በኮንስትራክሽን ውሎች አፈጻጸም ወቅት የመሀንዲሱ ሚና እና የጥቅም ግጭት

መግቢያ

እንደሚታወቀው በኮንስትራክሽን ውሎች አፈጻጸም ወቅት መሀንዲሱ የሚጫወተው ሚና እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡ አንዳንዴም መሀንዲሱ በውኑ የመሀንዲስ አድራጎት የማይመስሉ ተግባራትን ሲያከናውን ይሰተዋላል፡፡ ይህም ነገሩ አጀብ! ቢያሰኝም እውነታው ግን ከዚህ የራቀ አይደለም፡፡

እርግጥ ነው መሀንዲሱ ብዙ አልፎ አልፎም እርስ በእርሳቸው የሚጣረሱ ተግባራትን የሚያከናውንበት ጊዜ አለ፡፡ ለአብነት ያህልም፡-የግንባታው ዲዛይነር፣ የአሰሪው ወኪል (employer’s agent)፣ አማካሪ (supervisor)፣ የሥራ ርክክብ አረጋጋጭ (certifier)፣ ብሎም አንዳንዴ አራጊ ፈጣሪ ገላጋይ ዳኛ ወይም ከፊል አስታራቂ (adjudicator or quasi-arbitrator) ሊሆን ይችላል፡፡

በነገራችን ላይ የመሀንዲሱ ሚና ከላይ በጠቀስናቸው ተግባራት ላይ ብቻ የተወሰነ አይደለም፡፡ በግንባታ ውሉ አፈጻጸም ወቅት አስቀድሞ ለፕሮጀክቱ አፈጻጸም የሚሆኑ ሥራዎን በራሱ አነሻሽነት (proactive works) ወይም ፕሮጀክቱ ወደ ሥራ ከገባ በኋላ ለውሉ አፈጻጸም የሚሆኑ ተግባራት እና ሥራዎችን በአሰሪው ወይም ሥራ ተቋራጩ ትእዛዝ (reactive works) እንዲሁም በውሉ በግልጽ ተለይተው ባይሰጡትም ለፕሮጀክት አፈጻጸም አንድ መደበኛ መሀንዲስ ሊሰራቸው የሚችሉ ሥራወችን ሊያከናውን ይችላል፡፡

አንዳንዴም ባለሃብቶች የመገንባት ሃሳቡ ኑሯቸው ወደ ስራው ሊገቡ ሲሉ ዘርፈ ብዙ የቴክኒክ ችግሮች፣ የምርታማነት እና ንግድ ጉዳዮች እንዲሁም የሕግ መወሳሰብ ባለማወቃቸው ብሎም ከግምት ባለማስገባታቸው የተነሳ እክል ሊገጥማቸው ይችላል፡፡ በሲቪል ምህንድስናው ዘርፍም ይህንን የባለሃብቱን ሃሳብ እና ስጋት ወደ እውነት ለመተግበር አማካሪ መሀንዲሱ ወይም መሀንዲሱየተባለውን ጉዳይ ሊፈጽምለት ይችላል፡፡

ነገሩ እንዲህ ነው! መሀንዲሱም ሆነ አማካሪ መሀንዲሱ በውል የተጣለባቸውን ሥራወች ሲሰሩ ግልጽ የሆነ የጥቅም ግጭት (manifest conflict of interest) ሊከሰት ይችላል፡፡ እነዚህ የጥቅም ግጭቶችም በሥራው ላይ ከተፈጥሮ ሕግ እና ርትዕ(natural law and equity) አንጻር የፍትሃዊነት ጥያቄ ስለሚያስነሳ በጥልቀት እና በአንክሮ መታየት ያለበት ጉዳይ ነው፡፡

Continue reading
  17216 Hits

ድጋፍ የተሳነው እና እየተዘነጋ የመጣው የኮንስትራክሽን ውሎች አማራጭ የግጭት አፈታት

 “In business as in life, you don’t get what you deserve, you get what you negotiate.”

Dr.Chester L. Karrass

መግቢያ

ግጭት የሰው ልጅ ወደ ምድር ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ  የነበረ፣ ያለ እንዲሁም በእልት ተዕለት የማህበራዊ መስተጋብር ውስጥ ሊከሰት የሚችል አለመግባባት ወይም ልዩነት ነው፡፡ ይህም አለመግባባት በጊዜና በሚገባ ካልተፈታ፣ በማህበረሰብ ውስጥ ከፍተኛ ስጋትና አለመረጋጋት ሊፈጥር ይችላል፡፡ ይህንንም ተግዳሮት ለማስቀረት በማሰብ አብዛኛውን ጊዜ የመንግስት ባህላዊ ተግባር (traditional functions of government) በመባል የሚታወቀው ማለትም ቋሚ የሕግና ፍትሕ ሥርዓት በመገንባት ለሚነሱ ቁርሾዎች መላ ሊያገኙበት የሚችልበትን ሥርዓት መዘርጋት ነው፡፡ ይህም ሊሆን የሚችልበት አንዱ መንገድ መደበኛ ፍርድ ቤቶችን ወይም አማራጭ የግጭት መፍቻ መንገዶችን በየደረጃው በማቋቋምና ለሚነሱ ግጭቶች በጊዜ መፍትሄ በመስጠት ሊሆን ይችላል፡፡

በዓለምአቀፍም ሆነ በአገር ወስጥ የሕግ ሥርዓት አስተማማኝና በቂ የግጭት አፈታት ሥርዓት መኖር በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ይህም መሆኑ በህብረተሰቡ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ኑሮ ውስጥ ሰላምና መረጋጋት ከማምጣቱ ባሻገር ተጠባቂ የሕግ ሥርዓት (Predictable legal system) እንዲኖረን ያደርጋል፡፡

የግጭት አፈታት ሲባልም በግራ ቀኝ በኩል የሚመጣ ማነኛውም ግጭት ወይም አለመግባባት ለመፍታት የሚተገበር ሥነ-ስርዓት ሲሆን ይህም በመደበኛው የፍርድ ሂደት ወይም በአማራጭ የግጭት አፈታት (alternative dispute resolution) መንገድ ሊከናወን ይችላል፡፡

Continue reading
  13340 Hits

የኮንስትራክሽን ዋስትና ምንነትና በተግባር የሚስተዋሉ የሕግ ክፍተቶች - ክፍል 1

መግቢያ

ይህ ጹሑፍ በ6ኛው የኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ኢንቨስትመንት ፎረም ላይ “የኮንስትራክሽን ዋስትና ሕጎች እና የገንዘብ ተቋማት አሰራር” በሚል አውደ ጥናት ላይ ለውይይት የቀረበ ነው፡፡

ዋስትና በውል አፈጻጸም ወቅት እንደተጨማሪ ግዴታ የሚቆጠር በሕግ ፊት ሊጸና የሚችል (juridical act) ተግባር ነው፡፡ በአለፉት ጥቂት ዓመታት ብቻ በአለማችን ከኢኮኖሚያዊ እድገት ጋር ታያይዞ ዋስትና (security) የመጠቀም ልማድ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጧል፡፡

ሆኖም ግን እኤአ ከ2007 ዓ.ም በኋላ ከዓለም ኢኮኖሚ መዳከም ጋር ተያይዞ የዋስትና ጥቅም በአግባቡ የታየበት ብሎም አሰፈላጊነቱም ጭምር ጥያቄ ምልክት ውስጥ የገባበት ጊዜም አይዘነጋም፡፡

ዋስትና መልኩ ይለያይ እንጂ በተግባር አገልግሎት ላይ መዋል የጀመረው እእኤ ከ2750ዓ.ዓ ገደማ ጀምሮ ነበር፡፡ በወቅቱም ዋስትናው ጥሬ ገንዘብ እንደመያዣነት በማቅረብ ነበር፡፡ በተለይ ስለ ሰው ዋስትና (surety) ሕግጋት እና መርሆዎች በተመለከተ ጥናታዊ ሮማዊያን እኤአ በ150ዓ.ም ገደማ ያዘጋጁት ተጠቃሽ ነው፡፡ (ጄፈሪ በርተን፡2000፡9) ከዚያም የሦስተኛ ወገን ዋስትና ወደ ማቅረብ የተሄደበትም ጊዜ ነበር፡፡ ዘመናዊ የፋይናንስ ተቋማት ማደግን ተክትሎ በዋናነት ለዓለምአቀፍ የሽያጭ ግብይቶች ክሬዲ (letters of credit) እየተስፋፋ የመጣበትን ሁኔታ እናገኛልን፡፡

Continue reading
  16369 Hits

የኮንስትራክሽን ዋስትና ምንነትና በተግባር የሚስተዋሉ የሕግ ክፍተቶች - ክፍል 2

በክፍል 1 ላይ ጸሐፊው ስለ አጠቃላይ የዋስትና የሕግ ማዕቀፍ በአጭሩ ለማቅረብ ሞክሯል፡፡ በዚህ ክፍል ደግሞ ስለ ኮንስትራክሽን ዋስትና ምንነት፣ ዓይነቶች እንዲሁም በተግባር የሚታዩ ክፍተቶች ይዳስሳል፡፡

 

1. የኮንስትራክሽን ዋስትና (Construction security)

 

በኮንስትራክሽን ውል አፈጻጸም ወቅት በርካታ የዋስትና ዓይነቶች ሲተገበሩ ይታያል፡፡ ከቅድመ ግንባታ ጀምሮ በግንባታ ወቅት አንዳንዴም ከግንባታ በኋላ ለሚከሰቱ ችግሮች ዋስትና ጥቅም ላይ ሲውል ይሰተዋላል፡፡ በተለይም የህንጻ አሰሪዎች (Clients) ግንባታው በፈለጉት ጊዜና ዕቅድ መሰረት እንዲካናወንላቸው ካላቸው ጽኑ ፍላጎት የተነሳ ውሉ እንዲፈጸምላቸው አሰፈላጊ ከለላ እንዲኖራቸው ይሻሉ፡፡

በኢትዮጵያም አብዛኛው የኮንስትራክሽን ውሎች መንግስት አሰሪ በመሆን የሚቀርብባቸው ናቸው፡፡ ለማሳያ ያህል የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ግንባታ፣ የኢንዲስትሪ ፓርኮች ግንባታ፣ የባቡር ዝርጋታ፣ የመንገድ ግንባታዎች ወዘተ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ በተለምዶው የመንግስት ኪስ እርጥብ (solvent) ነው ቢባልም በውል አስተዳደር ወቅት በተለያዩ ምክንያቶች የክፍያ መዘግየት ይስተዋላል፡፡ በዚህ ጊዜም ሥራ ተቋራጩ ልክ እንደ አሰሪው ሁሉ ግዴታ አለተፈጸመልኝም ብሎ ጥያቄ ማቅረብ ይችላል፡፡ በመርህ ደረጃ አሰሪ ሆኖ የቀረበው የመንግስት መስሪያ ቤት ውል ባለመፈጸሙ ምክንያት ሥራ ተቋራጩ ውል አልተፈጸም በሚል መከራከሪያ ሊያቀርብ እንደማይችል ከፍትሐብሔር ሕጉ አንቀጽ 3177 ድንጋጌ እና ከተለመደው የላቲን አባባል፡- ‘Exceptio non adimpleti contractus’ (ግዴታ አለተፈጸመልኝምን እንደ መከራከሪያ አለማቅረብ) መረዳት ይቻላል፡፡

Continue reading
  20871 Hits