በሕገ መንግሥት ማሻሻያ አንቀጽ 39ኝን መቀየር ይቻል ይሆን?

ሕገ መንግሥት ማሻሻል ማለት ምን ማለት ነው

ሕገ መንግሥት ማሻሻል ማለት በአጭር አነጋገር ለሕገ መንግሥት ማስተካከያ የሚደረግበት ሂደት ነው ማለት ይቻላል፡፡ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ሂደት ክለሳ (Revision) አብዮት (Revolution) ማለት አይደለም፡፡ (ቃለአብ ታደሰ) አብዛኛው ጊዜ ማሻሻያ የሕገ መንግሥቱን ቃላት፣ ሃረግ፣ ዓ.ነገር ወይንም አንቀፆችን ሊያጠቃልል ይችላል፡፡ በእነዚህ በሚሻሻሉት ፋንታ በከፊል መጨመር፣ መቀነስ ወይንም ሙሉ በሙሉ መለወጥ ሊሆን ይችላል፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ ሁሉ ለውጦች ከሕገ መንግሥቱ አጠቃላይ አላማ፣ ግብና መንፈስ ጋር በሚጣጣም መልኩ መሆን አለበት፡፡ (ቃለአብ ታደሰ፡ 2011)

  7312 Hits

የክልሎች (የትግራይ ክልል) ምርጫ ሕገ-መንግሥታዊነትና ራስን በራስ የማስተዳደር ብሎም የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት

ለዚህ ጽሑፍ መነሻ የሆነኝ 6ተኛውን ሀገር አቀፍ ምርጫ የፌደራል መንግሥቱ ማራዘሙን ተከትሎ የትግራይ ክልላዊ ብሔራዊ መንግሥት ምርጫውን በክልሉ ለማካሔድ በመወሰን የምርጫ ቦርድ በማቋቋም ምርጫውን ለማድረግ አስፈላጊ ናቸው ያላቸውን ዝግጅት በማድረጉ ሲሆን የትግራይ ክልል መንግሥት ምርጫውን ማድረግ ይችላል አይችልም? ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቁጥጥር ውጭ የሆነና ራሱን የቻለ ምርጫ ቦርድ ማቋቋም ይችላል አይችልም? ምርጫውስ ከተካሄድ ሊኖረው የሚችለው ውጤት ምን ድን ነው? የሚሉትንና ተያያዥነት ያላቸውን ጥያቄዎች ለመመለስ እንዲሁም የትግራይ ክልል ምርጫውን ማድረግ መቻሉ ጋር የምርጫውን በክልል ደረጃ መደረጉን የሚደግፉ ፖለቲከኞችና አስተያየት ሰጭዎች ራስን በራስ ከማስተዳደርና የራስን እድል በራስ ከመወሰን ሕገ መንግሥታዊ መብት ጋር ስለሚያያይዙት ከነዚህ መብቶች ጋር ምርጫ ማድረግ እንዴት ሊታይ ይገባል? የሚለውን ከፌደራሉ ሕገ መንግሥት እና ከምርጫ አዋጆች (አ/ቁ. 1133/2011 እና አ/ቁ. 1162/2011) አኳያ ለማብራራትና ሃሳብ ለማቅረብ በሚል የተዘጋጅ አጭር ጽሑፍ (Article) ነው፡፡ በዚህ ጽሑፍ ላይ ማንኛውም አስተያየት ሰጭ ለሚሰጠው አስተያየት ጸሐፊው ለማስተናገድና ሃሳብ ለመለዋወጥ ዝግጁ መሆኔን ከወዲሁ ማሳወቅ እፈልጋለሁ፡፡ መልካም ንባብ፡፡

  7366 Hits

በፌዴሬሽን እና በትግራይ ክልላዊ መንግሥት ም/ቤቶች የተሰጡ ውሳኔዎች ሕገ-መንግሥታዊነት

በዓለማችን እና በሀገራችን የተከሰተውን የኮቪድ-19 ኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ተከትሎ በሀገራችን የፌደራል መንግሥትና የትግራይ ክልላዊ መንግሥት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጆች መታወጃቸው ተከትሎ የሀገራዊ ምርጫን መራዘምና ክልላዊ ምርጫ በትግራይ መከናወኑን ከሕገ-መንግሥቱ ድንጋጌዎች አኳያ እንደሚከተለው አስቀምጣለሁ፡፡

  6734 Hits

አንዳንድ ጉዳዮች ስለ ሕገ-መንግሥት እና ፍርድ (ትርጉም)

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የስራ ዘመን ከማለቁ በፊት ምርጫን ማከናወን እንደማይችል፤ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ካሳወቀ ጊዜ ጀምሮ፤ የጉዳዩ ሕገ መንግሥታዊ ገፅታዎች በተለያዩ መድረኮች ውይይት እየተደረገባቸው ነው። አራት አማራጭ መፍትሄዎች የቀረቡለት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ በጉዳዩ ላይ የሕገ መንግሥት ትርጉም፤ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት ጠይቋል። የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ፤ ጥያቄውን ተቀብሎ፤ የሕገ መንግሥት ምሁሮች አስተያየታቸውን በፅሁፍ እንዲያቀርቡ ጋብዟል። በቃልም እንዲያስረዱና ጥያቄዎችን እንዲያቀርቡ ጋብዟል።

  11260 Hits

የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ሕገ-መንግሥት መተርጎም ላይ ያለው ሚና እና በጉባዔው አዋጅ ላይ የተደረገ አጭር ምልከታ

ሁሉም ሕጎች በራሳቸው ምሉዕ አይደሉም፡፡ በመሆኑም ሕጎችን በተገቢው የአተረጓጎም ሥርዓት መሠረት ተርጉሞ ሥራ ላይ ማዋል ያስፈልጋል፡፡ በተለይ ደግሞ አጠቃላይ መርሆዎችን የደነገጉ ሕጎችን የያዙ እንደ ሕገ-መንግሥት ዓይነት ሕጎች በከፍተኛ ጥንቃቄ መሠረታዊ የአተረጓጎም መርሆዎችን በተከተለ ሁኔታ ፍጹም ገለልተኛና ብዘሀኑን በሚወክል ብቃት ባለው ሕገ-መንግሥት ተርጓሚ ሊተረጎም ይገባዋል፡፡ ይህም በመሆኑ ብዙ ሐገራት ሕገ-መንግሥት የሚተረጉም ራሱን የቻለ ተቋማትን አቋቁመዋል፡፡

  8967 Hits

‘ኮማንድ ፖስት’ ለአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተሰጠ ልዋጭ ስም?

በሀገራችን ኢትዮጵያ የፀጥታ ችግር በተለያዩ ጊዜያትና ቦታዎች ሲከሰት መንግሥት በሕግ የተቀመጠለትን መደበኛውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመጠቀም ፈንታ በስም የተለየ ነገር ግን በአተገባበር ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር ተመሳሳይነት ያለውን የሕግ ማስከበር መንገድ ‘ኮማንድ ፖስት’ በሚል ስያሜ እያዘወተረ እየተጠቀመ ይገኛል፡፡ ከዚህም በመነሳት ህብረተሰቡም ይህንኑ ኮማንድ ፖስት የተባለውን ስያሜ እኩል ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር አገናኝቶ ሲጠቀም ይስተዋላል፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት ኮማንድ ፖስት መንግሥት በመደበኛ የሕግ ማስከበር መንገድ ሕግን ማስከበር ሲቸገር እየተጠቀመው የሚገኝና በተግባርም የግለሰቦችን መብት የሚገድቡ ክልከላዎችን ጭምር በማውጣት በተግባር ተጠያቂ እያደረገ በመስተዋሉ ነው፡፡ ብዙን ጊዜ ይህንን አዋጅ ሲያውጅ የሚስተዋለው በፌደራል ደረጃ የተዋቀረ ‘ብሔራዊ የፀጥታ ም/ቤት’ የሚባል አካል እነደሆነ ይደመጣል፡፡ ይህ አካል አዋጁን ያውጅ ዘንድ በሕገ-መንግሥቱ ሥልጣን የተሰጠው አካል እንዳይደለ መረዳትም ይቻላል፡፡

  10943 Hits

የመፈንቅለ መንግሥት ጽንሰ ሃሳብ እና መገለጫዎች

መፈንቅለ መንግሥት ከጥንታዊ የሥልጣኔ ባለቤት ሃገራት ጀምሮ በታሪክ የሚታወቅ ሕዝብን እየመራ ባለ የመንግሥት ወይም የገዢ አካል ላይ የሚደረግ ከሥልጣን የማዉረድ ሁኔታ ሲሆን የበርካታ ሃገራት የታሪክ አካልም ነዉ፡፡ ለዚህ ጽሑፍ ዋነኛ መነሻ የሆነዉ የመፈንቅለ መንግሥት ጽንሰ ሃሳብ እና ትርጓሜዉ በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ የሚሰጠዉ ትንታኔ ከምን አንጻር የታየ እንደሆነ በዉል ባይታወቅም አብዛኞቹ ይህን መሰል ድረጊቶች መፈንቅለ መንግሥት ነዉ የሚል ስያሜ ሲሰጣቸዉ እንመለከታልን፡፡

  6966 Hits

የኢፌድሪ ሕገ-መንግሥትን በሕገ-መንግሥታዊ መንገድ ለማሻሻል ብቸኛው መንገድ፡- የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ተግባራዊ ማድረግ

ሕገ መንግሥት በባሕርይው ጠቅላላ ድንጋጌዎችን የሚይዝ በመሆኑ፤ ሕገ መንግሥትን ከተለዋወጭ የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ እና ማኅበራዊ ሁኔታዎች ጋር ለመጣጣም እና ዘላቂነት ኖሮት ገዚ ሆኖ እንዲኖር ያስችል ዘንድ ማሻሻልን ይጠይቃል፡፡ ለዚህም ሲባል የተፃፉ ሕገ-መንግሥት ያላቸው ሀገራት በሕገ መንግሥታቸው ውስጥ ማሻሻያ ሥርዓቶችን ወይም ማስተካከያ የሚደረግበት ሂደት የሚደነግጉ አንቀጾችን አካተው ይይዛሉ፡፡ በ1987 ዓ.ም የወጣው የኢፌድሪ ሕገ መንግሥትም እንዴት እንደሚሻሻል የማሻሻያ ሥርዓቶቹን በአንቀጽ 104 እና 105 ስር ተደነግጎ ቢገኝም እስካሁን ድረስ ሥርዓቶቹን ተከትሎ ማሻሻያ ሳይደረግበት ቆይቷል።  

  5607 Hits

ንብረት የማፍራት እና ፍትሐዊ ዳኝነት የማግኘት መብት: ከወቅታዊው የሕገ-ወጥ መሬትና ንብረት ማስመለስና ማፍረስ ጋር በተያያዘ

አሁን አሁን በተለያዩ የሃገራችን ክልሎች በተለይ ደግሞ በአዲስ አበባ ዙርያ በሚገኙ የኦሮሚያ ልዩ ከተሞች ላይ ከዕለት ወደዕለት በዜጎች የመዘዋወር መብት፤ንብረት የማፍራት፤ የእኩልነት እና ፍትህ የማግኘት ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በሕግ ማስከበር ሰበብ ሲጣሱ ማዬት የዕለት ተዕለት ተግባራዊ ኩነት እየሆነ መጥቷል፡፡

  13994 Hits
Tags:

በክልል የተገደበው የመዘዋወር ነፃነት

1. የመዘዋወር ነፃነት አለም አቀፋዊ አንድምታው

የሰው ልጅ ሰው ሆኖ በመፈጠሩ ከሚያገኛቸው አያሌ የተፈጥሮ መብቶች ውስጥ ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነት በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡ የሰው ልጆችን ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነት ከሐይማኖት፤ ከባህል እና ከሌሎች የተፈጥሮ ህግጋት ጀምርን ስንመለከተው ፅኑ መሰረት ያለው ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ በአለማችን ታሪክ ይህ ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብት በአንዳንድ የታሪክ አጋጣሚዎች ላይ ተገድቦ የነበረ ቢሆንም በአብዛኛው ግን ሰዎች ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብታቸው ሲከበር ቆይቷል፡፡ ይሄንን ተፈጥሮአዊ መብት በመጠቀም የተለያዩ የአውሮፓ ሰዎች አዲስ ግኝትን፤ የመካከለኛውና የሩቅ ምስራቅ ሀገሮች ደግሞ ንግድን በማጧጧፍ ለሀገራቸው እና ለአህጉራቸው ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አበርክተዋል፡፡ ይህንን ጥቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት እንደ ማግና ካርታ (Magna Carta) አይነት ጥንታዊ ሰነዶች ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብትን አውጀዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በታላቋ ሮም የነገሱ አብዛኛው ነገስታት ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነትን ሲያከብሩ መቆየታቸውን የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡

  11563 Hits