‘ኮማንድ ፖስት’ ለአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተሰጠ ልዋጭ ስም?

በሀገራችን ኢትዮጵያ የፀጥታ ችግር በተለያዩ ጊዜያትና ቦታዎች ሲከሰት መንግሥት በሕግ የተቀመጠለትን መደበኛውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመጠቀም ፈንታ በስም የተለየ ነገር ግን በአተገባበር ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር ተመሳሳይነት ያለውን የሕግ ማስከበር መንገድ ‘ኮማንድ ፖስት’ በሚል ስያሜ እያዘወተረ እየተጠቀመ ይገኛል፡፡ ከዚህም በመነሳት ህብረተሰቡም ይህንኑ ኮማንድ ፖስት የተባለውን ስያሜ እኩል ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር አገናኝቶ ሲጠቀም ይስተዋላል፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት ኮማንድ ፖስት መንግሥት በመደበኛ የሕግ ማስከበር መንገድ ሕግን ማስከበር ሲቸገር እየተጠቀመው የሚገኝና በተግባርም የግለሰቦችን መብት የሚገድቡ ክልከላዎችን ጭምር በማውጣት በተግባር ተጠያቂ እያደረገ በመስተዋሉ ነው፡፡ ብዙን ጊዜ ይህንን አዋጅ ሲያውጅ የሚስተዋለው በፌደራል ደረጃ የተዋቀረ ‘ብሔራዊ የፀጥታ ም/ቤት’ የሚባል አካል እነደሆነ ይደመጣል፡፡ ይህ አካል አዋጁን ያውጅ ዘንድ በሕገ-መንግሥቱ ሥልጣን የተሰጠው አካል እንዳይደለ መረዳትም ይቻላል፡፡

በሌላ በኩል እየተዘወተረ የመጣው የክልሎች የጸጥታ መደፍረስን ምክንያት በማድረግ ‘ኮማንድ ፖስት’ እያወጁ የግለሰቦችን መብት መገደብ በብዛት እየተስተዋለ የመጣ ሲሆን ይህ ስልጣን በህገ-መንግስቱ ለነርሱ ያልተሰጠ ሆኖ ሳለ ይኸው ‘ኮማንድ ፖስት’ የተባለው ሲያሜ ምቹ አጋጣሚ እንደፈጠረላቸው እንመለከታለን፡፡

በዚህ ጽሑፍ ስለአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምንነት፤ ለምን እንደሚታወጅ፤ ማን እንደሚያውጀው እና ሲታወጅም ይሁን ከታወጀ በኃላ አዋጁንና አፈፃፀሙን በሚመለከት ሊሟሉ የሚገባቸው ይዘታዊም ሆኑ ሥነ-ሥርዓታዊ የሕግ መጠይቆችን እንመለከታለን፡፡ ከዚሁ ጋር አያይዘንም ከላይ ያተትነው ኮማንድ ፖስት የተባለው አዋጅን ከመደበኛው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጽንሰ ሃሳብ ጋር አገናኝተን እንመለከትና በዚሁ ኢ-መደበኛ አዋጅ ያሉትን ችግሮች ነቅሰን በማውጣት መሆን አለበት የምንላቸውን መፍትሔዎች እናስቀምጣለን፡፡

መግቢያ

አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማለት መንግሥት በመደበኛ ሕግና የሕግ አስከባሪ አካላት ሕግን የማስከበር አቅሙ ጥያቄ ውስጥ ሲገባ የሚታወጅ የግለሰቦችን መብት የመገደቢያና የተፈጠረን ችግርን ለመፍታት የሚሰራበት የሕግ ስሪት መንገድ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ ምክንያት የሚሆኑ ጉዳዮች ምንጫቸው ተፈጥሮአዊ (ለምሳሌ፡- የመሬት መደርመስ /መንሸራተት/፤ ያልተጠበቀ ጎርፍ እና የህዘብን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ ተላላፊ በሽታዎች መከሰት ወይም ሰው ሰራሽ (ለምሳሌ፡- የውጭ ወረራ ሲያጋጥም፤ አመጽ፤ መፈንቅለ መንግሥትና የመሳሰሉት….) ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

Continue reading
  8502 Hits

የኢፌድሪ ሕገ-መንግሥትን በሕገ-መንግሥታዊ መንገድ ለማሻሻል ብቸኛው መንገድ፡- የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ተግባራዊ ማድረግ

 

 

1. መግቢያ

ሕገ መንግሥት በባሕርይው ጠቅላላ ድንጋጌዎችን የሚይዝ በመሆኑ፤ ሕገ መንግሥትን ከተለዋወጭ የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ እና ማኅበራዊ ሁኔታዎች ጋር ለመጣጣም እና ዘላቂነት ኖሮት ገዚ ሆኖ እንዲኖር ያስችል ዘንድ ማሻሻልን ይጠይቃል፡፡ ለዚህም ሲባል የተፃፉ ሕገ-መንግሥት ያላቸው ሀገራት በሕገ መንግሥታቸው ውስጥ ማሻሻያ ሥርዓቶችን ወይም ማስተካከያ የሚደረግበት ሂደት የሚደነግጉ አንቀጾችን አካተው ይይዛሉ፡፡ በ1987 ዓ.ም የወጣው የኢፌድሪ ሕገ መንግሥትም እንዴት እንደሚሻሻል የማሻሻያ ሥርዓቶቹን በአንቀጽ 104 እና 105 ስር ተደነግጎ ቢገኝም እስካሁን ድረስ ሥርዓቶቹን ተከትሎ ማሻሻያ ሳይደረግበት ቆይቷል።  

የኢትዮጵያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ደኤታ አቶ ሬድዋን ሁሴን ታህሳስ 9 2014 ዓ.ም ለቱርኩ አናዶል ኤጀንሲ በሰጡት ቃለ ምልልስ ላይ በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት ውስጥ ለረጅም ጊዜ ሲያጨቃጭቁ የቆዩ ጉዳዪች ላይ ምክክር ማድረግና ለሕዝበ ውሳኔ በማቅረብ ሕገ መንግሥቱን ማሻሻልን ጨምሮ ሁሉን አካታች ሀገራዊ የምምክር መድረክ ለማካሄድ መታቀዱን ተናግረዋል።  በተመሳሳይ መልኩ የሀገሪቷ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አብይ አህመድም የሕገ-መንግሥት ማሻሻያ አጀንዳ ላይ ምክክር እንደሚደረግ በቅርቡ መግለጻቸው ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረትም አገራዊ መግባባት ለመፍጠር ያስችላል ተብሎ የታመነበት የኢትዮጵያ አገራዊ ምክር ኮሚሽን መቋቋሚ አዋጅ በቅርቡ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መፅደቁ ይታወሳል፡፡ ነግር ግን የኢፌድሪ ሕገ-መንግሥት ማሻሻያ ሥርዓቶች እጅግ ውስብስና ጥብቅ (very stringent and rigid) ስለመሆናቸው የዘርፉ ምሁራን ያስረዳሉ፡፡

Continue reading
  3092 Hits

Derogation of the right to life and its Suspension during State of Emergency: Art 93 of FDRE Constitution

 

Introduction

Various international, regional and domestic laws imposes obligation on the state to respect and protect fundamental human right and freedom. Stated otherwise, government has the duty respect and protect fundamental rights of its subject. Protecting and respecting these fundamental rights of its subject is internationally and regionally recognized principle.

The same principle hold true in domestic law including our country Ethiopia. FDRE constitution under its art 13(1) provides that “All Federal and State legislative, executive and judicial organs at all levels shall have the responsibility and duty to respect and enforce the provisions of this Chapter”.  As per this provision, all organs of the government be it federal and regional are duty bound to respect and enforce the provisions concerning fundamental right including the right to life. Moreover, they are under the duty to ensure the observance of the constitution and the duty to obey. In this respect, art 9(2) FDRE constitution stipulate that “state that all citizens, organ of the state, political organization, other association, as well as their official have the duty to ensure the observance of this constitution and obey it.”

However, none of these human rights are absolute and without limitation. Thus, none of human right may be applauded without limitation and absolutely and hence, be restricted.

In accordance with international human rights law there are essentially two ways in which the State put aside this international obligation. In other word, there are exceptional circumstance in which state restrict fundamental rights of its citizen. These are limitation and. Derogations.

Thus, this piece examines the status of the right to life as far as derogation of human rights is concerned under FDRE constitution. In doing so, the distinction between limitation and derogation will be put. Some international and regional human right instruments will also be dealt with.

Continue reading
  33030 Hits

ጥቂት ስለአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የኢትዮጵያ መስፈርት ከአለምፍ ሕግ ጋር ሲቃኝ

 

ሀገሮች የዜጎቻቸውን የንብረት፣ የህይወት በአጠቃላይ የስብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን ለማስጠበቅና ለማረጋገጥ የተለያየ ሕጎችን ያወጣሉ፡፡ እነዚህም ሕጎች ከሕገ-መንግስቱ (የየሃገሩ የበላይ ህግ) ጨምሮ አዋጆችን፣ ደንቦችንና መመሪያዎችን ያካትታል፡፡ በእነዚህ ሕጎች የተደነገጉት መብቶችን ማራመድ አንዳንድ ጊዜ የሌላውን ሰው መብትና ደህንነት አደጋ ላይ ሊጥል ይችላል፡፡ በእንደዚህ ሁኔታ ላይ ሲሆን ሕግ እነዚህ መብቶች ላይ ገደብ (limitation) ያስቀምጣል፡፡ ይህ የመብት ገደብ ዘለቄታና በቋሚነት የሚፀና ነው፡፡ ለምሳሌ ያህል በሕገ- መንግስታችን አንቀፅ 29 ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ተደንግጓል ፡፡ ነገር ግን በተመሳሳይ አንቀፅ ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ወጣት ዜጎችን እና የሌሎች ሰዎች መብትና ክብር ለመጠበቅ ሲባል በህግ ሊገደብ እንደሚችል ተደንግጓል፡፡ ይህ የመብት ገደብ ሲሆን ተፈፃሚነቱም በዘለቄታዊነት ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የመብት ገደብ ነገሮች ተፈጥሮዊና በተለመደው ሥርዓት ላይ እያሉ የሚተገበር ነው፡፡

በአንፃሩ አንድ ሀገር የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ (state of emergence) የምታውጀው አንድን ክሰተት ባለው ነባርዊና በተለምዶ በተዘረጋው ሥርዓት መቆጣጣር ሳይቻል ሲቀር እንዲሁም የሀገሪቱን ህልውና የሚፈታተን አደጋ ሲያጋጥም ነው፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ሲያጋጥም በሕግ የተደነገጉ መብቶችን ሁሉ ተግባራዊ ላድርግ ማለት አዳጋች አንዳንዴም የማይቻል ሊሆን ይችላል ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ሰፊው የስብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ሊገደቡ ይችላሉ፡፡ ይህ የመብት ገደብ ከላይ ከጠቀስነው የመብት ገደብ የሚለየው ነገር ቢኖር በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ወቅት የመብት ገደብ ዘላቄታዊ ሳይሆን ጊዜያዊ ነው፡፡

የተለያዩ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ስምምነቶች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመደንገግ እና በዚህም የተነሳ መብቶች ሊገደብ እንደሚችሉ እውቅና ይሰጣሉ፡፡ እነዚህም ዓለም አቀፍ ስምምነቶች  ይህንን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመደንገግ መብት ሲሰጡ በተመሳሳይ መልኩ ምን ምን የሥነ-ሥርዓት (procedural requirements) እና የይዘት (substantive requirements) መስፍርቶችን መሟላት እንዳለባቸው ደንግገዋል፡፡

  1. የይዘት መስፈርቶች

ሀ. የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ  እጅግ አስፈላጊ መሆን አለበት (necessity test)

Continue reading
  10606 Hits

Making Extraordinary Power Part of the Ordinary Discourse? The Case of Ethiopian State of Emergency Declared on February 16

 

 

Introduction

In this piece, I will examine the legality of and intent induced the State of Emergency (SoE) declared on Feb. 16, 2018, in Ethiopia. Throughout, I will utilise legal and public choice analytical models. To do so, I will start by giving an overview of SoE as a general practice and under the 1995 FDRE constitution. I will then employ functional analysis to highlight the functions of SoE – mainly reassurance and existential rationales. Tied to the functional review, I will discuss the possibility of abuse of function and alternatives to control an abuse through ex-ante and ex-post monitoring mechanisms. In the fourth section, I will turn to the examination of a motive element that may induce declaration of SoE with a focus on benevolent intent and as a power-maximizing tool. Against these theoretical backdrops, under the fifth section I will diagnose the legality of and the rationale that induced the declaration of the current SoE. I would argue that SoE is an extraordinary power to be used in any but dire circumstances. The vaguer the condition for declaring an emergency and the weaker the check and balance of emergency process, the higher will be the risk of emergency power abuse. Further, its repeated reoccurrence sets a threat of normalization of SoE which is as much dangerous as the threat it is meant to mitigate.      

Continue reading
  12150 Hits