ሕግ መንግሥቱን በፖለሲ ማዕቀፍ ሥር?

ሰሞኑን በአንድ ካፌ ገብቼ የተደረደሩ ቀን ያለፈባቸው ጋዜጦች ስመለከት የሪፖርተር ጋዜጣ በሚያዚያ 1/2009 የእለተ-እሁድ እትሙ ላይ “ሰበር ሰሚ ችሎት  በክራውን ሆቴል የንግድ ምልክት ላይ የሰጠው የመጨረሻ ውሳኔ ሕገ መንግሥታዊ ትርጉም ያስፈልገዋል ተባለ” በሚል ርእስ ባወጣው ዘገባ ላይ ዐይኔ አረፈ። ከዚህ በፊት በርካታ ጉዳዮች ወደ ሕገ መንግሥት አጣሪ ጉባኤ ስለመቅረባቸው አውቃለሁ። በሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ላይ የሕገ መንግሥት ጉዳይ ክርክር ተነስቶበት ወደ ጉባኤው ስለመቅረቡ ሳነብ ግን የመጀመሪያዬ ነው።  ምናልባት እኔ ያላወቅኳዋቸው ተመሳሳይ ጉዳዮች ከዚህ በፊት ቀርበው ይሆናል። ያም ሆነ ይህ ርእሰ ጉዳዩ ቀልቤን ስለሳበው ባለጉዳዮቹ  ስለተከራከሩበት ጉዳይና የችሎቱ ውሰኔ  ለማወቅ ጉጉት አደረብኝ። እናም  ወደ ሕገ መንግሥት አጣሪ ጉባኤ ስለተወሰደው የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔና ስለክርክሩ ከሥሩ ለማየት ወሰንኩ። ስለሆነም የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ቅጂ ፈልጌ በመመልከት የሚከተለውን  የግል እስተያየቴን ለመጻፍ ውደድኩኝ።

ሕገ መንግሥታዊ ትርጉም ያስፈልገዋል የተባለው ውሳኔ ምንነት

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሰኔ የሰጠበት ጉዳይ በክራውን ሆቴል  ባለቤት (አመልካች) እና ሲክስ ኮንትኔታል ሆቴልስ (ተጠሪ) ከ2006 ዓ.ም ጀመሮ ከአእምሮ ንብረት ጽሕፈት እሰከ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ብሎም ወደ ሰበር ሰሚ ችሎት የቀረበ  ክርክር ነው። ይህ የመዝገብ ቁጥሩ 117013 የሆነውና ሰበር ሰሚ ችሎቱ በሰኔ 22 ቀን 2008 በዋለውና አምስት ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የተወሰነው ውሳኔ ከንግድ ምልክት ጥበቃ ጋር የተያየዘ ክርክር ነው። ወደ ሰበር ሰሚ ችሎት የቀረበው ጉዳይ ከንግድ ምልክት ምዝገባ  ተቃውሞ ጋር በተያየዘ የክራውን ሆቴል ባለቤት በአእምሮ ጽሕፈት ቤት ውሰኔ ቅር ተሰኝተው ለከፈተኛ ፍርድ ቤት ይገባኝ ያሉበት ጉዳይ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የእእምሮ ጽሕፈት ቤት ውሳኔውን ስለኣጸና የፍርድ ቤቱ ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ ይታረምልኝ በማለት ሲሆን፤ ሰበር ሰሚ ችሎቱም ጉዳዩን ከስር መሰረቱ በመፈተሽ መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት ብሎ ለአመልካች ወስኗል። 

ጉዳዩ ከመሰረቱ ሲታይ በወርሃ ነሃሴ 2005 “CROWNE PLAZA” በሚል በተጠሪ በኩል  በቀረበው የንግድ ምልክት ምዝገባ ጥያቄ ላይ ተቃውሞ ካለ በቀረበው የጋዜጣ ጥሪ መሠረት አመልካች (CROWN HOTEL) በቃልና በጽሁፍ በተደጋጋሚ ተቃውሞ ያቀርባሉ። ለተቃውሞ ምክንያት የሆነው በሕግ ጠበቃ ያገኘውን የንግድ ምልክት የቀዳሚነት መብቴን ይጥሳል የሚል ነው። ተቃውሞው የተመሠረተው በአዋጅ 501/ 2005 አንቀጽ 6 እና  አንቀጽ 7 መሠረት ሲሆን በተለይም በአንቀጽ 7(1) “ከአንድ ዓይነት ወይም ተመሳሳይ እቃዎች ወይም አግልግሎቶች  ጋር የተያያዘ  የሌላ ሰው ቀዳሚ የንግድ ምልክት ጋር አንድ ዓይነት ወይም መሳከርን ሊያስከትል ተመሳሳይነት ያለው”  ሲሆን ለምዝጋባ በቁ አይደለም ብሎ በሚደነግገው መሠረት እንዲሁም በተጨማሪም በንግድ ምዝጋባ አዋጅ 686/2002 አንቀጽ 24 (3) (ሀ) መሠረት የንግድ መዝጋቢው አካል “ቀደም ሲል ከተመዘገቡት የንግድ ስሞች ጋር አንድ ዓይነት ወይም ተመሳሳይና አሳሳች አለመሆን  24 (3) (በ) መሠረት ደግሞ በንግድ ስም መዝገብ  በተመዘገበ የንግድ ስም ላይ ላይ ከፊቱ ወይም ከኋላው ቃላት በመጨመር ያልቀረበ መሆኑን በማረጋገጥ እንዲመዘገብ በሚደነግገው መሠረት ቀደም ሲል ተመዝግቦ ሥራ ላይ ካለው CROWN HOTEL+ logo ጋር ይመሳሰል። በዚህም በሕግ ጥበቃ ያገኘው መልካም ስሜና ዝናዬ ይነካል የሚል ነበር። እውነት ነው የእእመሮ ንብረት ጽሕፈት ቤት ትኩረት የንግድ ምልክቱ ወይም የፈጠራው ጉዳይ ላይ ሲሆን የንግድ መዝጋቢው አካል ደግሞ በንግድ ስሙ ላይ ያተኩራል። ቀዳሚነት ያለው የንግድ ምልክት “CROWN HOTEL” የሚል ሲሆን፤ አዲሱ የንግድ ምልክት “CROWNE PLAZA” የሚል ነው። የተጨመሩት ነገሮች በ CROWN ላይ” E”  እንዲሁም “PLAZA”  የሚለው ቃል ነው።  ሁሉቱም የሆቴል አግልግሎት ሰጪዎች መሆናቸው ልብ ይሏል። በክርከር ሂደቱ በርካታ ጭብጦት ለክርክር ቀርበው የነበረ ሲሆን የዚህ ጽሑፍ ዓላማ በክርክር ሂደቱ በጭብጥነት ተይዞ እስከ መጨረሻ በዘለቀው  ጭብጥ ላይ ብቻ  የሚያተኵር ይሆናል። 

በፍርድ ሃተታው እንደተመለከተው በአመልካች በኩል ለተቃውሞ መነሻ የሆኑት የሕግ መሰረቶች  የንግድ ምዝገባ አዋጅ እና የንግድ ምልክት ምዝጋባ አዎጅ ሲሆኑ  ጽሕፈት ቤቱ በመጀመሪያ  ተቃውሞውን  ከአዋጅ 501/ 1998 ጋር በማገናዘብ ተቀበሎ የምዝገባ ሂደቱን አቋረጦ የነበረ ቢሆንም ለሁለተኛ ጊዜ ውሳኔውን ሊቀለበሰው ችሏል። ውሳኔው ለአመልካች ከተነገረ በኋላ እንደገና ውሰኔውን በመቀየር የሚከተሉት ምክንያቶችን አቅርቧል። ጽሕፈት ቤቱ የንግድ ምልክቶቹ መመሳሰል ሳይክድ ኢንቨስትመነትን ለማበረታት ይጠቅማል በሚል ሁለቱም የንግድ ምልክቶች እንዲቀጥሉ ወስኗል። አክሎም ጽሕፈት ቤቱ ውሳኔው እንዳይደገም ራሱን አስጠንቅቆ ዘግቶታል። ይህም ውሰኔው ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት ካለው ፍላጎት ውጭ ተገቢ እንዳለሆን ያመነበት ይመስላል። ምክንያቱ ይህንን ውሳኔ ከሰጠ በኋላ ተመሳሰይ ውሳኔ እንዳይደገም በራሱ ላይ እግድ አስቀምጧል። እዚህ ላይ ሊነሳ የሚቸለው ጥያቄ ውሳኔው ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት እስከ ሆነ ድርስ የማይደገመበት ምክንያት ምንድ ነው? ከአዲሱ ድርጅት የተሻለ ኢንቨስትመነት ይዘው በተመሳሳይ  የንግድ ምልክት ለሚቀርቡ ባለሃብቶችስ ምን ዓይነት ምላሽ ሊስጥ ነው? ዜጎችን በእኩልና ፍታሃዊ መንገድ ሊያገልግል የቋቋመ ተቋም ልክ እንዳልሆነ አምኖ እንዳይደገም የሚለውን ውሳኔ እንዴት ሊወስን ይችላል? CRROWN HOTELS and Convention Center የሚል የንግድ ምልክት ይዞ ከቀደሙት ሁለቱ ሆቴሎች ይልቅ የተሻለ አቅም ያለው ባለሀብት ለምዝገባ ቢያመለክትስ? ወዘተ የሚሉ ጥያቄዎችን ማንሳት ይቻላል።

Continue reading
  12780 Hits

The Control of constitutionality of laws - (A comparative analysis between Ethiopia and Nigeria)

1.      Introduction

This essay examines the normative contemporary constitutional law question ‘how constitutionality of laws is controlled?’ under Ethiopian and Nigerian Federal Systems. In constitutional terms, both this question and federal systems require a written constitution that serve as a fundamental or basic law and placed hierarchically at the highest peak.

Federalism with written constitutions is one of the hallmarks of the Ethiopian and Nigerian political system. In both countries there are constitutionally entrenched distribution of powers between States and federal government to enact law, to execute and adjudicate as means of modern attempt to accommodate democratic complexity and pluralism. In exercising these constitutionally entrenched powers, the possibility of enacting inconsistent and ultra virus laws and hence, disputes regarding the constitutionality of laws is inevitable. The federal and state laws should be consistent not only with the terms and conditions of the federal constitution i.e. considered as a Basic Law but also should exist in harmony with each other. The settling of disputes concerning the constitutionality of laws is essential in federal systems and takes distinct form. Irrespective of its distinct form, the constitutionality of laws is one of the central problems of Constitutional Law that must be addressed in any federal states.

The objective of this essay is therefore; to compare how Ethiopia and Nigeria arrange the control of constitutionality of laws in their federal structure the aim of which is to guarantee and ensure the observance of hierarchy of legal norms and rule of law. In doing so, the essay is divided in to four sections. Section I explore the methods of controlling Unconstitutional Provisions and provide list of possible solutions for comparison. Section II demonstrates the general background and legal basis for application of control over unconstitutional provisions in Ethiopia and Nigeria. Section III compares the two countries method followed by conclusion under Section IV.  

 

Continue reading
  18090 Hits

የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ሕገ-መንግሥት መተርጎም ላይ ያለው ሚና እና በጉባዔው አዋጅ ላይ የተደረገ አጭር ምልከታ

 

መግቢያ

ሁሉም ሕጎች በራሳቸው ምሉዕ አይደሉም፡፡ በመሆኑም ሕጎችን በተገቢው የአተረጓጎም ሥርዓት መሠረት ተርጉሞ ሥራ ላይ ማዋል ያስፈልጋል፡፡ በተለይ ደግሞ አጠቃላይ መርሆዎችን የደነገጉ ሕጎችን የያዙ እንደ ሕገ-መንግሥት ዓይነት ሕጎች በከፍተኛ ጥንቃቄ መሠረታዊ የአተረጓጎም መርሆዎችን በተከተለ ሁኔታ ፍጹም ገለልተኛና ብዘሀኑን በሚወክል ብቃት ባለው ሕገ-መንግሥት ተርጓሚ ሊተረጎም ይገባዋል፡፡ ይህም በመሆኑ ብዙ ሐገራት ሕገ-መንግሥት የሚተረጉም ራሱን የቻለ ተቋማትን አቋቁመዋል፡፡

ሐገራችን ኢትዮጵያም እንደሌሎች ሐገራት የሕገ-መንገስት ትርጉም ጥያቄ ሲቀርብ ጉዳዩን ተቀብሎ ተገቢውን ውሳኔ የሚሰጡ ተቋማትን አቋቁማለች፡፡ የኢ.ፊ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግሥት የሕገ-መንግስታዊ ክርክር ጉዳይ ሲነሳ ጥያቄው እንዴት መልስ ያገኛል ለሚለው ድንጋጌ አስቀምጧል፡፡ በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 62 ላይ የፌደሬሽን ምክር ቤት ሕገ-መንግስቱን የመተርጎም ሥልጣን ይኖረዋል፡፡ የሕገ-መንግስታዊ ክርክር ጉዳይ ሲነሳ በፌደሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ ያገኛል በማለት ደንግጓል፡፡ የፌደሬሽን ምክር ቤቱም የሕገ-መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ በሚያቀርብለት ሕገ- መንግስታዊ ጉዳይ ላይ በሠላሳ ቀናት ውስጥ ውሳኔ ይሰጣል፡፡

የፌደሬሽን ምክር ቤት ሕገ-መንግስታዊ ትርጉም በሚሰጥበት ጊዜ ሞያዊ ዕገዛ የሚሰጠው የሕገ-መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ሥልጣንና ተግባር በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 84 ላይ ተዘርዝሮ ተቀምጧል፡፡

Continue reading
  6587 Hits

Constitutional Special Interest of the State of Oromia in Addis Ababa City Administration

INTRODUCTION        

The phraseology of special interest is technical employment. The geographical location, historical, socio economic underpinnings and legal grounds attract the attention of ONRS and Oromo people. These grounds inspire them to know about the City and special interest. The Constitutional Special Interest is not only ethical, political or legal issue but it also involves the identity of the People, indigenous people are the foundation. It is, therefore, a particularistic interest recognized and guaranteed, almost the same, when the Constitution comes into scene. It is particularistic because it is of a single state interest that it shares with no other constituent regional states.

Today, we do not watch concrete job being done to implement the interest and things are left in limbo.  After the enactment of the Constitution two Charters, Proclamation, (Proc.) No. 87/1997 and 361/2003, have been issued for the City. However, both of them have failed to state the relationship between ONRS and AACA along with the Constitution. Though both Charters empower the City government and Federal government to reach an agreement with the Region, this has not yet been materialized. For the people, therefore, the past decades have meant a major loss of control over special interest. They are the gate keepers, of success or failure to husband their interest.

CONCEPT OF STATE INTEREST

Even after decades of  talk  about  the political safeguards  of  federalism, there is  a lot we  do not know  about the  formal  even  informal  ways  in  which states’ interests  influence parliamentarian decision  making. What seems clear, however, is that there are avenues of influence, often very strong ones.

Continue reading
  29491 Hits