን እና ስርዓቱን የሚጎዱ ነገሮች (Obscene) በአደባባይ እንዳይኖሩ ማድረግ ማለታችን ነው፡፡ ቤተ እምነትን የሚያጎድፉ ነገሮችም (Blasphemous) እንዲሁ:: እንዲሁም በሦስተኝነት በሕግ የተዘረጋውን ስርዓት ለመጠበቅ ሲባል ሲሆን  ይሄም የግደባ ሂደት ሳንሱር (Censorship) ይባላል፡፡

 

የሕግ ማዕቀፉ እና ልምዱ ምን ይላል?

 

Continue reading
  7041 Hits
Tags: