ዓለም አቀፍ ስምምነቶች በኢትዮጵያ የሕግ ሥርዓት ያላቸው ደረጃ

 

1.    ስለዓለም አቀፍ ሕግ በአጭሩ

ዓለም አቀፍ ሕግ በሉዓላዊ አገሮች መካከል ያለን ግንኙነት ወይም በአገሮችና እንደተባበሩት መንግሥታት ያሉ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች መካከል ያለን ግንኙነት የሚገዛ የሁሉ አቀፍ ደንቦች እና መርሆዎች ሥርዓት ነው። በሌላ አነጋገር «International law is the universal system of rules and principles concerning the relations between sovereign States, and relations between States and international organizations such as the United Nations» የሚል ትርጉም ተሰጥቶት እናገኘዋለን። ቀደም ባሉት ጊዜያት በዓለም አቀፍ ሕግ እና በየሐገሩ በሚገኙ ዜጎች፣ ሉአላዊ ባለሆኑ አካላት (Transnational Corporations) እና መንግሥታዊ ባለሆኑ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች (International Non-Governmental Organization) ቀጥተኛ ግንኙነት ያለነበረ ቢሆንም አሁን አሁን ግን ይህ የታሰበው ቀጥተኛ ግንኙነት በስፋት እየታየ መሆኑን ዓለም አቀፍ ምሁራንን እያስማማ ነው።

ይሁን እንጂ ዓለም አቀፋዊ የሆነ ማዕከላዊ ሕግ አውጭ ባለመኖሩ፣ አለፎ አልፎ ከሚታዩት በስተቀር ዓለም አቀፍ ሕግን ውጤታማና ቀጣይነት ባለው መልኩ እንዲከበር የሚያደርጉ የእርምጃ ዘዴዎች ባለመጎልበታቸው፣ እራሱን የቻለ የተጠናከረ ማዕከላዊ አስፈጻሚ አካል ጎልቶ አለመታየቱ (የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ሳይዘነጋ መሆኑ ይታወቃል) ፣ ክርክሮችን ተቀብሎ እልባት የሚሰጠው ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤትም ስራውን የሚያከናውነው እና ችሎት የሚቀመጠው አለመግባባት የታየባቸው አገሮች በራሳቸው ፍቃደኝነት ጉዳያቸውን ሲያቀርቡለት እንጂ አስገድዶ የማስቀረብ ሥልጣኑም ሆነ ተቋማዊ አደረጃጀት የሌሉት መሆኑ እና ዓለም አቀፍ ሕግ በዓለም ላይ ተጽዕኖ ፈጣሪ በሆኑ አገሮች ጥቅምና አምሳል የተፈጠረ በመሆኑ እና አፈፃፀሙም በእነሱ ተጽዕኖ ሥር በመውደቁ ፍትሃዊነቱ አጠያያቂ ነው፣ የደሃ ሐገሮችን ጥቅም አያስጠብቅም የሚሉ ትችቶችን ወ.ዘ.ተ. ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ዓለም አቀፍ ሕግ የሚባል ነገር እንደ ሕግ የመቆም ብቃት የለውም የሚሉ ወገኖች እየበረከቱ መጥተዋል። በተለይ የሕግ መሠረታዊ ባህሪ ነው ተብሎ የሚታሰበውን የአስገዳጅነት ተፈጥሮ አልተላበሰም በሚል የሕግ ዋጋ የለውም እያሉ ክፉኛ ያብጠለጥሉታል።  ሌሎች ደግሞ እንደ ሕግ ባለመከበሩና በመጣሱ ምክንያት ብቻ ሕግ ከመሆን የሚያግደው ነገር የለም ባይ ናቸው። እንደዚያም ከሆነ ብሄራዊ ሕጎችስ በተደጋጋሚ ሲጣሱ ይታዩ የለምን? ሲሉ በአጽእኖት ይጠይቃሉ፣ እናም የዓለማችን ግንኙነት እየሰፋ በመጣበት በአሁኑ ወቅት የዓለም አቀፍ ሕግን አሳንሶ መመልከትም ይሁን ጭራሽ እልውናውን መፈታተን እውነታን ያላገናዘበ ድምዳሜ ነው ሲሉም ትችት ያቀርባሉ።   

ዓለም አቀፍ ሕጎች በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች ልንመድባቸው እንችላለን። እነሱም ዓለም አቀፋዊ የመንግሥት ሕግ (Public International Law) እና ዓለም አቀፋዊ የግል ሕግ (Private International Law) በማለት ሲሆን ዓለም አቀፋዊ የመንግሥት ሕግ በሁለት ወይም ከዚያ በላይ በሆኑ ራሳቸውን በቻሉ ነፃ እና ሉአላዊ አገሮች መካከል የሚፈጠረውን የሁለትዩሽ ወይም ከዚያ በላይ ግንኙነቶች የሚገዛና የሚቆጣጠር ሕግ ነው። በሌላ በኩል ዓለም አቀፋዊ የግል ሕግ በፍትሐብሄር ጉዳዩች ዙሪያ የሚፈጠሩ ግንኙነቶች እና አለመግባባቶች በሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ አገሮች ዜጎችን በተፎካካሪነት ያሳተፈ ሲሆን አልያም የሌሎች አገር ተወላጆች ንብረት በአንዲት አገር የሚገኝ ከሆነ እንዲሁም የውጭ አገር ዜጎች አንዳንድ የፍትሐብሄር ድርጌቶችን ለምሳሌ ውርስ፣ ውል፣ ከውል ውጭ የሚያስጠየቁ ኩነቶችን የፈፀሙ እንደሆነ አለመግባባቱ መፍትሄ የሚያገኘው በዓለም አቀፍ የግል ሕግ አማካኝነት ነው።   

Continue reading
  16505 Hits

Ethiopia’s Human Rights Treaty Reporting to the UN Treaty Bodies

INTRODUCTION

Preamble of the United Nations (UN) Charter requires member states and the people of the UN “to reaffirm faith in fundamental human rights, in the dignity and worth of the human person, in the equal rights of men and women and of nations large and small”. In order to achieve this goal of the charter and secure universal recognition and implementation of human rights to their citizens’ member states of the United Nations entered into seven major human rights treaties.

 

The seven core international human rights treaties create legal obligations for state parties to promote and protect human rights at the national level. When a country accepts one of these treaties through ratification, accession or succession, it assumes a legal obligation to implement the rights set out in that treaty. In addition to this, state parties to these treaties have also the obligation to report every activities conducted in the name of implementation to the United Nations treaty based bodies. 

Ethiopia as a member of the United Nation and member of these human rights treaties has the obligation to implement the treaties and report its implementation. However, a part from the implementation problem Ethiopia has been criticized for its failure or delay to report its implementation of the treaties. Keeping in mind this criticism related to Ethiopian human rights reporting record, questions and issues related with human rights reporting system with special emphasis to the Ethiopian context is assessed and analyzed under this paper. And, just because human rights reporting are highly related with the rights enshrined under the treaties concepts about some rights are discussed in a summarized fashion.  

Continue reading
  24651 Hits