የዞን ዘጠኝ አምስት ተከሳሾች ክስ መቋረጥ ብዥታ

መጠይቅ ደግ ነው፡፡ የአስፈጻሚ አካላት ሥልጣንና ተግባራትን ለመደንገግ የወጣው አዋጅ ቁጥር 691/2003 አንቀጽ 16(6) ፍትሕ ሚኒስቴር በቂ ምክንያት ሲኖር በሕግ መሠረት ሂደት ላይ ያለን ክስ ያነሳል በሚል ይደነግጋል፡፡ ፍትሕ ሚኒስቴር የተሰጠው ክስ የማንሳት ሥልጣን እስከምን ድረስ ነው? ክስ ማንሳት በማንኛውም ጊዜ ይቻላል? ክሱን ሲያነሳስ በቂ ምክንያቱን ለፍርድ ቤቱ ያቀርባል? በቂ ምክንያትስ የምንለው ምንድን ነው? የክስ መነሳትስ ተከሳሾች ላይ ያለው ውጤት ምንድን ነው? በዚህ ሂደት የፍርድ ቤቶች ሚና ምን መሆን ይገባዋል? የሚለው ጥያቄ ሊመለስ የሚገባው ነው፡፡

  11529 Hits