በኢትዮጵያ የብድር ሕግ "አበደረ" ማለት የብድሩን ገንዘብ ሰጠ ማለት ይሆን?

በዚህ በኩል ግቡ

ብድር የሰው ልጅ እና ጎደሎው ከተገናኙበት ሩቅ ዘመን ጀምሮ የነበረ ሰዋዊ ድርጊት ነው፡፡ የብድር መሰረቶቹ መቀራረብ፣ እዝነት እና መተማመን ናቸው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ግን እነዚህ መሰረቶቹ እየተናጉ የብድርን ህልውና ሲፈታተኑት ይስተዋላል፡፡ በርካታ ሰዎችም ብድርን መሰረት ላደረጉ ክርክሮች ሲዳረጉ ይታያሉ፡፡

ከእነዚህ በርካታ ብድር ነክ ክርክሮች አንዱ በውሉ ላይ ተበዳሪ ተብለው የተሰየሙ ሰዎች የብድሩን ገንዘብ አልተቀበልኩም በማለት የሚያነሱት ክርክር ነው፡፡ ተበዳሪው በውሉ ላይ ተበድሬአለሁ ብሎ የፈረመ ቢሆንም ውሉ ፍ/ቤት ሲመጣ ግን ተበድሬአለሁ ብዬ ፈርሜአለሁ ግን የብድሩን ገንዘብ አልተቀበልኩም ማለት ይከራከራል፡፡

Continue reading
  3669 Hits

በጽሑፍ የሰፈረን የውል ቃል የምስክርና ሌላ ዓይነት ማስረጃን በማቅረብ ማሻሻል ይቻላል?

የጉዳዩ መነሻ

ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ በመዝገብ ቁጥር 78398 በአቶ ሽፈራዉ ደጀኔ እና ወ/ሮ ጸሀይ ተስፋዬ በአንድ በኩልና በአቶ ሲሳይ አበቡ በሌላ በኩል በተደረገ ሙግት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ጥቅምት 19 2005 የሰጠዉ ዉሳኔ ነዉ፡፡ ጉዳዩ የተጀመረዉ በወረዳ ፍርድ ቤት በአቶ ሲሳይ አበቡ ከሳሽነትና በአቶ ሽፈራዉ ደጀኔ እና ወ/ሮ ጸሀይ ተስፋዬ ተከሳሽ ነዉ፡፡ ከሳሹ እንደሚለዉ በእሱና በተከሳሹ መካከል ሐምሌ 17 2003 የተቋቋመ የቤት ሽያጭ ዉል አለ፡፡

Continue reading
  16229 Hits

የሽያጭ ውልን የተመለከቱ አንዳንድ ነጥቦች ከሰበር ውሳኔ ጋር ተገናዝቦ የቀረበ

 

መግቢያ

በዚህ ጽሑፍ የሽያጭ ውል ምንነት፣ የማይንቀሳቀስ ንብረት የገዛ ሰው ስላለው መብትና ገዥው ስለሚኖርበት ግዴታ፣ የሽያጭ ውልን መሰረት አድርገው የሚቀርቡ ክርክሮች ይዘታቸው እና  የይርጋ ገደባቸው ምን እንደሚመስል እንዲሁም የማይንቀሳቀስ ንብረት የገዛ ሰው ንብረቱን ሊለቅ የሚችልባቸው የሕግ አግባብ ምን ምን እንደሆኑ ከፍትሐብሔር ሕግ እና ከሰበር ውሳኔዎች አንጻር ዳሰሳ ለማድረግ ተሞክሯል፡፡   

Continue reading
  5539 Hits

እንዴት ያለባለቤቱ ሙሉና ነጻ ፈቃድ የተላለፈን ንብረት ማስመለስ፤ የተቋቋመን የመብት ገደብ ማስነሳት ይቻላል?  

 

ጥያቄው?

በዚህ ጽሁፍ መመለስ የምፈልገው ጥያቄ ቀላል ይመስላል፤ እንዴት ያለባለቤቱ ሙሉና ነጻ ፈቃድ የተላለፈን ንብረት ማስመለስ፤ የተቋቋመን የመብት ገደብ ማስነሳት ይቻላል የሚለውን ነው፡፡ ቀጥታ ጥያቄውን ወደ መመለሱ ከመሄዴ በፊት፤ ጥያቄው የሚመለከታቸው ሁኔታዎች ምን አይነቶቹን እንደሆነ ግልጽ ላድርግ፡፡

ያለ ሙሉና ነጻ ፈቃድ ሲባል?

እንደሚታወቀው ንብረትን (የማይንቀሳቀስም ይሁን ልዩ ወይም ተራ የማይንቀሳቀስ) ለሌላ ሰው ውልን መሰረት አድርጎ ለማስተላለፍ የባለቤቱ ሙሉና ነጻ ፈቃድ ያስፈልጋል፡፡ ባለቤቱ ፈቃዱን ሰጥቷል ነገር ግን ፈቃዱ ሙሉ እና ነጻ አልነበረም የሚባለው የባለቤቱ ፈቃድ በስህተት ወይም በማታለል ወይም በሃይል ተግባር ምክኒያት የተሰጠና በሕጉም መሰረት ውሉ ፈራሽ ውል ሲባል ነው፡፡ ባለቤቱ ፈቃዱን የገለጸው ራሱ ወይም በወኪሉ በኩል ሊሆን ይችላል፡፡ በመሆኑም በዚህ ሁኔታ የባለቤቱ ፈቃድ ጉድለት አለበት፤ ነገር ግን ንብረቱ ተላልፎ ሊሆን ይችላል ወይም የመብት ገደብ ተቋቁሞ ሊሆን ይችላልና እንዴት ባለቤቱ ንብረቱን ማስመለስ ገደቡን ማስነሳት ይችላል የሚል ጥያቄ ያስነሳል፡፡

ባለቤቱ በምንም አይነት መልኩ ፈቃዱን ሳይገልጽ ከሆነስ?

በሁለተኛ ደረጃ የንብረት ማስመለሱና የመብት ገደቡን የማስመለስ ጥያቄ ሊነሳ የሚችለው ከመጀመሪያውኑ ባለቤቱ በምንም መልኩ ፈቃዱን ያልገለጸ ከሆነ ነው፡፡ ባለቤቱ ፈቃዱን ሳይገልጽ እንዴት ንብረት ይተላለፋል ወይም መብት ይገደባል ለሚል ጥያቄ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ሁኔታዎች መልስ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

1. አንድ ሰው ህጋዊ ባለቤት ሳይሆን ባለቤት እንደሆነ በማስመሰል ከሌላ ሰው ጋር በመዋዋል ንብረቱን ሊያስተላልፍ ወይም የመብት ገደብ ሊያቋቁም ይችላል፡፡ ንብረቱ ተራ የሚንቀሳቀስ ንብረት ከሆነ ይህን ለማድረግ ቀላል ነው፡፡ ንበረቱ የማይንቀሳቀስ ወይም ልዩ ተንቀሳቃሽ ቢሆንም ይህን ለማደድረግ ቀላል ነው፡፡ ነገር ግን ሰነዶችን ፎርጅድ ማድረግ ሊጠይቅ ወይም የሌላ አካል ትብብርን ሊጠይቅ ይችላል፡፡ እነዚህ ሰነዶች ይህ ሰው ባለቤት መሆኑን የሚያሳዩ ወይም ንብረቱን አስመልክቶ በባለቤቱ ስም ውል የመዋዋል ስልጣን አንዳለው የሚያሳዩ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

Continue reading
  19706 Hits

በኢትዮጵያ ሕግ የግል የኮንስትራክሽን ውሎች ምንነት፣ የሚስተዋሉ አንዳንድ ችግሮችና የመፍትሔ ሀሳቦች

 

“And they said, Go to, let us build us a city and a tower, whose top may reach unto heaven; let us make as a name, lest we be scattered abroad upon the face of the whole earth…Therefore is the name of is called Babel; because the Lord did there confound the language of all earth…” Genesis 11:4-9

መግቢያ

የኮንስትራክሽን ውል በጣም ውስብስብና ብዙ ባለድርሻ አካላትን የሚያሳትፍ ውል ነው፡፡ በይዘትም ሆነ በጥልቀት በጣም ሠፊ ከመሆኑ የተነሳ ውቂያኖስ መሰል ውል ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ ለምን ቢባል በተለያየ ዕውቀትና ሙያ ዘርፍ የሚሳተፋ ሰወች ከመኖራቸው አልፎ በየደረጃው ዘርፈ ብዙ ግንኙነቶች መኖራቸው፤ የተለያዩ ጊዜ ወሰድ የዲዛይን ለውጦችና ማሻሻያወች ስለሚስተዋሉበት ጭምር  ነው፡፡

ኮንስትራክሽን የሰው ልጅ ወደ ምድር ከመጣ ጊዜ ጀምሮ የነበረ፤ ያለና የሚኖር እንቅስቃሴ ነው፡፡ የመጀመሪያው ግንባታ የሚባለውም በጥንታዊ ጋርዮሽ ሥርዓተ ማኅበር የሰው ልጅ ለመጠለያነት የተጠቀማቸው መጠለያ ጎጆወች ናቸው፡፡ በዓለም ታሪክም አንኳር የሚባሉ ግንባታወች ወስጥ ዋና የሚባሉት በጽሑፋ መግቢያ ላይ የተጠቆመው የባቢሎን ግንብ፤ ግብፅ (ምስር) ውስጥ በፈርዖኖች 2700-2500 . የተሰሩ ፒራሚዶች፤ በንጉስ ሽን ሁኣንግ ትዕዛዝ በጄኔራል ሜይንግ ቲን 220 . ገደማ የተሰራው ታላቁ የቻይና ግንብ እና የሮማዊያን የውሃ ማቆሪያ ግንባታወች ተጠቃሽ ናቸው፡፡

Continue reading
  21396 Hits

ያልተመለሰ የገንዘብ ብድር ያለስምምነትና ያለማስታወቂያ/ያለማስጠንቀቂያ ወለድ ይቆጥራል?

የጉዳዩ መነሻ

ለዚህ አጭር ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት በሰበር መዝገብ ቁጥር 74950 የሰጠዉ ዉሳኔ ነዉ፡፡ ጉዳዩ የገንዘብ ብድርን ይመለከታል፡፡ ተበዳሪ ከአበዳሪ በታሕሳስ 26 ቀን 1995 የተወሰደዉን ብር 237000.00 በጥር 30 ቀን 1995 ለመመለስ ቃል ገብቷል፡፡ ነገር ግን ገንዘቡን ሳይመልስ በመቅረቱ የአበዳሪ ወራሾች በተበዳሪ ላይ ሐምሌ 21 ቀን 2002 ባስገቡት ክስ ተበዳሪ ዋናዉን ገንዘብ እንዲመልስና ከየካቲት 01 ቀን 1995 መሰረት የሚታሰብ ወለድም እንዲከፍል ዳኝነት ይጠይቃሉ፡፡ ተበዳሪ በበኩሉ በዉላቸዉ ዉስጥ ወለድ ይከፍላል የሚል ቃል እንደሌለና ማስታወቂያ/ማስጠንቀቂያ ስላልተሰጠዉ ወለዱን መክፈል እንደማይገደድ ይከራከራል፡፡ በዚህ ሙግት የተነሳዉና ይህ ጽሁፍ የሚዳስሰዉ ጥያቄም ይኸዉ ነዉ፤ ያልተመለሰ የገንዘብ ብድር ያለስምምነትና ያለማስታወቂያ/ያለማስጠንቀቂያ ወለድ ይቆጥራል?

ከፍተኛዉ ፍርድ ቤት

ጉዳዩን ለመጀመሪያ ጊዜ የተመለከተዉ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ የብድር መመለሻ ጊዜዉ ቁርጥ (ጥር 30) ባለመልኩ ስለተቀመጠ በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1775(ለ) መሰረት ይህ ጊዜ ካለፈ በኋላ ገንዘብ ጠያቂዉ ማስጠንቀቂያ መስጠት አያስፈልገዉም፡፡ ስለሆነም ማስጠንቀቂያ ስላልተሰጠኝ ወለድ ልከፍል አይገባም የሚለዉ ክርክር ተቀባይነት ስለሌለዉ ተበዳሪ ከየካቲት 01 ቀን ጀምሮ ገንዘቡ ተከፍሎ እስከሚያልቅ ድረስ ከሚታሰብ ሕጋዊ ወለድ ጋር ዋናዉን የብድር ገንዘብ ይክፈሉ ሲል ወስኗል፡፡

ጠቅላይ ፍርድ ቤት

Continue reading
  12614 Hits

‘መንግስት ወይም ለሕዝብ አገልግሎት የቆመ መስሪያ ቤት ላይ’ ግዴታ የሚጥሉ ዉሎች በምን አይነት ቅርጽ መሆን አለባቸዉ?

መግቢያ

የፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 1724 እንዲህ ይነበባል፤ መንግስት ወይም ለሕዝብ አገልግሎት የቆሙ መስሪያ ቤቶች ግዴታ የሚዋዋሉባቸዉ ዉሎች ሁሉ በጽሁፍና በሚገባ አኳኋን በፍርድ ቤት መዝገብ ወይም ባንድ ባስተዳደር ክፍል መስሪያ ቤት መዝገብ ወይም ዉል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠዉ ሰዉ ፊት መሰራት አለባቸዉ፡፡ እንግሊዘኛዉ ደግሞ እንዲህ ይነበባል፤ Any contract binding the Government or a public administration shall be in writing and registered with a court, public administration or notary. የኪራይ ቤቶች አስተዳደር ድርጅት የሚዋዋላቸዉ ዉሎች በዚህ የፍ/ብ/ሕ/ቁ.1724 የሚወድቁ ናቸዉ ወይ የሚለዉን ጥያቄ ለመመለስ እሞክራለሁ፡፡ ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነዉ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ.14285 በመጋቢት 15 1997 የሰጠዉ ዉሳኔ ነዉ፡፡

ጉዳዩ የተጀመረዉ የኪራይ ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በአንድ ግለሰብ ላይ በመሰረተዉ ክስ ዉዝፍ የቤት ኪራይ ባለመክፈላቸዉ እንዲከፍሉ ይወሰንልኝ በማለት ነዉ፡፡ ግለሰቡም ዉሉ ላይ የኪራይ ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ሃላፊ ሆነ እራሱ አልፈረሙበትም፤፤ ኪራይ ክፈልበት በተባልኩበት ቤት ዉስጥም አልኖርኩም፤ የተከራየዉ ሌላ ቤት ሲሆን በዚያም የሚጠበቅበትን ክፍያ እንደፈጸመ በመግለጽ ተከራክሯል፡፡ 

የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት

የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በዉሳኔዉ ኪቤአድ የመንግስት መስሪያ ቤት ነዉ፡፡ በፍ/ብ/ሕ/ቁ. 1724 መሰረት ደግሞ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ዉል በጽሁፍ መሆን አለበት፡፡ በፍ/ብ/ሕ/ቁ. 1727(1) እና (2) መሰረት ደግሞ በጽሁፍ የሚደረገዉ ዉል በሁለት ምስክሮች መረጋገጥ አለበት፤ ይህ ካልሆነ ዉሉ አይጸናም፡፡ ለጉዳዩ መነሻ የሆነዉ ዉል በሁለት ምስክሮች ያልተረጋገጠ በመሆኑ አይጸናም በሚል ወስኗል፡፡ ይህም ዉሳኔ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመጽናቱ የሰበር አቤቱታ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ቀርቧል፡፡

Continue reading
  10050 Hits

ተጨማሪ ማስታወሻ፡‘መንግስት ወይም ለሕዝብ አገልግሎት የቆመ መስሪያ ቤት ላይ’ ግዴታ የሚጥሉ ዉሎች በምን አይነት ቅርጽ መሆን አለባቸዉ?

ሰበር ችሎቱ በመዝገብ ቁጥር 11270 የሚቀራረብ ጭብጥ አጋጥሞት ነበር፡፡ በዚህ መዝገብ የሚሟገቱት የትምህርት መሳሪያዎች ማምረቻና ማከፋፈያ ድርጅት እና አንድ የቀድሞ ሰራተኛዉ ናቸዉ፡፡ ጥያቄዉ ጉዳዩ በአዋጅ ቁጥር 42/83 ይሸፈናል ወይ የሚል ነበር፡፡ ይህን የተመለከተዉ ሰበር ችሎቱ በመጋቢት 23 ቀን 1997 በሰጠዉ ዉሳኔ እንዲህ ብሏል፡፡

ለዚህ ጉዳይ አግባብነት ያለዉና የአመልካች መስሪያ ቤትን ያቋቋመዉ አዋጅ ቁ.266/76 በአንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 1 ላይ መስሪያ ቤቱ የመንግስት መስሪያ ቤት እንደሆነ ደንግጓል፡፡ ይህም ማለት በመርህ ደረጃ አመልካች መስሪያ ቤት አስተዳደራዊ ስራዎችን የሚሰራ ሆኖ በአጋጣሚ ግን ከምርት ዉጤቶቹና ከአገልግሎት ዋጋ ገቢ ያገኛል፡፡ የመስሪያ ቤቱን በጀትም የተመለከትን እንደሆነ በአብዛኛዉ ከመንግስት ከሚሰጥ አመታዊ ድጋፍ እንደሚገኝ የማቋቋሚያዉ አዋጅ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 1 ይገልጻል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ መስሪያ ቤት በትምህርት ሚኒስቴር ስር ሆኖ በመቋቋሙ አስተዳደራዊ ስራዎችን ከመስራት በቀር በትርፍ ስራ ላይ ሊሰማራ እንደማይችል እንረዳለን፡፡ በመጨረሻም በአንቀጽ 9 ንኡስ ቁጥር 2/ሀ/ ላይ እንደተመለከተዉ መስሪያ ቤቱ ሰራተኞችን የሚቀጥረዉ፤ የሚያስተዳደረዉም ሆነ የሚያባርረዉ በመንግስት ሰራተኞች ሕግ ነዉ፡፡

በአጠቃላይ መስሪያ ቤቱ ተጠሪ በተሰናበተበት ጊዜ በዋናነት አስተዳደራዊ ስራዎችን የሚሰራ በመሆኑ እና በጀቱንም በዋናነት ለመንግስት በየአመቱ የሚያገኝ በመሆኑ አመልካች መስሪያ ቤት በአዋጅ ቁ.42/85 የሚሸፈን አልነበረም፡፡

በመሆኑም ይህ ችሎት በአመልካች እና በተጠሪ መካከል ያለዉን ግንኙነት የሚገዛዉ አዋጅ ቁ.42/85 አይደለም ሲል ወስኗል፡፡ በዚህም አቤቱታ የቀረበባቸዉን የስር ፍ/ቤቶች ዉሳኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁ.348(1) መሰረት ሽሮታል፡፡

የትምህርት መሳሪያዎች ማምረቻና ማከፋፈያ ድርጅት በኋላ ላይ እንደ ልማት ድርጅት መልሶ ተደራጅቷል፡፡ በፊት ግን የራሱ የሕግ ሰዉነት ያለዉ ድርጅት ሲሆን የሚተዳደረዉ በትምህርት ሚኒስቴር ስር ሲሆን እንቅስቃሴዎቹን በየአመቱ በሚወሰን በጀት ይሸፍናል፡፡ ሰበር ችሎቱም ድርጀቱ በትምህርት ሚኒስቴር ስር የሚተዳደርና በአመታዊ በጀት የሚደገፍና ምንም እንኳ ገቢ ቢያመጣም የአስተዳደር ስራ የሚሰራ መስሪያ ቤት በሚል ወስኗል፡፡

Continue reading
  9716 Hits

Corona Virus and Force Majeure

A post on American Bar Association’s (ABA) website and a comment by a colleague prompted me to write this. Let me begin by posing a question: can a pandemic be considered as a force majeure? The importance of this post may be revealed later as the economy opens up and creditors require debtors to perform their obligation, repudiate an agreement or hold debtors liable for failure.

 

Covid-19 is shaking the world- all 6 continents are being put to the test- who expected life to be like this some months ago? Covid-19’s impact goes far beyond the health system. It is having enormous amount of political and economic pressure on governments. The unavailability of vaccine, scientists’ lack of understanding of its real nature and the origin makes the virus dreadful. Though billions of dollars are poured to research, no pharmaceutical firm managed to come up with a long lasting solution except socially engineered solutions like social distancing, staying at home, cleaning hands, etc.

 

Obviously, the pandemic has a deep economic impact on start-ups and big firms. Many governments are devising stimulus package and/or these businesses are asking for a bailout. This means that the performance of many commercial agreements will be disrupted: debtors will keep getting emails, phone calls from creditors asking to deliver a thing, sell their service or whatever scenario which comes to your mind.

Continue reading
  5642 Hits

The Effect of the Coronavirus Pandemic on Contractual Obligations in Ethiopia

 

Introduction

The response of the Ethiopian federal government to the economic impact of COVID-19 on businesses has so far been to relax tax burden through Tax Relief Directive No. 64/2012. However, tax relief is beneficial only if a business makes income which currently is much harder as the pandemic is disrupting the performance of privet contracts. Businesses all over the country are experiencing reduced demand, late payments, depressed revenue and overall disruption in supply chine. Similarly, all members of the public with privet contracts i.e. employees, tenants, farmers, homeowners and others face the prospect of defaulting on their obligation. The government has so far refrained from interfering with the terms of contracts. One exception is the Federal Housing Corporation (FHC) in Addis Ababa which has announced a 50% reduction of housing rent due to the pandemic. On the contrary, other countries like Belgium have passed temporary measures to protect debtors affected by the pandemic from creditors by imposing a moratorium on creditors’ rights to enforce debts, terminate or dissolve existing contracts and initiate bankruptcy proceedings. 

This blog is not about the merits or demerits of any potential government actions in contracts, rather on the impact of COVID-19 on debtor-creditor relationships as per the preexisting law of Ethiopia and provided there is no contractual provision to deal with such issues. It especially focuses on excuses available for debtors to successfully navigate out of contracts made physically or commercially impossible by the pandemic.  

  1. Re-negotiation Vs litigation

There are many factors that can be considered to objectively measure and compare different paths to justice i.e. monetary costs, opportunity costs, and intangible costs. In general, monetary costs include items like lawyers’ fees, administrative or court fees, and bribes and other unofficial payments that are common in Ethiopia, opportunity costs refer to missed opportunities or lost income that results from the time and energy spent on one activity like litigation, and intangible costs refer to the negative effects on parties emotion, reputation, and ongoing business relationship.

Continue reading
  4812 Hits