‘መንግስት ወይም ለሕዝብ አገልግሎት የቆመ መስሪያ ቤት ላይ’ ግዴታ የሚጥሉ ዉሎች በምን አይነት ቅርጽ መሆን አለባቸዉ?

መግቢያ

የፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 1724 እንዲህ ይነበባል፤ መንግስት ወይም ለሕዝብ አገልግሎት የቆሙ መስሪያ ቤቶች ግዴታ የሚዋዋሉባቸዉ ዉሎች ሁሉ በጽሁፍና በሚገባ አኳኋን በፍርድ ቤት መዝገብ ወይም ባንድ ባስተዳደር ክፍል መስሪያ ቤት መዝገብ ወይም ዉል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠዉ ሰዉ ፊት መሰራት አለባቸዉ፡፡ እንግሊዘኛዉ ደግሞ እንዲህ ይነበባል፤ Any contract binding the Government or a public administration shall be in writing and registered with a court, public administration or notary. የኪራይ ቤቶች አስተዳደር ድርጅት የሚዋዋላቸዉ ዉሎች በዚህ የፍ/ብ/ሕ/ቁ.1724 የሚወድቁ ናቸዉ ወይ የሚለዉን ጥያቄ ለመመለስ እሞክራለሁ፡፡ ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነዉ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ.14285 በመጋቢት 15 1997 የሰጠዉ ዉሳኔ ነዉ፡፡

ጉዳዩ የተጀመረዉ የኪራይ ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በአንድ ግለሰብ ላይ በመሰረተዉ ክስ ዉዝፍ የቤት ኪራይ ባለመክፈላቸዉ እንዲከፍሉ ይወሰንልኝ በማለት ነዉ፡፡ ግለሰቡም ዉሉ ላይ የኪራይ ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ሃላፊ ሆነ እራሱ አልፈረሙበትም፤፤ ኪራይ ክፈልበት በተባልኩበት ቤት ዉስጥም አልኖርኩም፤ የተከራየዉ ሌላ ቤት ሲሆን በዚያም የሚጠበቅበትን ክፍያ እንደፈጸመ በመግለጽ ተከራክሯል፡፡ 

የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት

የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በዉሳኔዉ ኪቤአድ የመንግስት መስሪያ ቤት ነዉ፡፡ በፍ/ብ/ሕ/ቁ. 1724 መሰረት ደግሞ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ዉል በጽሁፍ መሆን አለበት፡፡ በፍ/ብ/ሕ/ቁ. 1727(1) እና (2) መሰረት ደግሞ በጽሁፍ የሚደረገዉ ዉል በሁለት ምስክሮች መረጋገጥ አለበት፤ ይህ ካልሆነ ዉሉ አይጸናም፡፡ ለጉዳዩ መነሻ የሆነዉ ዉል በሁለት ምስክሮች ያልተረጋገጠ በመሆኑ አይጸናም በሚል ወስኗል፡፡ ይህም ዉሳኔ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመጽናቱ የሰበር አቤቱታ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ቀርቧል፡፡

Continue reading
  10059 Hits

ተጨማሪ ማስታወሻ፡‘መንግስት ወይም ለሕዝብ አገልግሎት የቆመ መስሪያ ቤት ላይ’ ግዴታ የሚጥሉ ዉሎች በምን አይነት ቅርጽ መሆን አለባቸዉ?

ሰበር ችሎቱ በመዝገብ ቁጥር 11270 የሚቀራረብ ጭብጥ አጋጥሞት ነበር፡፡ በዚህ መዝገብ የሚሟገቱት የትምህርት መሳሪያዎች ማምረቻና ማከፋፈያ ድርጅት እና አንድ የቀድሞ ሰራተኛዉ ናቸዉ፡፡ ጥያቄዉ ጉዳዩ በአዋጅ ቁጥር 42/83 ይሸፈናል ወይ የሚል ነበር፡፡ ይህን የተመለከተዉ ሰበር ችሎቱ በመጋቢት 23 ቀን 1997 በሰጠዉ ዉሳኔ እንዲህ ብሏል፡፡

ለዚህ ጉዳይ አግባብነት ያለዉና የአመልካች መስሪያ ቤትን ያቋቋመዉ አዋጅ ቁ.266/76 በአንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 1 ላይ መስሪያ ቤቱ የመንግስት መስሪያ ቤት እንደሆነ ደንግጓል፡፡ ይህም ማለት በመርህ ደረጃ አመልካች መስሪያ ቤት አስተዳደራዊ ስራዎችን የሚሰራ ሆኖ በአጋጣሚ ግን ከምርት ዉጤቶቹና ከአገልግሎት ዋጋ ገቢ ያገኛል፡፡ የመስሪያ ቤቱን በጀትም የተመለከትን እንደሆነ በአብዛኛዉ ከመንግስት ከሚሰጥ አመታዊ ድጋፍ እንደሚገኝ የማቋቋሚያዉ አዋጅ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 1 ይገልጻል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ መስሪያ ቤት በትምህርት ሚኒስቴር ስር ሆኖ በመቋቋሙ አስተዳደራዊ ስራዎችን ከመስራት በቀር በትርፍ ስራ ላይ ሊሰማራ እንደማይችል እንረዳለን፡፡ በመጨረሻም በአንቀጽ 9 ንኡስ ቁጥር 2/ሀ/ ላይ እንደተመለከተዉ መስሪያ ቤቱ ሰራተኞችን የሚቀጥረዉ፤ የሚያስተዳደረዉም ሆነ የሚያባርረዉ በመንግስት ሰራተኞች ሕግ ነዉ፡፡

በአጠቃላይ መስሪያ ቤቱ ተጠሪ በተሰናበተበት ጊዜ በዋናነት አስተዳደራዊ ስራዎችን የሚሰራ በመሆኑ እና በጀቱንም በዋናነት ለመንግስት በየአመቱ የሚያገኝ በመሆኑ አመልካች መስሪያ ቤት በአዋጅ ቁ.42/85 የሚሸፈን አልነበረም፡፡

በመሆኑም ይህ ችሎት በአመልካች እና በተጠሪ መካከል ያለዉን ግንኙነት የሚገዛዉ አዋጅ ቁ.42/85 አይደለም ሲል ወስኗል፡፡ በዚህም አቤቱታ የቀረበባቸዉን የስር ፍ/ቤቶች ዉሳኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁ.348(1) መሰረት ሽሮታል፡፡

የትምህርት መሳሪያዎች ማምረቻና ማከፋፈያ ድርጅት በኋላ ላይ እንደ ልማት ድርጅት መልሶ ተደራጅቷል፡፡ በፊት ግን የራሱ የሕግ ሰዉነት ያለዉ ድርጅት ሲሆን የሚተዳደረዉ በትምህርት ሚኒስቴር ስር ሲሆን እንቅስቃሴዎቹን በየአመቱ በሚወሰን በጀት ይሸፍናል፡፡ ሰበር ችሎቱም ድርጀቱ በትምህርት ሚኒስቴር ስር የሚተዳደርና በአመታዊ በጀት የሚደገፍና ምንም እንኳ ገቢ ቢያመጣም የአስተዳደር ስራ የሚሰራ መስሪያ ቤት በሚል ወስኗል፡፡

Continue reading
  9759 Hits

Effect of Irregularities in Public Contract Awarding

 

 

 

Abstract

Continue reading
  7103 Hits