የሕግ ሙያ አገልግሎትን መቆጣጠር፣ የሕዝብ ጥቅም፣ የግለሰብ ፍላጎትና የውድድር ሕግ

በተለምዶ የሕግ ባለሙያዎች በንግዱ ዘርፍ ለሚንቀሳቀሱት ተወዳዳሪ ኃይሎች የተጋለጡ አልነበሩም፡፡ ይህ በሲቪል ሎው የሕግ ሥርዓት ተከታይ ሃገራት በአድቮኬቶችና ላቲን ኖታሪዎች እንዲሁም በኮመን ሎው የሕግ ሥርዓት ተከታይ ሃገራት በባሪስተሮች፣ ሎሊሳይቶሮች እና ኮንቬሮች መካከል ተመሳሳይ እውነታ ነበር፡፡ በእነዚህ በሁለቱ ሥርዓት የሕግ ሙያ ቁጥጥር የሚተገበረው በቀጥተኛ የመንግሥት ቁጥጥርና በላቀ ሁኔታ ደግሞ በራስ አስተዳደር (self regulation) ባለሙያዎች በተቀረፁ ሕጎች በመተዳደር ነው፡፡ ይህ የሕግ ሙያ ቁጥጥር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በእነዚህ ሥርዓቶች በፈጠረው የፀረ-ውድድር ተፅዕኖ ምክንያት በከፍተኛ ሁኔታ እየተተቸ ይገኛል፡፡ 

Continue reading
  13908 Hits

‘ጠባቂ የሌለው ጠበቃ’ ጥቂት ስለ ኢትዮጵያ የሕግ ባለሞያዎች ማህበር

 

 

  1. መነሻ ነጥብ[1]

የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያዎች ማህበር በ1958 ዓ.ም.በእድርና እቁብ አይነት ቅርጽ የተመሰረተ ድርጅት ነው፡፡ በሰዓቱ ከአርባ የማይበልጡ አባላት የነበሩት ሲሆን አባሎቹም በከተማይቱ አዲስ አበባ የጥብቅና አገልግሎት የሚሰጡ ነበሩ፡፡ ይህ ማህበር የተደራጀና የአባላቱን እንዲሁም የተከበረ ሙያ የሆነውን የጥብቅና ሙያ ለማስጠበቅና ለመጠበቅ ሳይሆን በማህበርተኞች መካከል ለሚፈጥሩ ማህበራዊና ሰዋዊ ችግሮች ለመረዳዳት ተብሎ የተመሰረተ ተቋም ነበር፡፡ ይህ ስብስብ በተመሰረተ በአመቱ ማለትም በ1959 ዓ.ም. በቀድሞው አጠራር የሀገር ግዛት ሚኒስቴር ተመዝግቧል፡፡ ከአብዮቱም በኋላ የኢትዮጵያ የጠበቆች ማህበር የሚለውን ስያሜ የያዘ ሲሆን በማህበሩ ውስጥ ጠበቆች፣ የሕግ መምህራን፣ ዳኞች፣ የሕግ ጉዳይ ፀሐፊዎች እና ሌሎችም አባል ሆነው ይሰሩ ነበር፡፡ ስሙን ቀይሮ የመጣው ማህበር የግብርና የዓላማ ለውጦችንም በማድረግ ደረጃውን የጠበቀ የጥብቅና ሙያ እንዲኖር ግንባር ቀደም ዓላማው አድርጎ ተነሳ፡፡ በወቅቱም ልክ አሁን እንዳለው ተመሳሳይ አሰራር የጥብቅና ፍቃድ በማሳየትና የአባልነት ክፍያ በመክፈል አባል መሆን ይቻል ነበር፡፡

ብዙ ያነጋገረው የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማሕበራት አዋጅ ማለትም አዋጅ ቁጥር 621/2000 ከወጣ በኋላም ማህበሩ በድጋሚ ምዝገባ የማህበሩን ስያሜ ከኢትዮጵያ የጠበቆች ባለሙያዎች ማህበር ከሚለው ወደ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያዎች ማህበር ለውጦ ተመዝግቧል፡፡ የስም ለውጡ በሁለት አበይት ምክንያቶች የመጣ ነው፡፡ አንደኛው በክልሎች ላይ የጠበቆች ማህበር የሚለው ስያሜ ስላለና ይህንን ተመሳሳይ ስም ሌላ ማህበር መጠቀም አይችልም በማለት ሲሆን ሁለተኛው ዐብይ ምክንያት ደግሞ ማህበሩ ላይ ተሳታፊ የነበሩ አባላት ጠበቆች ብቻ ስላልነበሩ የጠበቆች ሳይሆን የሕግ ባለሙያዎች ቢባል ሁሉንም አካታች ስለሚሆን መልካም ነው በሚል ነው፡፡ በአሁን ሰዓት ማህበሩ ከሰባት መቶ ያልበለጡ አባሎች ያሉት ሲሆን ወርሀዊ መዋጮውም ሀምሳ ብር ነው፡፡

Continue reading
  11673 Hits