የውርስ ምንነት፣ የውርስ ዓይነቶች እና ወራሾችን ማጣራት በኢትዮጵያ የውርስ ሕግ

 

መግቢያ

የሰው ልጅ ወደዚች ምድር ከመጣበት /ከተወለደበት/ እለት አንስቶ እስከ ሕይወቱ ፍፃሜ ድረስ በዚች ምድር ላይ የሚኖረው ለተወሰነ ጊዜ ነው፡፡ የሰው ልጅ በዚች ምድር ላይ ዘላለማዊ አይደለም፡፡ ለያንዳንዱ ሰው በፈጣሪው የተጠው የምድር ቆይታ ጊዜ አለው፡፡ ይህ የምድር ላይ ቆይታው በአይቀሪው ሞት ይጠናቀቃል፡፡ የሰው ልጅ ወደዚች ምድር ከተቀላቀለበት እለት አንስቶ እስከ እለተ ሞቱ ድረስ የሕግ መብት አለው፡፡

በዚች ምድር ላይ በቆይታው ጊዜው የሰው ልጅ የተለያዩ መብቶች እና ግዴታወች አሉ፡፡ ለምሳሌ ያህል ንብረት የማፍራት መብት የሚጠቀስ ነው፡፡ በእለት ተእለት ኑሮው የተለያዩ ሥራዎችን እየሠራ የራሱን ብሎም የቤተሰቡን ጉርስ ለመሸፈን ጥረት ያደርጋል፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ የራሱ የሆነ ጥሪት ማፍራቱ አይቀሬ ነው፡፡ ይህን ጥሪት በምድር ላይ እስካለ ብቻ ነው የሚጠቀምበት፡፡ ሕይወቱ ካለፈች በኋላ ይህን ያፈራውን ንብረት በሕይወት ያሉ የሱ የቅርብ ሰዎች ናቸው የሚጠቀሙበት፡፡ እነዚህ በሕይወት ያሉ የሟችን ንብረት ሕይወቱ ካለፈ እለት በኋላ የሚጠቀሙበት በውርስ በመውረስ ነው፡፡ ውርስ የአንድ የሞተን ሰው ኃብትና ንብረት እንዲሁም ሊተላለፉ የሚችሉ መብትና ግዴታዎች ለአንድ ወይም ከአንድ በላይ ለሆኑ በሕይወት ላሉ ሰዎች የሚላለፋበት ሕጋዊ ሰርዓት ነው፡፡ ይህ ሰርዓት ደግሞ ሊያስከትል የሚችለው ሕጋዊ ውጤት ስለሚኖረው ራሱን የቻለ ሕግ ሊኖረው ይገባል፡፡

የሟችን ንብረት የሚወርሱት እንማንናቸው፣ ወራሽነትን የሚያሳጡ ነገሮች ምንድን ናቸው፣ ንብረቱ እንዴት ይከፋፈላል፣ ሟች ኑዛዜ ከተወ ኑዛዜው ሕጋዊ ውጤት እንዲኖረው ምን ምን መሟላት አለበት እና የመሳሰሉትን ነገሮች የሚመራው የሕግ ክፍል የወርስ ሕግ ይባላል፡፡ በዚህ ጽሑፍ የሃገራችን የውርስ መሠረታዊ ጉዳዩች እንቃኛለን፡፡

Continue reading
  58019 Hits

ስለ ኑዛዜ ከውርስ ሕግና ከሰበር ውሳኔዎች ጋር ተገናዝቦ የቀረበ

 

 መግቢያ

የኢትዮጵያ የውርስ ሕግ ኑዛዜ ማለት ምን ማለት እንደሆነ የሰጠው ትርጉም ባይኖርም አንድ ኑዛዜ ህጋዊ ውጤት እንዲኖረው ማሟላት የሚገባቸውን መስፈርቶች ምን ምን እንደሆኑ በዝርዝር የሚያስቀምጡ የሕግ ድንጋጌዎችን ከፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 857 እስከ 908 ተደንግጎ እናገኘዋለን፡፡

በዚህ ጽሁፍ ኑዛዜ በምን አግባብ ቢደረግ በሕግ ዘንድ ውጤት ይኖረዋል፤በውርስ ሕጋችን ላይ የተቀመጡት የኑዛዜ አደራረግ ስርዓቶች አስገዳጅነታቸው እስከምን ድርስ እንደሆነና ኑዛዜ በፍርድ ቤት ቢጸድቅ ሊያስገኝ የሚችለው ውጤትና ባለመጽደቁ የሚያመጣው ተጽእኖ ምን እንደሆነ ከውርስ ሕግ እና አስገጋጅ ከሆኑ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ውሳኔዎች አንጻር  በአጭሩ ዳሰሳ ለማድርግ ተሞክሯል፡፡ 

ለኑዛዜ ዋጋ መኖር አስፈላጊ የሆኑ የስረ ነገር ሁኔታዎች    

Continue reading
  6377 Hits