የማስረጃ ሕግ - ሕጉ እና አተገባበሩ

በሰዎች የእለት ከዕለት መስተጋብር ዉስጥ ከሚፈጠሩ ነገሮች መካከል አንዱ ቅራኔ ነዉ። ቅራኔ ሲኖር ደግሞ የመረጃ ወይም ማስረጃ ጉዳይ አብሮ ይነሳል። በተለይ ለዳኝነት አካላት ማለትም ለፍርድ ቤት፤ ለግልግል እና ለመሳሰሉት በሚቀርቡ ክርክሮች ላይ ማስረጃን ወይም መረጃን የሚመለከቱ ጉዳዮች መነሳታቸዉ አይቀሬ ናቸዉ። እዚህ ላይ የመረጃ እና ማስረጃን ልዩነት መረዳት ተገቢ ነዉ። ማስረጃ አንድን አከራካሪ ፍሬ ጉዳይ ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል የሚቀርብ ተጨባጭ ጉዳይ ሲሆን፤ መረጃ ግን አንድን ነገር ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል የሚሰጥ መግለጫ (Information) ብቻ ነዉ። ሁሉም ማስረጃ የመረጃነት ባህሪ ያለዉ ሲሆን፤ ሁሉም መረጃ ግን ማስረጃ አይደለም። ማስረጃ ለፍትሕ አካል የሚቀርብ መረጃ ሲሆን፤ ይህ መረጃም ፍሬ ነገርን የሚመለከት ነዉ። ፍሬ ነገር ማለትም በፍርድ ቤት ወይም በሌላ የዳኝነት አካል ፊት አከራካሪ ሆኖ የወጣ እና የተያዘ ጭብጥን የሚመለከት ነዉ። ማስረጃ የሚቀርበዉም ይህንን አከራካሪ ጭብጥ ወይም ፍሬ ነገር ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል ነዉ። የማስረጃ ሕግ ተፈጻሚነት የሚታየዉም በዚህ ጊዜ ነዉ።

  3896 Hits

በጽሑፍ የሰፈረን የውል ቃል የምስክርና ሌላ ዓይነት ማስረጃን በማቅረብ ማሻሻል ይቻላል?

የጉዳዩ መነሻ

ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ በመዝገብ ቁጥር 78398 በአቶ ሽፈራዉ ደጀኔ እና ወ/ሮ ጸሀይ ተስፋዬ በአንድ በኩልና በአቶ ሲሳይ አበቡ በሌላ በኩል በተደረገ ሙግት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ጥቅምት 19 2005 የሰጠዉ ዉሳኔ ነዉ፡፡ ጉዳዩ የተጀመረዉ በወረዳ ፍርድ ቤት በአቶ ሲሳይ አበቡ ከሳሽነትና በአቶ ሽፈራዉ ደጀኔ እና ወ/ሮ ጸሀይ ተስፋዬ ተከሳሽ ነዉ፡፡ ከሳሹ እንደሚለዉ በእሱና በተከሳሹ መካከል ሐምሌ 17 2003 የተቋቋመ የቤት ሽያጭ ዉል አለ፡፡

  20348 Hits