የኤቲኤም ካርድ በጠፋ ጊዜ የባንክ ኃላፊነት

 

በዘመናዊ የባንክ አገልግሎት ክፍያን ከሚያሳልጡ አሠራሮች መካከል አንዱ የኤቲኤም ካርድ አገልግሎት ነው፡፡ አንድ የባንክ ደንበኛ በባንኩ ውስጥ በከፈተው ሒሳብ ያጠራቀመውን ገንዘብ ለማውጣት የቁጠባ ሒሳብ ደብተሩን መያዝ፣ የባንክ ባለሙያን ማነጋገር፣ ገንዘብ ወጪ ለማድረግ የሚያስችል ፎርም መሙላት፣ ወረፋ መጠበቅ ወዘተ. አይጠበቅበትም፡፡ በደንበኛውና በባንኩ መካከል በሚፈጸም የኤቲኤም ካርድ አገልግሎት ውል ከባንኩ ካርዱንና የሚስጥር ቁጥሩን በመቀበል ባንኩ በተለያዩ ቦታዎች ካስቀመጣቸው የኤቲኤም ማሽኖች አገልግሎት ማግኘት ይችላል፡፡ በአገራችን ይህ አሠራር በተግባር ላይ ከዋለ የተወሰኑ ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን፣ በጣም ውሱን ከሆኑ ጀማሪ ባንኮች በስተቀር በሁሉም የግልና የመንግሥት ባንኮች ተፈጻሚ ሆኗል፡፡ የኤቲኤም ካርድን መጠቀም የራሱ የሆኑ ጥቅሞች እንዳሉት የታመነ ቢሆንም፣ የተወሰኑ በአጠቃቀም ወቅት የሚስተዋሉ ችግሮች እንዳሉ ብዙ ሰው የሚያውቀው ነው፡፡ የኤቲኤም ካርድ በአንዳንድ ማሽኖች ተቀባይነት አለማግኘቱ፣ አንዳንዶቹ ፈጽሞ የማይሠሩ (Active ያልሆኑ) መሆናቸው፣ በአንድ ቀን ማውጣት የሚቻለው የገንዘብ መጠን መወሰኑ፣ የኔትወርክ አለመኖርና ተደጋጋሚ የማሽን ብልሽት፣ በቂ የክፍያ ማሽኖች በየቦታው አለመኖራቸው፣ በኤቲኤም አሠራር የሚታዩ ግድፈቶች ወዲያው ሊታረሙ አለመቻላቸው ተጠቃሽ ችግሮች ናቸው፡፡ በዚህ ጽሑፍ የምንመለከተው ግን ከባንኩ ውጭ በሆኑ ምክንያቶች በኤቲኤም ካርድ አገልግሎት ላይ ከተጋረጡ ችግሮች ዐቢይ የሆነውን የካርድ መጥፋት ጉዳይ ነው፡፡

በባንኮችና በደንበኞቻቸው መካከል የሚፈረም የኤቲኤም ካርድ አገልግሎት ውል ደንበኞች ካርዳቸውን ወይም የሚስጥር ቁጥራቸውን ለሦስተኛ ወገን አሳልፈው እንዳይሰጡ፣ ካርዳቸውን እንዳይጥሉ፤ ይህ ካልሆነ ግን ካርድ በመጥፋቱ፣ ወደ ሦስተኛ ወገን በመተላለፉ ወይም የሚስጥር ቁጥሩ በመገለጡ ምክንያት ለሚመጣው ጉዳት ደንበኞቹ ኃላፊ ሊሆኑ እንደሚገባ ነው፡፡ የኤቲኤም ካርድ በጠፋ ጊዜም ግን ባንኮች ኃላፊነት ሊኖርባቸው የሚችልበት ሁኔታ ዝግ አይደለም፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት 17 ቮልዩም አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ ከሰጠባቸው ጉዳዮች ውስጥ የሰበር መዝገብ ቁጥር 96309 አንዱ ሲሆን፣ በዚህ ጽሑፍ ይህን አስተማሪ ፍርድ መነሻ በማድረግ አጠር ያለ ዳሰሳ ለማቅረብ እንሞክራለን፡፡

የጉዳዩ አመጣጥ

ጉዳዩ የጀመረው በፌዴራል መጀመሪያ ፍርድ ቤት ሲሆን፣ ከሳሽ አቶ ዓለማየሁ ግርማ ተከሳሽ ደግሞ ዳሸን ባንክ ነው፡፡ ደንበኛው በባንኩ የቁጠባ ሒሳብ ተጠቃሚ ሲሆኑ፣ የቁጠባ ሒሳባቸውን በኤቲኤም ካርድ ያንቀሳቅሳሉ፡፡ ጥር 23 ቀን 2003 .. የደንበኛው የኤቲኤም ካርድ ይጠፋል፤ ደንበኛውም መጥፋቱን ጥር 25 ቀን 2003 .. በጽሑፍ ለባንኩ ያሳውቃሉ፡፡ ይሁን እንጂ ባንኩ የኤቲኤም ሒሳባቸውን ባለመዝጋቱ ሪፖርት ከተደረገበት ቀን ጀምሮ እስከ የካቲት 9 ቀን 2003 .. ባንኩ ለማይታወቁ ሦስተኛ ወገኖች ብር 40,300 በኤቲኤም ክፍያ ይፈጽማል፡፡ በዚህ ጊዜ ነው ደንበኛው ባንኩ ሒሳቤን መዝጋት ሲገባው ባለመዝጋቱ ያለፈቃዳቸው ወጪ ለተደረገው ገንዘብ ወለድና ወጪ ባንኩ ኃላፊ እንዲሆን ክስ ያቀረቡት፡፡

Continue reading
  17432 Hits