“ለእግረኛ ቅድሚያ በመከልከል…” ከሕግ አንጻር ሲታይ


በሀገራችን እጅግ አሳሳቢ እና አነጋጋሪ ከሆኑት የወንጀል ድርጊቶች መካከል በአሽከርካሪዎች የሚፈጸመው ወንጀል ቀዳሚውን ሥፍራ ይይዛል ለማለት ይቻላል፡፡ ከትራፊክ ፖሊስ ዕለታዊ ሪፖርት በየዕለቱ እንደምንሰማው በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ እንኳን ያለበትን ሁኔታ ብንመለከት በንብረትና በሰው ላይ፣ ቢያንስ በአንደኛው ላይ አደጋ ሳይደርስ የዋለበት ቀን የለም ለማለት ይቻላል፡፡ የአደጋ ዜናው በ24 ሰዓት፣ በወርና በዓመት ስሌት ሲነገር ስንሰማው እጅግ አሳሳቢ ነገር ነው፡፡ በትርፊክ ፖሊስ የዘወትር ሪፖርት እንደምንሰማውም ብዙውን ጊዜ አደጋው የደረሰው ለእግረኛ ቅድሚያ መከልከል በአሽከርካሪ ጥፋት መሆኑን መዘገቡ የተለመደ ነው፡፡


በዚህ ጽሁፍ ፍተሻ የምናደርግባቸው ነጥቦች አሽከርካሪ አጥፍቷል ወይም በቸልተኝነት ወንጀል ፈጽሟል የሚባለው መቼ ነው; የወንጀል ድርጊቱን ለመከላከል/ለመቀነስ እግረኞችስ ምን ዓይነት ግዴታ አለባቸው; አደጋውን እያባባሱ ያሉት ዋና ዋና ሁኔታዎች ምንድን ናቸው; የሕግ ስርዓታችንና በፍርድ ቤቶች የተሰጠው ቦታስ ምን ይመስላል; የሚሉትንና ተያያዥነት ያላቸውን ነጥቦች ናቸው፡፡


ወደ ዝርዝር ነጥቦች ከመግባታችን በፊት ጭብጡን በፍርድ ቤቶች በታዩና ፍርድ በተሰጠባቸው ጉዳዮች ለመደገፍ ይቻል ዘንድ በቅድሚያ ሶስት ዐቃቤ ህግ የወንጀል ክስ ያቀረበባቸውንና ፍርድ ቤት ፍርድ የሠጠባቸውን ናሙና ጉዳዮችን በአጭሩ እንመልከት፡፡


ጉዳይ አንድ፡ ጊዜው ነሐሴ ወር 2002 ዓ.ም ነው፡፡ በ70ዎቹ የዕድሜ ክልል የሚገኙት አዛውንት ከኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ለሥራ ጉዳይ በማለት ወደ አዲስ አበባ ይመጣሉ፡፡ አዛውንቱ ሥራ ያሉትም በመንገድ ላይ ገንዘብ ለምኖና አጠራቅሞ ወደመጡበት መመለስ ነበር፡፡ ሥራቸውንም በተክለሃይማኖት አካባቢ ባለው አስፋልት ላይ ቀኑን እንደ ሸማኔ መወርወሪያ ከግራ ወደቀኝ በመመላለስ በትጋት ሲያከናውኑ መዋል ጀመሩ፡፡ የልመና ገንዘቡም በዋናነት ከአሽከርካሪዎች እየተሰበሰበና እየተጠራቀመ ነው፡፡ ይሁንና በአንዲቷ ጎደሎ ቀን ከአንዱ አሽከርካሪ ሳንቲም ተቀብለው በሌላኛው ተሽከርካሪ ተከልለው መንገዱን ከቀኝ ወደ ግራ ሲያቋርጡ ከአንድ የጭነት ተሽከርካሪ አይሱዙ ጋር ይጋጩና ከአስፋልቱ ላይ ይወድቃሉ፡፡ አዛውንቱም የሰበሰቡትን ገንዘብ የት እንዳስቀመጡት ሳይናገሩና እንዳሰቡትም ወደ መጡበት ሳይመለሱ እንደወጡ ቀሩ፡፡ የትራፊክ ፖሊስ የአዛውንቱ ሞት በአሽከርካሪ ጥፋት ለእግረኛ ቅድሚያ መከልከል የተፈጸመ መሆኑን በመግለጽ ፕላኑን አዘጋጅቶና ሪፖርቱን ጽፎ ጉዳዩን ለዐቃቤ ህግ አስተላለፈ፡፡ ዐቃቤ ህግም በሪፖርቱ መሠረት ክሱን በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀጽ 543/2/ ተላልፎ በቸልተኝነት ሰው መግደል የወንጀል ክስ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቀረበ፡፡


ጉዳይ ሁለት፡ ጊዜው በስድስተኛው ወር በ2002 ሲሆን አሽከርካሪዋ ሴት ነች፡፡ አሽከርካሪዋ ባለቤቷ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለይ የነበራቸውን ጅምር ቤት በመሸጥ ሁለት ህጻናት ልጆቿን ለማሳደጊያ ይሆናት ዘንድ በማሰብ አንድ ትንሽ ላዳ ታክሴ በመግዛት ሹፌር ቀጥራ ገቢ ማግኘት ጀመረች፡፡ ሴትዮዋ ያላት የመንጃ ፈቃድ 2ኛ ሆኖባት እንጅ 3ኛ ቢሆን ኖሮ ታክሲዋን ራሷ በማሽከርከር ገቢዋን የተሻለ የማድረግ ሀሳቡ ነበራት፡፡ ሀሳቧን ከግብ ለማድረስም 3ኛ ደረጃ አሽከርካሪነት የሙያ ፈቃድ ለማግኘት ልምምድ ጀመረች፡፡ ነገር ግን ልምምዱ በተፈቀደላቸው አሰልጣኞችና የመለማመጃ ተሸከርካሪዎች ብቻ የተወሰነ አልነበረም፡፡ ከዚህ አልፎ በራሷ ታክሲ እና በሹፌሯ አለማማጅነት ልምምዷን በኮተቤ አስፋልት ቀጠለች፡፡ ይሁንና እንኳን በ3ኛ ደረጃ መንጃ ፈቃድ የሚነዳውን ተሸከርካሪ ማሽከርከር ይቅርና ችሎታዋ በ2ኛ ደረጃ ለሚሽከረከረውም አጥጋቢ አልነበረምና ከኋላ በተከተላትና ድምጹን በሰማቸው ከባድ ተሸከርካሪ ምክንያት በድንጋጤ ከመንገዱ በመውጣት በከባድ ቸልተኝነት የመንገዳቸውን ቀኝ ጠርዝ ይዘው ይጓዙ ከነበሩት ሴት ህጻናት ተማሪዎች መካከል በአንዷ ላይ የሞት አደጋ፣ በሁለቱ ላይ የአካል ጉዳት አደጋ በማድረስ ግቢ ጥሳ በመግባት በንብረትም ላይ ጉዳት የማድረስ ድረጊት ይፈጸማል፡፡ የትርፊክ ፖሊስም አደጋው የደረሰው ከመንጃ ፈቃድ ደረጃ ውጭ ደንብ በመተላለፍ፣ በአሽከርካሪ ጥፋት ለእግረኛ ቅድሚያ መከልከል የተፈጸመ መሆኑን በመግለጽ ፕላኑን አዘጋጅቶና ሪፖርቱን ጽፎ፣ አለማማጁንም ከምስክሮች መካከል አድርጎ (እያለማመደ የነበረ መሆኑን ክዷል) ጉዳዩን ለዐቃቤ ህግ አስተላለፈ፡፡ ዐቃቤ ህግም በሪፖርቱ መሠረት ክሱን በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀጽ 543/2/ እና 559/2/ ተላልፎ በቸልተኝነት ሰው መግደል እና የአካል ጉዳት ማድረስ እንዲሁም በመንጃ ፈቃዱ ደንብ በመተላለፍ ሦስት የወንጀል ክሶችን በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቀረበ፡፡ 

Continue reading
  10223 Hits

አንዳንድ ነጥቦች ስለአዲሱ የመንገድ ትራፊክ መቆጣጠሪያ ማሻሻያ ደንብ ቁጥር 395/2009

 

በየካቲት ወር 2008 ዓ/ም መዲናችን አዲስ አበባ ላይ የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 208/2003 ዓ/ም የሪከርድ አያያዝ ትግበራ መጀመሩን ተከትሎ የታክሲ የአሽከርካሪዎች ስራ የማቆም አድማ ነበረ፡፡ በዚህም መሰረት ተግባራዊ መደረግ ተጀምሮ የነበረው የሪከርድ አያያዝ ተግባራዊነቱ እንዲቋረጥ ተደርጎ ከአሽከርካሪዎች እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ከተደረገ በኋላ የደንቡ መሻሻል አስፈላጊነት ታምኖበት ደንቡ እንዲሻሻል ተደርጓል፡፡ በወቅቱ በአሽከርካሪዎች በኩል ሀገሪቱ ባላት የትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ብቃት ደረጃ፣ የመንገድ መሰረተ ልማት ችግሮች፣ ልል የሆነ የትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ተጠያቂነት፣ የተቆጣጣሪዎች ስነምግባር ችግር እንዲሁም ከብዙ ተያያዥ ጉዳዮች ጋር በተገናኘ በደንብ ቁጥር 208/2003 ዓ/ም ላይ ሪከርድን የሚመለከተው ክፍል ወደ ተግባር የሚገባ ከሆነ አስቸጋሪ ሁኔታዎች እንደሚፈጠርባቸው ለስራ ማቆም አድማው የተሰጡት ምክንያቶች ነበሩ፡፡ ደንቡ በ2003 ዓ/ም እንደመውጣቱ እሪከርድን የሚመለከተው ክፍል ተግባራዊ መደረግ የጀመረው በ2008 ዓ/ም መሆኑ በራሱ የህግ አስፈጻሚውን ቸልተኝነት የሚያሳይ ሲሆን ደንቡን በመተግበር ረገድ ቀድመው የጀመሩ እንደ አማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ያሉትን ደግሞ በክልላቸው የሚንቀሳቀሱትን አሽከርካሪዎች በሀገሪቷ ውስጥ ካሉ ሌሎች አሽከርካሪዎች በተለየ ሁኔታ ተጎጂ ሲያደርጋቸው ነበር፡፡ ይህ ጽሁፍ ደንቡ የተሻሻለበትን ምክንያቶች አግባብነት፣ ማሻሻያው ውስጥ የተጨመሩ እና ማስተካከያ የተደረገባቸውን አንቀጾች እንዲሁም የማሻሻያውን አንድምታ በተወሰነ መልኩ ለመዳሰስ ይሞክራል፡፡

የደንብ ቁጥር 208/2003 መሻሻል አስፈላጊነት

የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ የሚንስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 208/2003 ዓ/ም / ከዚህ በኋላ "ደንቡ" እያለ ይቀጥላል / በርከት ያሉ ድንጋጌዎች ከያዙ እና የመንገድ ትራፊክ ፍሰትን ለማሳለጥ ከሚያስችሉ መሰረታዊ ህጎች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ለዚህ ደንብ መሻሻል ገፊ ምክንያት የሆነው ከደንቡ የሪከርድ ክፍል ጋር በተያያዘ የተነሳው ተቃውሞ ቢሆንም ከጊዜ ቆይታ እና የሁኔታዎች ተለዋዋጭነት አንጻር እንዲሁም ደንቡ ቀድሞውንም ሲወጣ ከነበሩበት የህግ አወጣጥ ችግሮች ጋር በተያያዘ መሻሻል የነበረበት በመሆኑ የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ማሻሻያ ደንብ ቁጥር 395/2009 ዓ/ም /ከዚህ በኋላ "ማሻሻያው" እያለ ይቀጥላል /መውጣቱ ተገቢነት ያለው ነው፡፡ ይህ ደንብ ሲሻሻል ከግምት ውስጥ ሊያስገባ የሚገባው መሰረታዊ ነጥብ ቢኖር ሀገሪቷ በአሁኑ ሰአት ከየትኛውም አደጋ በላይ በአመት ከ5000 /አምስት ሺ/ የሚበልጥ የሰው ሂወት እየቀጠፈ እና ከባድ የሆነ የንብረት ውድመት እያስከተለ ያለውን የትራፊክ አደጋን መቀነስ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር አብዛኞቹ የትራፊክ አደጋዎች የሚደርሱት በአሽከርካሪዎች ጥፋት መሆኑ እየታወቀ ሪከርድን የሚመለከተው የህጉ ክፍል የተሻሻለበት መንገድ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ከማስገባት ይልቅ በነበረው ተቃውሞ ተጽእኖ ስር ሆኖ የተሻሻለ ነው፡፡ ይህንን ከታች በዝርዝር እንመለከተዋለን፡፡ ሪከርድን ከሚመለከተው ክፍል ውጪ የተሻሻለው የደንቡ ክፍል ከነ ክፍተቶቹም ቢሆን ከዚህ ቀደም በደንቡ ላይ ግልጽነት የጎደላቸውን ድንጋጌዎች ለማስተካከል ከመሞከሩም በላይ አዳዲስ አንቀጾችን በመጨመር የደንቡን ክፍተቶች ጥሩ በሚባል መልኩ አስተካክሏል፡፡

መሰረታዊ ማሻሻያ የተደረገባቸው እና አዲስ የተጨመሩ ድንጋጌዎች በከፊል

Continue reading
  21822 Hits

የብሮድካስቲንግ ቁጥጥር/ሪጉሌሽን እና የባለሥልጣኑ ደብዳቤ

ስለሪጉላቶሪ መሳሪያዎች መግቢያ

ዛሬ የብሮድካስቲንግ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ለሁለት ብሮድካስተሮች ጽፈውታል የተባለ ደብዳቤ በፌስቡክ መለጠፉን ተከትሎ የተለያዩ አስተያየቶች እየተስተናገዱ ነው። በደብዳቤው ብሮድካስተሮቹ ለምን የቅዳሜውን የድጋፍ ሰልፍ እንዳላስተላለፉ መረጃ በተጠቀሰው ቀን ይዘው በመምጣት ከባለሥልጣኑ ጋር እንዲወያዩ ያሳስባል። ባለሥልጣኑ ይህን ደብዳቤ “ሊመልሰው፣ ይቅርታ ሊጠይቅ ይገባል”፣ እና የመሳሰሉት አስተያየቶች በመሰጠት ላይ ይገኛሉ። የዚህ ጽሑፍ አቅራቢ ምንም እንኳን በሚዲያ ተቋማት ዙሪያ የግሌ ጠቅላላ አስተያየትና እምነት ቢኖረኝም የብሮድካስቲንግ አዋጁን አስመልክቶ ያለኝን ግንዛቤና አረዳድ እንደሚከተለው አካፍላለሁ።

እንደሚታወቀው ብሮድካስቲንግ ባለሥልጣን ተቆጣጣሪ አካል ወይም ሪጉሌተር ነው። በመሆኑም ለመግቢያ ያህል በጠቅላላው በተለያዩ ማህበራዊና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮች የተለያዩ ሪጉላቶሪ አካላት የመቆጣጠር ስልጣናቸውን ምን ዓይነት የፓሊሲ ወይም የሪጉላቶሪ መሳሪያዎችን በመጠቀም እንደሚያሳኩ ባጭሩ እንመልከት። የተለያዩ ሪጉላቶሪ አካላት የሚከተሉትን ስምንት ዋና ዋና መሳሪያዎች በአማራጭ ወይም በስብጥር ይጠቀማሉ።

አንደኛው የፈቃድ ሥርዓት መዘርጋት ነው። በአንድ የተለየ ተግባር ላይ መሰማራት የሚፈልግ አካል፣ ወደ ተግባር ከመግባቱ በፊት ከሚመለከተው ተቆጣጣሪ/ሪጉሌተር ፈቃድ እንዲያወጣ ይጠበቅበታል። የፈቃድ ሥርዓት ከማሳወቅ ሥርዓት ይለያል። ምክንያቱም ፈቃዱ ሊከለከል ይችላል። ፈቃዱን ለማግኘት አመልካቹ ማሟላት ያለበት ቅድመ ሁኔታዎች በሕግ ይቀመጣሉ። እነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች የተለያዩ መልኮች ሊይዙ ይችላሉ፤  የዜግነት ወይም የነዋሪነት ግዴታ፣  የትምህርት ወይም የብቃት ደረጃ፣ የድርጅት ዓይነት (ለምሳሌ በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ለመሰማራት፣ የግድ አክሲዮን ማህበር ማደራጀት ያስፈልጋል ሊባል ይችላል)፣ የገንዘብ አቅም፣ ፈተና፣ ልምድ፣ እና የሃላፊነት መድን (በሥራው የተነሳ በሌሎች አካላት ላይ ጉዳት ቢያደርስ፣ ጉዳቱን የሚክስ መድን አስቀድሞ እንዲገባ ማድረግ።

ሁለተኛው የሪጉላቶሪ መሳሪያ የጥራት ቁጥጥር ነው። አንዴ ፈቃድ አግኝቶ ወደ ተግባር የገባ አካል፣ የሚያቀርባቸው ምርትና አገልግሎቶች ሊያሟሏቸው የሚገባቸውን የጥራት ደረጃ ቁጥጥር ማድረግ። የጥራት ቁጥጥር ሁለት ዓይነት ዋና ዋና የጥራት ስታንዳርዶችን በመጠቀም ይከናወናል። አንደኛው የተግባሩ ውጤት ወይም ፍሬ ሊያሟላው የሚገባ የጥራት መለኪያ በወለል ወይም በጣሪያ መልክ ሊቀመጥ ይችላል። ለምሳሌ የታሸገ ውሃ ሊኖረው የሚገባው ከፍተኛ የአርሰኒክ መጠን በተቆጣጣሪው አካል በሕግ ሊደነገግ ይችላል። ሁለተኛው የጥራት ስታንዳርድ ዓይነት የግብአት ወይም ቴክኖሎጂ ወይም የሂደት ጥራት ነው። በዚህኛው መሠረት የተግባሩ ውጤት ወይም ፍሬ ሊያሟላው የሚገባ የጥራት ደረጃ ሳይሆን ትኩረት የሚደረገው፣ ውጤቱን ወይም ፍሬውን ለማምረት ወይም ለማቅረብ አምራቹ ወይም አቅራቢው ሊጠቀመው የሚገባ የግብአት፣ ቴክኖሎጂ፣ ወይም ሂደት ዓይነትና ጥራት በሪጉላቶሪ አካሉ ወይም በሕግ አውጪው በሕግ ሊደነገግና ክትትል ሊደረግበት ይችላል። ሁለቱንም ዓይነት ስታንዳርዶችን አሰባጥሮ መጠቀም ቢቻልም ብዙ ጊዜ ሁለተኛው ዓይነት ስታንዳርድ የምንጠቀመው፣ የመጀመሪያውን ዓይነት ስታንዳርድ ማውጣት ወይም ክትትል ማድረግ አስቸጋሪ በሚሆንበት ጊዜ ነው። ለምሳሌ የትምህርት ተቋማትን የአገልግሎት ጥራት ለመለካት የስራቸው ፍሬ የሆኑትን ተማሪዎቻቸው ሊያሟሏቸው የሚገቡ የጥራት መለኪያዎችን ማስቀመጥ ከባድ ስለሆነ የትምህርት ተቋማቱ ሊጠቀሙባቸው በሚገቡ ግብአቶች (ለምሳሌ የትምህርት መጽሐፍት፣ የመማሪያ ክፍሎች፣ የተማሪና የአስተማሪ የቁጥር ምጣኔ)፣ ሂደቶችና ቴኬኖሎጂዎች ላይ ትኩረት ይደረጋል። እንዲሁም በከተሞች የሚቀርቡ የቧንቧ የመጠጥ ውሃን አስመልክቶ የመጀመሪያውን ዓይነት ስታንዳርድ ማውጣትቢቻልም፣ ክትትሉ ግን እጅግ አስቸጋሪ ስለሚሆንን እና አስተማማኝነቱም ዝቅተኛ ስለሚሆን በዋናነት በሁለተኛው ዓይነት የጥራት ስታንዳርድ ስራ ላይ ሲውሉ ይስተዋላል። ሊታወቅ የሚገባው ጉዳይ ሁለተኛው ዓይነት የሪጉላቶሪ መሳሪያ ለኪራይ ሰብሳቢነት የተጋለጠ ከመሆኑ በተጨማሪ፣ አማራጭ ቴክኖሎጂዎች፣ ግብአቶች፣ ወይም ሂደቶች እንዳይዳብሩ ወይም እንዲከስሙ ማድረጉ ነው።

Continue reading
  9035 Hits

ደብዳቤው

ያው ጉባኤው የሚለውን ርእስ መኮረጄ ነው

እየመረጥክ ከዘገብክ የገለልተኝነት እና የእኩልነትን መርህ ጥሰሃል፡፡

/በበውቀቱ እስታይል/

ተከታዮ የመጀመሪያ አንቀፅ ለአገላለፅ ውበት እንጅ በጉዳዩ ላይ ያለኝ መቆጨት እንዳገላለፁ አለመሆኑ ይታወቅልኝ፡፡

የኢትዮጵያ ፕሮድካስቲንግ ባለስልጣል ለኢ ኤን ኤን የቴሌቪዚን ጣቢያ የፃፈውን ደብዳቤ እዚህ የፌስቡክ መንደር ውስጥ እያወቁ በድፍረት ሳያውቁ በስህተት እንደሆን እንጃ እጅጉን ሲተች ባይ ሆድ ባሰኝ፤ እንባየ መጣ ፤ቁጭት ልቤን መዘመዘው፤ አላስችል አለኝ በመጀመሪያ መብት የለውም አሉ ዝም አልኩኝ እነሱ ግን ይህን ሳያርሙ ሌላ ገደፉ እንዴት  ማለት ሲገባቸው ስህተት ነው ብለው ተናገሩ፡፡ በዚህ መች አብቅተው  እኩልነት ተጥሷል እል ብለው የሀሳብ ነጻነት ተደፍሯል ብለው አረፉ እንግዲህ ይህን ዝም ብሎ ማለፍ እንደምን ይቻላል፡፡ ምእመናን  አሳምራችሁ እንደምታወቁት የመገናኛ ብዙሃን መሰረት ገለልተኝነት እና በእኩልነት መርህ መገዛት አይደለምን? የመረጃ ነጻነት አደጋ ላይ የወደቀው እነዚህን መርሆች በጥብቅ ባለመከበራቸው መሆኑስ ይዘናጋል ምእመናን፡፡ እነዚህን መርሆች አለማክበርስ የመገናኛ ብዙሃንን ሃላፊነት በቅጡ ካለመረዳት የመጣ አይደለምን? መቼም ይህን ለማወቅ በዘርፉ ሙህር መሆን ይጠይቃል እያልኩ አይደለም ጎበዝ አስተዋይ ለሆነ ሰው ባለፈው ግዜ ሚዲያዋች የሰሩትን በማየት  ሚዲያዎቹ አድር ባይ የመንግስት አፈ ቀላጤ የነበሩ መሆናቸውን  መረዳት ይቸግረዋል ወይ ምእመናን? ስለዚህ እንደኔ እንደኔ ይን ጉዳይ በቀላሉ ልናልፈው አይገባም ባይ ነኝ፡፡

Continue reading
  8171 Hits

አንዳንድ ጉዳዮች ስለ ግብርና እድገትና የመሬት ፓሊሲና ሕግ

 

 

የግብርና እድገትና የመንግስት ሚና

ግብርና የሃገራችን ወሳኝ የኤኮኖሚ ዘርፍ ነው። ምጣኔ ሃብት ምሁሮች እንደሚሉት፥ በቅጥርና አገራዊ ምርት የግብርናው ድርሻ እንዲቀንስ (በሌሎች ዘርፎች እንዲተካ)፥ ግብርናው በፍጥነት ማደግ አለበት። ለማነስ፤ በፍጥነት ማደግ።

የግብርና እድገት ምን ይጠይቃል? የመስኖ መሰረተልማት። የተሻሻለ ግብአት፥ ምርጥ ዘር፥ ማዳበሪያ፥ አረም ማጥፊያ። የምርት ገበያ። መሬት። ጉልበት። እውቀት። የገጠር መንገድ። የአርብቶ እና አርሶ አደሮች ትምህርት። የገጠር የጤና አገልግሎት። የገጠር የመጠጥ ውሃ አገልግሎት። የገጠር ሃይል አቅርቦት። የገጠር ሰላምና ደህንነት ማስከበር። የግብርና ግብይቶችን እና ድርጅቶችን መጠበቅ።

እነዚህን ሁሉ ማነው የሚያቀርበው? አሁን ባለበት ሁኔታ እነዚህን ሁሉ በዋናነት የሚያቀርበው መንግስት ነው። የፌዴራሉ መንግስት፥ የክልሎች መንግስታት፥ እና አካባቢያዊ መስተዳድሮች። የእነዚህ ሁሉ ዋና አቅራቢ መንግስት ሆኖ፥ እንዴት ነው ታዲያ ግብርናውን በፍጥነት ማሳደግ የሚቻለው? መንግስት እኮ ከግብርናው በተጨማሪ ሌሎች ሃላፊነቶችም አሉበት።

Continue reading
  10774 Hits

ተጨማሪ ሃሳቦች ስለ ግብርና እድገትና የመሬት ፓሊሲና ሕግ

 

ከዚህ በፊት ባለው ጽሁፍ የሚከተሉትን ሃሳቦች አቅርቤ ነበር። በዋናነት የእነዚህ ሃሳቦች ተግባራዊነት ዉጤት፤ አሁን ተበጣጥሶ የሚገኘውን በገጠር መሬት ላይ የግብርና ውሳኔ መብት በአንጻራዊነት እንዲማከል ማድረጉ ነው። የግብርና ውሳኔ ማለት፥ በአንድ እርሻ ላይ ምን ላምርት? መቼ ላምርት? ምን አይነት እና መጠን ያለው ማዳበሪያ ልጠቀም? ምን አይነት የውሃ ቴኬኖሎጂ ልጠቀም? ምን አይነት ማረሻ፥ ማጨጃ፥ እና መውቂያ ልጠቀም? ምን አይነት የመሬትና አፈር ጥበቃና አስተዳደር አሰራሮችን ልከተል? እና የመሳሰሉት ናቸው። ከግብርና ውሳኔዎች ጋር የሚገናኙ የገበያ ውሳኔዎች ይኖራሉ። ለምሳሌ፤ ምን ያህል ምርቴን፥ መቼ፥ ለማን ልሽጥ? ምን ያህል ገንዘብ፥ ከማን፥ በምን ያህል ወለድ ልበደር? እነዚህና የመሳሰሉት ገበያ ነክ ውሳኔዎች ካነሳኋቸው ነጥቦች ጋር በቀጥታ አይገናኙም። እኔ ያነሳሁት የግብርና ውሳኔዎችን ነው።

አሁን ባለው ሁኔታ ሁለት አይነት መበጣጠሶች ይታያሉ። አንደኛው በቀደመው ጽሁፍ እንዳብራራሁት የመሬት መበጣጠስ አለ። በእርግጥ የመሬት መበጣጠሱ ሁኔታ እንደቦታው ይለያያል። እኔ ያደኩበትን አካባቢ ኢህአዴግ ከደርግ ነጻ እንዳወጣና ደርግን ተክቶ የሕዝብ አስተዳደር ሃላፊነትን ሲወስድ ካደረጋቸው ነገሮች አንደኛው መሬትን መልሶ ማከፋፈል ነው። ለምን? ምክንያቱም ጥቂት ‘አድሃሪያን’ ፍትሃዊ ባልሆነ መንገድ ጥሩ ጥሩ መሬቱን በብዛት ስለያዙት። እኔ በበኩሌ የመሬት ክፍፍልና ራሱን አልቃወምም። የኔ ነጥብ የዚህ መሬት ክፍፍልና የክፍፍሉ ስልት ስለፈጠረው የመሬት መበጣጠስ ነው። እንደገለጽኩት አንድ ገበሬ ከግማሽ ኳስ ሜዳ ያነሱ፥ ሶስትና አራት እርሻዎች ይኖሩታል። አንደኛው የጓሮ መሬት ሲሆን ሌሎች ከመኖሪያ ጎጆዉ በተለያየ አቅጣጫ በተለያየ እርቀት ይገኛሉ።  የመሬት መበጣጠስ የምለው ይሄን ነው። ሁለተኛው አይነት መበጣጠስ፥ የግብርና ውሳኔዎችን የመስጠት መብት መበጣጠስ ነው።

 

ኤኮኖሚ ኦፍ ስኬል (economy of scale)

የሁለት አይነት መበጣጠሶች፥ መጠን/ስኬል ከሚያስገኘው ጥቅም መጠቀም እንዳንችል ሆኗል። ብዙ አይነት የስኬል ጥቅሞች አሉ። አንደኛው ስኬል የሚባለውና ብዙ የሚታወቀው፥ ‘ኤኮኖሚ ኦፍ ስኬል’ ነው። ‘ኤኮኖሚ ኦፍ ስኬል’ ማለት በብዛት በማምረት የሚገኝ የነፍስ ወከፍ ወጪ መቀነስና የምርት መጨመር ነው።

Continue reading
  8588 Hits

የድሬዳዋ አስተዳደር ቻርተር አዋጅ፤ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ሕግ የማውጣት ሥልጣን እና የአስተዳደሩ ተጠሪነት ጉዳይ

 

 

የዚህ አጭር ጽሑፍ ዋና ትኩረቱን በድሬዳዋ አስተዳደር ቻርተር አዋጅ ቁጥር 416/1996 ላይ በማድረግ አዋጁ ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግስት በአንቀፅ 55(1) ላይ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ከተሰጠው ሕግ የማውጣት ስልጣን ጋር ያለውን ተቃርኖ እና የሕገ መንግስቱን የበላይነት ያላከበረ ስለመሆኑ እንዲሁም የድሬዳዋ አስተዳደር ተጠሪነት ላይ የሚነሱ የሕግ ጉዳዮችን በመዳሰስ መፍትሔውን ማስቀመጥ ነው፡፡

በአስራ አንድ ምዕራፎች እና በአንድ መቶ ስድስት አንቀጾች የተዋቀረው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግስት ህዳር 29 ቀን 1987ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በተወካዮቻቸው አማካኝነት አፅድቀውት ከነሐሴ 15 ቀን 1987 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ስራ ላይ እንደዋለ ከሕገ መንግስቱ መግቢያ እና በአንቀፅ 2 ላይ የተገጾ የምናገኘው ሲሆን ሕገ መንግስቱ በምእራፍ አራት እና አምስት ስለመንግስታዊ አወቃቀር እንዲሁም ስለሥልጣን አወቃቀርና ክፍፍል በሚገልፀው ክፍል ደግሞ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ስርዓተ መንግስት ፓርላሜንታዊ እንደሆነ፤ በፌዴራል መንግስት እና በክልሎች የተዋቀረ እንደሆነ፤ ክልሎቹም ዘጠኝ (ትግራይ፤ አፋር፤ አማራ፤ ኦሮሚያ፤ ሶማሌ፤ ቤንሻንጉል/ጉሙዝ፤ ደቡብ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች፤ የጋምቤላ ሕዝቦች እና የሐረሪ ሕዝብ ክልል) እንደሆኑ፤ አዲስ አበባም የፌዴራሉ መንግስት ርዕሰ ከተማ እንደሆነችና የከተማ አስተዳደሩም ተጠሪነቱ ለፌዴራል መንግሰቱ ሆኖ ዝርዝሩ በሕግ የሚወሰን እራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ ስልጣን እንዳለው ተደንግጎ ይገኛል፡፡

በተጨማሪም በአንቀፅ 51 ላይ የፌዴራሉን መንግስት ስልጣን እና ተግባር የሚዘረዝር ሲሆን በአንቀፅ 55(1) ላይ ደግሞ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሕገ መንግስቱ ለፌዴራሉ መንግስት በተሰጠው የስልጣን ክልል ሕጎችን እንደሚያወጣ ይገልፃል፡፡

Continue reading
  9538 Hits

ፍርዶች ዳግመኛ ሰለሚታዩባቸው መንገዶች (Review of Judgments)

 

ፍርድን እንደገና መመርመር ማለት ምን ማለት ነው?

ፍርድን እንደገና መመርመር (Review of Judgments) ማለት በአንድ በተወሰነ ጉዳይ ላይ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች የሰጡት ፍርድ /ውሳኔ/ የፍርድ ባለዕዳውን ወይም የፍርድ ባለመብቱን ቅር ሲያሰኘው ወይም አጥጋቢ ሆኖ ሳያገኘው ሲቀር ይህ የተሰጠው ፍርድ ዳግመኛ ይታይለት ዘንድ ሊጠቀምበት የሚችልበት ጠቃሚ የሥነ-ሥርዓት ሕግ አካል ነው፡፡

ፍርዶች ዳግመኛ ለምን ይታያሉ?

የፍርድ ቤቶች ውሳኔ በተለያየ መንገድ የዜጐችን የአኗኗር ዘይቤ ጥሩም መጥፎም የማድረግ እድላቸው ከፍተኛ ነው፡፡ ይህም ማለት ፍርድ ቤቶች ከሶሶቱ የመንግስት አካላቶች መካከል የዜጐች መብትና ነፃነት እንዲከበር እንዲሁም ፍትህን ከማስፈን አኳያ ያላቸው አስተዋፅኦ እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ ጉዳዬችን የሚያጤኑበት ወይም የሚመረምሩበት መንገድ እጅግ ጥንቃቄ የተሞላበት እንዲሁም በሕግና በሥርአት የተደገፈ መሆን አንዳለበት ይታመናል፡፡ ከተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ ፍርድ ቤቶች የሚሰጡት ውሳኔ ስህተት ሊሆን ወይም ደግሞ የሕጐችን አጠቃላይ መንፈስ ያልተከተለ የሚሆንባቸው አጋጣሚዎች እጅግ በርካታ ናቸው፡፡ ለዚህም በአሁኑ ሰዓት በሀገራችን በይግባኝ ፍርድ ቤቶች እና በሰበር ሰሚ ችሎቶች ተከማችተው የሚገኙትን የጉዳዬች ብዛት መመልከት በቂ ነው፡፡ ተከራካሪ ወገኖች ልክ እንደማንኛውም ዜጋ ፍትህ የማግኘት ሕገ- መንግስታዊ መብት ባለቤት በመሆናቸው ትክክል አይደለም ብለው የሚያስቡትን ፍርድ የተሻለ ፍትህ እናገኝበታለን ብለው ወደሚያስቡት የፍትህ ተቋም ጉዳያቸው ዳግመኛ እንዲታይላቸው መጠየቅ ይችላሉ መንግስትም ይህ የዜጐች የተሻለ ፍትህ የማግኘት መብት አንዲከበር ሊያግዝ የሚችል ተቋማዊ መዋቅር መዘርጋት ይጠበቅበታል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በአንድ ሀገር የሕግ ሥርአት (legal system) ውስጥ ወጥ (uniform) የሆነ የሕግ አተረጓጎም እንዲኖር ለማስቻል የፍርድ ቤቶችን ውሳኔ እንደገና መመርመር የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ መዘርጋት አስፈላጊ ነው፡፡

Continue reading
  11417 Hits

የሕዝብ ተሳትፎ በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ ያለው ሚና

 

 

1. መግቢያ

ቀደም ባሉት ጊዜያት የፍትሕ ሥርዓት ቅቡልነት እና የሕዝብ አመኔታ መሠረት ተደርገው የሚወሰዱት ቢሮክራሲ፣ ምክንያታዊነት እና ሞያን መሠረት ማድረግ ነበር፡፡ በመሆኑም በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ ዋና ተዋናዮች የሕግ ባለሞያዎች እና ሌሎች የፍትሕ አካላት ባለሞያዎች ሲሆኑ፣ ሌሎች ማህበረሰብ አካላትን ያገለለ ሆኖ ቆይቷል፡፡ ስለሆነም መንግሥት እና የሕግ ሰዎች ፍትሕ የማስፈን ሀላፊነትን በብቸኝነት በመያዝ አባታዊ የአስተዳደር ዘዴ (Paternalistic Approach) ሲከተሉ ነበር፡፡ የዚህም አጠቃላይ አሠራር ሁሉን ነገር ለባለሙያ የመተው (Leave to the professional) የምንለው ነው፡፡ ይህም የወንጀል ተጠቂዎችን እና ባለጉዳዮችን እንዲረሱ በማድረግ ኒልስ ክሪስቲ እንደተባሉ አንድ ፀሐፊ አባባልየራሳቸውን ጉዳይ በባለሙያዎች ተሰርቀዋል፡፡

የዚህ አይነት አሠራር ሁሉም ችግር የሚፈታው በባለሙያ ነው የሚል አመለካከት ህብረተሰቡ እንዲያዳብር አድርጓል፡፡ ነገር ግን ማህበሰቡ በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ በተለያየ ደረጃ የሚኖራቸው ተሳትፎ ወሳኝ እና ቁልፍ ባለድርሻ መሆኑ እውቅና ሊሰጠው ይገባል፡፡ በዚህ ጽሑፍም የማህበረሰብ ተሳትፎ በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ በወፍ በረር እንቃኛለን፡፡

Continue reading
  9730 Hits

ሰበር ለመታረቅ በተደረገ ስምምነት ላይ የያዘው አቋም ሲፈተሽ

 

ኢትዮጵያ ውስጥ የዳኝነት ሥልጣን ያላቸው ፍርድ ቤቶች ብቻ አይደሉም፡፡ ይህን ሥልጣን የተጎናፀፉ ብዙ አካላት አሉ፡፡ ለአብነት ያህል ለመጥቀስ፡- በፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር ውስጥ የሚገኘው የአስተዳደር ፍርድ ቤት ከሥራ መሰናበት፣ ደመወዝ መቁረጥና የመሳሰሉትን ጥያቄዎች አስመልክቶ በመንግሥት ሠራተኛውና  በፌዴራል መንግሥት መሥሪያ ቤት መካከል የሚነሳ አለመግባባት ላይ ዳኝነት ይሰጣል፡፡ ሕገ መንግሥቱን መተርጎም ላይ አለመግባባት ከተፈጠረ ዳኝነት የመስጠት ሥልጣን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ነው፡፡ በግብር ጉዳዮች ላይ የግብር ይግባኝ ሰሚ ኮሚሽን የዳኝነት ሥልጣን አለው፡፡ የማኅበራዊ ዋስትና መብትና ጥቅም  ጥያቄዎች ላይ የዳኝነት ሥልጣን ለማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ ተሰጥቷል፡፡ የከተማ ቦታ ማስለቀቅና የካሳ ጉዳዮች ላይ የዳኝነት ሥልጣኑ በየከተማ አስተዳደሮች ለሚቋቋሙ ጉባዔዎች ተሰጥቷል፡፡ የንግድ ውድድር ጨቋኝ የሆኑ ድርጊቶችና ያልተገባ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ደግሞ ዳኝነት የሚሰጥ የንግድ አሠራርና የሸማቾች ጥበቃ ባለሥልጣን የሚባል ተቋም አለ፡፡ ወታደራዊ ፍርድ ቤቶችም አሉ፡፡ ይሁን እንጂ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ያለውን የዳኝነት ሥልጣን ያህል የተጎናፀፈ ፍርድ ሰጪ አካል ኢትዮጵያ ውስጥ የለም ለማለት ያስደፍራል፡፡ የዚህን ችሎት የዳኝነት ሥልጣን ሊወዳደር ወይም ሊበልጥ የሚችል ፍርድ ሰጪ አካል ኢትዮጵያ ውስጥ ካለ፣ የሕገ መንግሥት ትርጓሜ ላይ ዳኝነት የመስጠት ሥልጣን ያለው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ብቻ ነው፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የዳኝነት ሥልጣን ያላቸው አካላትን በሙሉ የፍርድ ሰጪነት ሥልጣናቸውን ሲጠቀሙ መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለመፈጸማቸውን ይቆጣጠራል፡፡ በተጨማሪ ይህ ችሎት አንድ የሕግ ድንጋጌን የተረዳበት ወይም የተረጎመበት መንገድ ሁሉም የሥር ፍርድ ቤቶች ሊከተሉ ይገባ ዘንድ ግዴታ አለ፡፡ ማለትም፣ ፍርድ ቤቶችና ሌሎች ፍርድ ሰጪ አካላት የሰበር ችሎቱ አንድን የሕግ ድንጋጌ ከተረጎመበት ውጪ አፈንግጠው የራሳቸውን ትርጉም መስጠት አይችሉም፡፡ ስለዚህ የሰበር ችሎቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ፍርድ ሰጪ አካላት ውስጥ ቁንጮ ላይ የሚቀመጥና የዳኝነት ሥርዓቱ ላይ ሰፊ ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆነ ተቋም ነው፡፡

ሰፊ ሥልጣን ሲኖር ደግሞ ሊነጠል የማይችል አብሮ የሚመጣ ግዴታ አለ፡፡ ሰፊ ሥልጣን በጠለቀ ዕውቀት፣ ገደብ የለሽ አስተዋይነትና ሰባዊነት መታጀብ አለበት፡፡ የዜጎች ነፃነት፣ ሕይወትና ደስተኝነት ላይ ተፅዕኖ የመፍጠር ሥልጣን የተሰጠው አካል ሁሉ ሥልጣኑን ሲጠቀም የመጠቀ ዕውቀት፣ የመተንተን ክህሎት፣ አስተዋይነትና ሰባዊነት በማይነጣጠል ሁኔታ ማንፀባረቅ አለበት፡፡ የፌዴራል ሰበር ሰሚ ችሎት ሰፊ የዳኝነት ሥልጣን ቢጎናፀፍም የጠለቀ የሕግ ዕውቀት፣ ትንታኔ እና መርማሪነት ግን በውሳኔዎቹ ማንጸባረቅ የቻለ መስሎ አይታይም፡፡ ይህ ደግሞ በራሱ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የማይካድ ሀቅ ነው፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት የሆኑት አቶ ተገኔ ጌታነህ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ውሳኔዎች ይዞ በሚወጣው ቅጽ 15 መግቢያ ላይ ‹‹አልፎ አልፎ በውሳኔዎች ጥራትና ሥርጭት ሊታዩ የሚችሉ ችግሮች ሥርዓቱ እየተጠናከረ ሲሄድ የሚፈቱ ሲሆን፣ እነዚህን ችግሮች ለማቃለል እኛም ጥረት በማድረግ ላይ እንገኛለን፡፡ ጥረታችን ሊሳካ የሚችለው በውሳኔዎች ላይ በሕግ ምሁራንና ባለሙያዎች ገንቢ የሆኑ ትችቶችና አስተያየቶች ሲቀርቡ ነው፤›› ሲሉ ጠቁመዋል፡፡

በዚህ ጽሑፌ አንድ ጭብጥን አስመልክቶ የሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠው ውሳኔ ሌላው ቀርቶ ጀማሪ የሕግ ተማሪዎች የሚማሩበት መጽሐፍ ላይ በቀላሉ የሚገኝ ዕውቀትን ማንፀባረቅ እንዳልቻለ ለማሳየት እሞክራለሁ፡፡ ጭብጡን አስመልክቶ የዛሬ ስምንት ዓመት በብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያና በዘላቂ ግብርና ተሃድሶ ኮሚሽን ጉዳይ ላይ (የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች ቅጽ 7 ገጽ 148 ይመልከቱ) የሰጠውን ውሳኔ አሁን ደግሞ በቅርቡ በቦሮ ትራቭል የግንባታ ሥራዎች ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበርና በአቶ ኤፍሬም ሽብሩ ጉዳይ ላይ ደግሞ ደግሞታል፡፡ (የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች ቅጽ 17 ገጽ 358 ጀምሮ ይመልከቱ)፡፡

Continue reading
  7618 Hits