የወንጀልና ቅጣት ግሽበት፤ ቅጣት እንደ እንቁ እና ሌሎች ጉዳዮች ከወንጀል ኤኮኖሚክስ አንጻር ክፍል አንድ

 

ጠቅላላ

የዚህ ጽሑፍ ርዕስ ምንም እንኳ የወንጀል ኤኮኖሚክስ ቢልም፤ እንዲሁም ይህ ጽሑፍ የተጠቀመባቸው የጥናትና ምሁራዊ ጽሑፎች የኖቤል ሎሬት ጌሪ ቤከር የጀመረውና በሌሎች ምሁራን የዳበረው የጥናት ክፍል የወንጀል ኤኮኖሚክስ በመባል ቢጠራም፤ በጽሑፉ የሚነሱት ዋና ዋና ነጥቦች በአጠቃላይ በቅጣት ለማስፈጸም የሚሞከርን ሕግን ይመለከታል፡፡ በመሆኑም ወንጀል ባይሆንም በአስተዳደራዊም ሆነ በሌላ ዓይነት ቅጣት የሚፈጸም ሕግን በዚህ የጥናት ዘርፍ በዳበሩ አስተሳሰቦች አንጸር መገምገም እንችላለን፡፡

ግለሰቦች ሕግን ለማክበርና ላለማክበር ሲወስኑ ብዙ ነገሮችን ግምት ውስጥ ያስገባሉ፡፡ (ይህ አስተሳሰብ ግለሰቦች ሕግን ሲጥሱ አስበውበት ነው ከሚል ይነሳል፡፡ በእርግጥ በደመነፍስ ወይም ያለእውቀት የሚፈጸም የሕግ ጥሰቶች አሉ፡፡) እንደ ኤኮኖሚክስ ባለሙያዎች አባባል፤ ሕጉን በመጣስ የሚገኘው ጥቅም ሕጉን በመጣስ ከሚያስከትለው ቅጣት ካነሰ ግለሰቦች ሕጉን ያከብራሉ፡፡ የሚያስከትለው ቅጣት የተባለው በሕጉ ላይ የተቀመጠው ቅጣት አይደለም፡፡ ይልቅስ ዜጎች የሚያወዳድሩት በሕጉ ላይ የተቀመጠው ቅጣት ሲባዛ በመያዝና በመቀጣት እድል ነው፡፡ ትክክለኛው ቀመር ይህ ነው፤

ሕግ በመጣስ የሚገኘው ጥቅም    (በሕጉ የተቀመጠው ቅጣት X የመያዝና የመቀጣት እድል X ዲስካውንት ፋክተር) + ሕጉን ለመጣስ የሚወጣው ወጪ + (ኢመደበኛ ቅጣት X የመያዝና የመቀጣት እድል X ዲስካውንት ፋክተር)

Continue reading
  15203 Hits

ወይኖን ግረፈው ኳሊ እንዲሰማህ፤ የወንጀል ኢኮኖሚክስ ክፍል ሁለት

 

1.  የመያዝና የመቀጣት እድል፤ ማጅራት መቺዎችን እና ቤት ሰርሳሪዎችን ከተማን በማጽዳት እንዋጋቸው ወይኖን ግረፈው ኳሊ እንዲሰማህ እና ሌሎችም አሳቦች

1.1 አጠቃላይ

ማስታወሻ ለአንባቢ፤ ይህ በወንጀል ኤኮኖሚክስ ዙሪያ የጻፍኩት ሁለተኛው ጽሑፌ ነው፡፡ የመጀመሪያውን ክፍል እዚህ ማግኘት ይቻላሉ:: አሳቦቼን ለማስረዳት ስል አንዳንዴ ተጓዳኝ ጉዳዮችን እያነሳው ባወራም፤ የዋናው ሃሳብ ፍሰት አይዛባም የሚል ዕምነት አለኝ፡፡

በመጀመሪያው የጽሑፉ ክፍል የተቀመጠው ቀመር ሌላኛው አካል የመያዝና የመቀጣት እድልን መጨመር ነው፡፡ ለማስታወስ ያህል ቀመሩ ይህ ነው፤

Continue reading
  13330 Hits

ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት መስጠት (የግዴታ ሥራ) እንደ ወንጀል ቅጣት

 

ጣልያንን ለዘጠኝ ዓመታት የመሩት የቀድሞው የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የኤሲ ሚላን እግር ኳስ ክለብ ፕሬዚዳንትና ባለቤት እንዲሁም ቢሊየነሩ ሲልቪዮ ቤርሎስኮኒ በተከሰሱበት የታክስ ማጭበርበር ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው በሚላን ከተማ የሚገኘው ፍርድ ቤት ቤርሎስኮኒ የአራት ዓመታት እስራት ቢፈረድባቸውም የእስራት ቅጣቱ በተለያዩ ምክንያቶች ቀርቶ በተቃራኒው ቤርሎስኮኒ በአረጋውያን ማቆያና መንከባከቢያ ማዕከል ውስጥ ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት እንዲሰጡ እ.ኤ.አ. በ2013 መወሰኑ ይታወቃል፡፡ በውሳኔው መሠረትም ቤርሎስኮኒ ሴሴኖ ከተማ ውስጥ በሚገኘውና ከ2000 በላይ በእድሜያቸው የገፉ፣ የአእምሮና የአካል ጉዳተኛ የሆኑ አረጋውያን በሚገኙበት ማዕከል ውስጥ ለአንድ ዓመት ያህል በሳምንት ለአራት ሠዓታት በማዕከሉ እየተገኙ አረጋውያኑን እንዲመግቡ፣ እንዲንከባከቡ፣ እንዲያንሸራሽሩ እንደ አጠቃላይም በማንኛውም መልኩ ከአረጋውያኑ ጎን እንዲሆኑ ተወስኖባቸው ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎቱን ፈፅመው አጠናቀዋል፡፡        

ታዋቂው አሜሪካዊ የሙዚቃ አቀንቃኝ ቦይ ጆርጅም በመኖሪያ ቤቱ የኮኬይን ዕፅ ይዞ መገኘትና በሀሰት የመኖሪያ ቤቴ ተዘርፏል በሚል ካቀረበው የሀሰት ጥቆማና ሪፖርት ጋር በተያያዘ እ.ኤ.አ. በ2006 በማንሀተን የወንጀል ችሎት ጥፋተኛ ከተባለ በኋላ የተወሰነበት ቅጣት ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት እንዲሰጥ ይኸውም በኒውዮርክ ከተማ ለአምስት ቀናት ያህል የከተማዋን መንገዶች እንዲያፀዳ ሲሆን ከኒውዮርክ ከተማ የፅዳት አገልግሎት ክፍል ጋር በመሆን የከተማዋን አውራ ጎዳናዎች ለአምስት ቀናት ያህል በማፅዳት ቅጣቱን ፈፅሟል፡፡

ሆላንዳዊው የእግር ኳስ ተጫዋች የነበረውና ለአያክስ አምስተርዳም፣ ኤሲ ሚላንና ባርሴሎና እግር ኳስ ክለቦች ተጫውቶ ያሳለፈው ፓትሪክ ክላይቨርትም የ19 ዓመት ወጣት በነበረበትና ለአያክስ አምስተርዳም እግር ኳስ ክለብ በሚጫወትበት ወቅት በአምስተርዳም ከተማ ከፍጥነት ወሰን በላይ መኪና ሲያሽረክር ባደረሰው የመኪና አደጋ የቲያትር ዳይሬክተር የነበሩ የ56 ዓመት ጎልማሳ ሕይወታቸው እንዲያልፍ በማድረጉ በፍርድ ቤት ጥፋተኛ ተብሎ ዕድሜው ገና 19 ዓመት የነበረና ተስፈኛ ስፖርተኛ መሆኑ ከግምት ገብቶ የተጣለበት የሶስት ወራት የእስራት ቅጣት በሁለት ዓመት የፈተና ጊዜ እንዲገደብ፣ ለ18 ወራት መኪና ከማሽከርከር እንዲታቀብ እና ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት እንዲሰጥ ተወስኖበታል፡፡ በሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎቱም ፓትሪክ ክላይቨርት ለ240 ሰዓታት ታዳጊ ሕፃናትን በእግር ኳስ ስፖርት እንዲያሰለጥንና ለሕፃናቱ መልካም አስተዳደግ አስተዋፅኦ እንዲያደርግ ተወስኖበት ቅጣቱን መፈፀሙም ይታወቃል፡፡ ከእነዚህ ሠዎች በተጨማሪ ሌሎች ሠዎችም ለፈፀሙት የወንጀል ድርጊት ቅጣት እንሆን ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት እንዲሰጡ ሲወሰንባቸው ይታያል፡፡     

ለመሆኑ የወንጀል አጥፊዎች ላይ የሚጣሉ ቅጣቶች ምን ዓይነት ናቸው? ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት መስጠት ወይም የግዴታ ስራ ምን ዓይነት ቅጣት ነው? ዓላማውስ ምንድን ነው? በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግስ ሽፋን ተስጥቶታል ወይ? ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት መስጠት ወይም የግዴታ ስራ የሚወሰነው ምን ምን ሁኔታዎች ሲሟሉ ነው? ስንት ዓይነት የግዴታ ስራዎች አሉ? ፍርድ ቤቶችስ የግዴታ ስራን አስመልክቶ በሕግ ተለይቶ የተሰጣቸው ሥልጣን ምንድን ነው? ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት መስጠት ወይም የግዴታ ስራን አስመልክቶ የሚስተዋሉ ችግሮችና መፍትሔዎቻቸው ምንድን ናቸው? የሚሉና ተያያዥ ነጥቦችን በዚህ ፅሁፍ በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡

Continue reading
  16126 Hits

ቅጥ አልባ ቅጣቶች በኢትዮጵያ ሕጎች    

             

መግቢያ

ከጥንት ጀምሮ እስከዛሬ ወንጀል የዚች ዓለም እውነት ነው፡፡ ቃኤል አቤል መግደሉ ከተሰማበት ይህን ጽሑፍ እርሶ እያነበቡ እስካሉት ቅፅበት ድረስ ወንጀል በሰው ልጆች ላይ በሰው ልጅ በራሱ ይፈፀማል፡፡ ይህ ከሰው ልጆች ታሪክ ጋር መሳ የሆነ ታሪክ ያለው ወንጀል ወደፊትም ማቆሚያ የሚኖረው አይመስልም፡፡ የሰው ልጅ ማድረግ የቻለው  ወንጀል የሚቀንስበትን አማራጭ መዘየድ እንጂ ወንጀል አልባ ዓለም መፍጠር አይደለም፡፡ ምናልባትም ወንጀል የመቀነስ ሙከራውም ተሳክቶ እንደሆነ እንጃ፡፡

ወጣም ወረደ ሁሉም ማህበረሰብ እንደ ማህበረሰቡ ታሪካዊና ማህበራዊ ዳራ ራሱን ከወንጀል ለመከላከል በዋናነት የዘየደው መላ ቅጣት ነው፡፡ የዚህ ጽሑፍ ማጠንጠኛም የወንጀል ቅጣት በኢትዮጵያ ሕግ ያለውን መልክ በመጠኑ ከጠቅላላ የቅጣት መርሆች አኳያ በመቃኘት በአሁኑ ሰዓት እርስ በእርሳቸው ተናባቢነት የሌላቸው በተመሳሳይ ጉዳይ የተለያየ ቅጣት የያዙ፣ ለቀላል ወንጀል ከባድ ቅጣት ለከባድ ወንጀል ቀላል ቅጣት የደነገጉ  በግብታዊነት እዚህም እዚያም ቅጣትን እንደ ተራ የመንገድ ጨቃ እያነሱ የሚለጥፉ ሕጎች ከወንጀል ጠቅላላ ዓላማና ግብ አኳያ በአጭሩ መፈተሸ ነው፡፡

የወንጀል ሕግ ዓላማ

Continue reading
  17833 Hits