ችሎት መድፈር፡- ሕጉ እና የአሠራር ግድፈቶች

 

 

የኢፌድሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 449፦

449. ፍርድ ቤትን መድፈር

(1) ማንም ሰው በፍርድ ቤት ምርመራ በሚደረግበት ወይም የፍርድ ሥራ በሚከናወንበት ጊዜ፦

Continue reading
  12832 Hits

ችሎት መድፈር በኢትዮጵያ ሕግ: ሕጉና አተገባበር

 

መግቢያ

"ችሎት መድፈር" ወይም Contempt of Court በአብዛኛው ሃገራት የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ግልጋሎት ላይ እየዋሉ ካሉ የሕግ ፅንሰ ሃሳቦች አንዱ ነው። ይህ የሕግ ፅንሰ ሃሳብ በእኛ ሃገር በሰፊው ሥራ ላይ እየዋለ ቢሆንም ከሕጉ መንፈስ ውጭ አተገባበሩ ላይ የሚታየው የሕግ አተረጓጎም ክፍተትና ልዩነት የተለያዩ የዜጎች መብት ጥሰቶችን ሲያስከትል ይታያል። 

ችሎት መድፈር በኢትዮጵያ ሕግ ምን ይመስላል? አተገባበሩና ችግሮቹስ?

"ችሎት መድፈር" ምን ማለት ነው?

ለሕግ ወይም ለፍርድ ቤት አለመታዘዝ፣ ለችሎት ክብር መንፈግ ወይም የፍርድ ቤትን ሥራ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለማወክ መሞከር አልያም ደግሞ በዳኝነት ሥራው ጣልቃ መግባት በተለምዶ "ችሎት መድፈር" ተብሎ ይጠራል።

Continue reading
  8741 Hits

የማይደፈረውን ፍርድ ቤት መድፈር

 

 

በአንጌሳ ኢቲቻ የተጻፈውን ‹‹ችሎት መድፈር፡- ሕጉና የአሠራር ግድፈቶች›› የሚለውን ሳነብ እ.አ.አ በታኅሣስ 2013 በተመሳሳይ ርዕስ የጻፍኩትን ለአንባብያን ለማካፈል ወደድኩ፡፡ በዚህ ጽሑፌ ፍርድ ቤት መድፈር ምን ማለት ነው? የኢትዮጵያ ሕግ ስለ ፍርድ ቤት መድፈር ምን ይላል? የሕጉ ዓለማስ ምንድነው፣ የወንጀሉ አወሳሰን ልዩ ባህርይስ እንዴት ይታያል፣ በአፈጻጸም የሚታዩ ችግሮች ምንድናቸው የመሚለውን እዳስሳለሁ፡፡

በወቅቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ይዞት የወጣው ከፍርድ ቤት ጋር የተያያዙ ሁለት ዜናዎች አንባቢውን በተለይም የሕግ ባለሙያዎችን የሚያስገርም ነበር፡፡ የመጀመሪያው ዜና አንድ የፖሊስ አባል የፌዴራል ፍርድ ቤት ዳኛን በማመናጨቅና ፍርድ ቤት በመድፈር ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው መታሠራቸውና ሌሎቹ ፖሊሶች ጉዳይ በቀጠሮ ላይ መሆኑ ነው፡፡ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሁለተኛ ፍትሐብሔር የቤተሰብ ችሎት ውስጥ የተፈጸመው ይህ ወንጀል ለየት የሚያደርገው ሕግን ለማስከበር አስፈጻሚውን በሚወክለው በፖሊስ መፈጸሙ ብቻ አይደለም፡፡ ፖሊሶቹ ያሳዩት ባህርይና ኃላፊዎቹ የሰጡት መልስ የበለጠ አስገራሚ ነበር፡፡ ፖሊሶቹ በጊዜው የዳኝነት ሥራ ስታከናውን የነበረችይቱን ዳኛ ‹‹አንመጣም›› ‹‹አንቀርብም›› ‹‹ስቀርብ ትፈትሽኛለሽ›› ‹‹ነገርኩሽ እኮ›› ወዘተ. በማለት ፍርድ ቤቱን ዝቅ የሚያደርግ፣ በኅብረተሰቡ ውስጥ ያለውን መተማመን የሚያሳጣና ሌሎች ዳኞችን የሚያሳቅቅ ነው፡፡ የፍርድ ቤት መድፈር በአብዛኛው በተከራካሪ ወገኖች፣ በቤተ ዘመዶቻቸው፣ በጋዜጠኞች ወዘተ. ተፈጸመ ተብሎ መስማት የተለመደ ነው፡፡ ችሎቱን ለማስከበር በተሰማሩት የፖሊስ አባላት መፈጸሙ ግን የበለጠ ግርምት ይፈጥራል፡፡ በጊዜው የፖሊስ ኃላፊው ‹‹ልጆቹ ጥፋት ያጠፉት ልጆች ስለሆኑ ነውና ይቅርታ ይደረግላቸው›› የሚለው ደግሞ፣ የፖሊስ ተቋሙ በፍትሕ አደባባይ፣ የሚበሳጭና የሚናደድ ተከራካሪ በሚኖርበት፣ ኅብረተሰቡ በብዛት አንዱን ነቅፎ ለሌላው ወግኖ በሚቆምበት ቦታ የሚመድባቸውን ፖሊሶች የትምህርትና የልምድ ሁኔታ ጥያቄ ውስጥ የማያስገባ ነው፡፡ ሁለተኛው ዜና የከፍተኛው ፍርድ ቤት ትዕዛዝ በአዲስ ክፍለ ከተማ መሬት ልማት ማኔጅመንት የመጣሱ ዜና ነው፡፡ በፍርድ ቤት በተያዘ አንድ ጉዳይ ፍርድ ቤቱ እንዳይፈርስ የእግድ ትዕዛዝ የሰጠበትን የንግድ ቤት የእግድ ትዕዛዙ ደርሶት ክፍለ ከተማው ቤቱን የማፍረሱ ዜና እጅጉን አስደንጋጭ ነው፡፡

እነዚህ ሁለት ዜናዎች በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ የተጋረጡትን ፈተናዎች አመላካች ናቸው፡፡ ፍርድ ቤቶች ከሦስቱ የመንግሥት አካላት አንዱ እንደመሆናቸው ሕገ መንግሥታዊ ጥበቃና ኃላፊነት ተሰጥቷአቸዋል፡፡ ፍርድ ቤቶች አስፈጻሚውን የመቆጣጠር ሕገ መንግሥታዊ ግዴታ ያለባቸው ሲሆን አስፈጻሚውን ለመቆጣጠር ባልቻሉ መጠን ህልውናቸው ላይ አደጋ ይፈጥራል፡፡ በሁለቱ ዜናዎች ፍርድ ቤቱ የተደፈረው በአስፈጻሚው አካል እንደመሆኑ መጠን የፍትሕ ተቋሙ ተመሳሳይ ጥሰቶች እንዳይኖሩ ተግቶ ሊሥራ እንደሚገባው አመላካች ነው፡፡ በአስፈጻሚው አካል ክብር ያልተሰጠው ፍርድ ቤት በተራ ዜጋው ክብር ይሰጠዋል ማለት አስቸጋሪ ነው፡፡ ተመሳሳይ ድርጊቶች በፍርድ ቤቶች ወይም በዳኞች ላይ የሚፈጸሙ ከሆነ ፍርድ ቤቶች በኅብረተሰቡ ውስጥ ያላቸውን ክብርና መተማመን ማጣታቸው አይቀርም፡፡ የራሱን መብት የማያስከብር ፍርድ ቤት የሌላውን ዜጋ መብት እንዲያስከብር መጠበቅ ሞኝነት መሆኑ ነጋሪ አይፈልግም፡፡

Continue reading
  9512 Hits