ጸሐፊው በዓለም አቀፍ ሕግ ሁለተኛ ዲግሪ ያላቸው ሲሆን በአሁኑ ሰዓት በመንግሥት መሥሪያ ቤት በሕግ ባለሙያነት እያገለገሉ ይግኛሉ። ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻው በ berhanbekele5@gmail.com ማግኘት ይቻላል።

የሕግ አረቃቀቅ ሥርዓት በኢትዮጵያ

ሕግ ማርቀቅ አንዱ እና ዋነኛው የሕግ ሙያ ዘርፍ ነው፡፡ ሕግ ማውጣት የሚያስፈልግበት ዋና ዓላማ የመንግስትን ፖሊሲ ለማስፈፀም ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ሕግ የፖሊሲ ማስፈፀሚያ ተደርጎም ይወሰዳል፡፡ የሕግ አረቃቅ ላይ ሊወሰድ የሚገባው ጥንቃቄ እና የአረቃቅ ሂደቱ ሕጉ ከፀደቀ በኋላ የሚኖረው አተገባበር ላይ ቀጥተኛ የሆነ ተፅእኖ ያለው መሆኑ ይታወቃል፡፡ የሕግ አረቃቀቅ በኢትዮጵያ ወጥነት የሚጎድለው፤ ትኩረት የሚሻ እና በሕግ አግባብ ሊመራ የሚገባ ዘርፍ ነው፡፡አሁን ላይ ይህ ዘርፍ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚመራበት አንድ ወጥ የሆነ የሕግ ማዕቀፍ የሌለውም ዘርፍ ነው፡፡ ዘርፉ በዚህ አግባብ የሚመራበት የሕግ ማዕቀፍ አለማግኘቱ በሕጎች አረቃቀቅ ጥረት፤ ወጥነት፤ መናበብ፤ እና አፈፃፀም ላይ የራሱ የሆነን አሉታዊ ተፅእኖ እንዳሳደረ ይታመናል፡፡

  1249 Hits

Would ‘reception’ look different in Ethiopia if we considered international law a custom rather than a treaty?

Until this day, no scholarly research has squarely dealt with the process of reception of international law into Ethiopia’s domestic legal system and its status and relationship with domestic laws. Some works have addressed the position of international human rights treaties in the Ethiopian legal order. However, the vexing issues that need clarification are: the process of reception of treaties and non-treaty sources of international law into the Ethiopian legal system; whether there are requirements to be met for the direct application of ratified treaties by Ethiopian courts and other state organs; the hierarchical relations between international law applicable to Ethiopia and its national laws; and the division of treaty-making power within the country’s federal legal system.

  1076 Hits

የመንግሥትና የግል አጋርነት አዋጅና መመሪያ ይዘት አጭር ማብራሪያ

መንግሥት ብቻውን የሀገሪቱን የመሠረተ ልማት ፕሮጀክት ሥራዎች ማከናወን የማይችል ከመሆኑ በተጨማሪ የግሉ ዘርፍ በሀገሪቱ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክት ሥራዎች ላይ የራሱን የሆነ ድርሻ ሊወጣ የሚገባው መሆኑን ተከትሎ በዚህ ረገድ መንግሥት ከግሉ ዘርፍ ጋር የሚኖረውን የሥራ ግንኙነት ለመወሰን እና በሕግ አግባብ ለመምራት ይቻል ዘንድ መዉጣቱ ይታወሳል፡፡

  1403 Hits