ሺሻን ለሽያጭ ከማቅረብና ከመጠቀም ጋር ተያይዘው የሚፈፀሙ ወንጀሎች

በልደታ ክፍለ ከተማ ውስጥ ሺሻ በማስጨስ ተግባር ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ግለሰቦች እና የማስጨሻ ቤቶች መኖራቸውን የተረዳው የልደታ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ እና በሥሩ የሚገኙ የተለያዩ ፖሊስ ጣቢያዎች የሺሻ ማስጨሻ ዕቃዎችን እና ሺሻ ሲያስጨሱ የነበሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር አውለዋል፡፡ ሺሻን ሲያስጨሱ የነበሩ ግለሰቦች ላይም የወንጀል ምርመራ የተጣራባቸው ሲሆን በምርመራ መዛግብቱ ላይ በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ በኩል ተገቢውን የሕግ አስተያየትና ውሳኔ መስጠት ይጠበቃል፡፡ ሆኖም ጉዳዩ ከዚህ ቀደም በፌዴራል ፍርድ ቤቶችና በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ ሲታይ ያልነበረ በአንፃሩ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶችና በከተማ ነክ ፍትሕ ጽ/ቤቶች የአቤቱታ ምርመራና የክስ አቀራረብ ንዑስ የሥራ ሂደት ሲታዩ የነበረና ሺሻን አስመልክቶ በቂ መረጃና የሕግ ማዕቀፍ ያልነበረ በመሆኑ በተጣሩት የምርመራ መዛግብት ላይ ተገቢውን የሕግ አስተያየት እና ውሳኔ ለመስጠት አስቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል፡፡

 

በመሆኑም የሺሻን ምንነት፣ ሺሻ የሚይደርሰውን ጉዳት፣ ሺሻን መጠቀም፣ ማስጠቀም እና ወደ አገር አስገብቶ ማከፋፈል ከሕግ አንፃር የሚያስከትለው ኃላፊነት ስለመኖሩ፣ ፖሊስና የወረዳ (ቀበሌ) አስተዳደር ሠራተኞች ሺሻ የሚያጨሱና የሚያስጨሱ ግለሰቦችን እንዲሁም የማስጨሻ ዕቃዎችን የሚይዙበትና ማስጨሻ ቤቶችን የሚዘጉበትን እንዲሁም ዐቃቤ ሕግ ሺሻ በሚያስጨሱ ግለሰቦች ላይ የተጣሩ የምርመራ መዛግብት ላይ የሕግ አስተያየት እና ውሳኔ የሚሰጥበት አግባብ ላይ እንደ አጠቃላይም ከሺሻ ጋር ተያይዘው ለሚነሱ ችግሮች የመፍትሄ ሃሳብ በማቅረብ ላይ ያተኮረ አነስተኛ ጥናት ማዘጋጀቱ አስፈላጊ ሆኗል፡፡ በዚሁ መሠረትም ይህ አነስተኛ ጽሑፍ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡

 

የሺሻ ምንነት

Continue reading
  11130 Hits
Tags:

ጣዕም መቀየሪያዎች የተጨመሩባቸው የሺሻ ትምባሆ ምርቶች መስፋፋትና ሕገ ወጥነት

በኅብረተሰብ ጤና ዘርፍ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የሚባል ለውጥ ካስመዘገቡ አገሮች ተርታ ትመደባለች፡፡ የጤና አገልግሎትን በቀበሌ ደረጃ ለማስፋፋት፣ በተለይም በዝቅተኛ የኢኮኖሚ ደረጃ ላይ የሚገኘውን የኅብረተሰብ ክፍል ማዕከል ያደረገና በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና የተቸረውን የጤና ኤክስቴንሽን መርሐ ግብር ተግባራዊ በማድረግ፣ የዓለም መንግሥታት ድርጅትን የጤና የሚሊኒየም ግቦችን ለማሳካት ችላለች፡፡ እንደ አብዛኛው ታዳጊ አገሮች ሁሉ ባለፉት ዓመታት የመንግሥት የጤና ፕሮግራሞችና የአጋር ድርጅት ትኩረቶች ውስጥ ወባ፣ ኤችአይቪ/ኤድስና ሳንባ ነቀርሳ የመሳሰሉ ተላላፊ በሽታዎች የመከላከልና ቁጥጥር ሥራ፣ እንዲሁም የሕፃናትና እናቶች ጤናን ማሻሻል በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡ ሆኖም ግን ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ የአገሪቱ የበሽታዎች ሥርጭት ሁኔታ በለውጥ ሒደት ላይ ያለ ሲሆን፣ በተለይም በከተማዎችና በዙሪያቸው ባሉ ሥፍራዎች በመስፋፋት ላይ የሚገኙት የልብ፣ የመተንፈሻ አካላት፣ ስኳርና ካንሰርን የመሳሰሉ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ይጠቀሳሉ፡፡

ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች እየተስፋፉ በመምጣታቸው ምክንያት የጤና ጥበቃ ሚኒስቴርን የትኩረት አቅጣጫ የሚያሳይ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መከላከያና መቆጣጠሪያ ብሔራዊ የድርጊት መርሐ ግብር ስትራቴጂ (National Strategic Action Plan (NSAP) for Prevention & Control of Non Communicable Diseases in Ethiopia) በ2007 ዓ.ም. ተዘጋጅቷል፡፡ ለእነዚህ በሽታዎች ወይም የጤና ሁኔታዎች ዋነኛ ምክንያቶች ተብለው ከተለዩት መካከልም ማንኛውንም ዓይነት የትምባሆ ምርት መጠቀም፣ ከመጠን በላይ የአልኮል መጠጦችን መውሰድ፣ በቂ የአካል እንቅስቃሴ አለማድረግና ለጤና ተስማሚ ያልሆኑ ምግቦችን ማዘውተር ይጠቀሳሉ፡፡

ከብሔራዊ የድርጊት መርሐ ግብር ስትራቴጂው በተጨማሪ በተመሳሳይ ዓመት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች አጋላጭ ከሚባሉት ዋነኛ መንስዔዎች አንዱ የሆነውን የትምባሆ ምርትን በሚመለከት፣ በዓለም የጤና ድርጅት የወጣውን የትምባሆ ምርት ቁጥጥር ማዕቀፍ ኮንቬንሽን አፅድቋል፡፡ ተግባራዊነቱን የኢትዮጵያ የምግብ፣ መድኃኒትና ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለሥልጣን እንዲከታተል ኃላፊነት በአዋጅ ቁጥር 822/2007 ሰጥቷል፡፡

በዚህ አዋጅ መሠረት የትምባሆ ምርት ቁጥጥር ማዕቀፍ ኮንቬንሽን ማፅደቂያ በከፊል ለማስፈጸም ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ከሁለት ዓመት በፊት የትምባሆ ቁጥጥር መመርያ አውጥቷል፡፡ የትምባሆ ቁጥጥር መመርያው ከአፈጻጸም ጋር በተያያዘ የተለያዩ ክፍተቶች ቢኖሩበትም፣ ሕፃናትንና ታዳጊ ወጣቶችን በእጅጉ ሱስ አስያዥ የሆነው ኒኮቲክ ለሚባለው ንጥረ ነገር ተጋላጭነት ለመቀነስና ብዛት ባላቸው አገሮች እያደገ በመጣው የትምባሆን ምርት ጣዕም መቀየሪያ እንዳይጨመርበት በመከልከል፣ ሊመሰገን የሚገባው የሕግ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡ ተመሳሳይ የሆኑ ድንጋጌዎች የያዘ የትምባሆ ምርት ቁጥጥርን መመርያ በተወሰኑ ክልሎችና በከተማ አስተዳደር ደረጃ ጭምርም የወጣ ሲሆን፣ ይህን ዓይነት ምርት በክልሎች ውስጥ ለሽያጭ ማቅረብ፣ መሸጥና ማከፋፈል የተከለከለ ነው፡፡ 

የኢትዮጵያ የምግብ፣ መድኃኒትና ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለሥልጣን ባወጣው የትምባሆ ምርት ቁጥጥር መመርያ ቁጥር 28/2007 መሠረት፣ የትምባሆ ምርት የሺሻ ትምባሆን ጨምሮ ማንኛውንም በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ከትምባሆ ቅጠል የተዘጋጀ በማጨስ፣ በመሳብ፣ በማኘክ፣ በማሽተት ወይም በሌላ መንገድ የሚወሰድ ንጥረ ነገርን እንዲያካትት ሆኖ ተተርጉሟል፡፡ ይህ ማለት ትምባሆ በስፋት በሚታወቀው የሲጋራ ምርት ብቻ ሳይወሰን የሚታኘክን፣ እንዲሁም የተለያዩ የማጨሻ መሣሪያዎችን በመጠቀም የሚጨስ እንደ ሺሻ ትምባሆ ያለን ምርት ያካትታል፡፡ ይህ የትምባሆ ምርት ትርጉም በተወካዮች ምክር ቤት በፀደቀው የትምባሆ ምርት ቁጥጥር ማዕቀፍ ኮንቬንሽን ጋር የተጣጣመ ሆኖ፣ የሺሻ ትምባሆን ወይም በባህላዊ መንገድ የሚዘጋጅ ጋያን በግልጽ እንዲያካትት ሆኖ ነው የተቀመጠው፡፡

Continue reading
  8982 Hits
Tags: