የንግድ ፈቃድን ማከራየት በወንጀል ያስቀጣል?

በሀገራችን የንግድ ሕግ ሥርዓት መሠረት ነጋዴነት ምን መብቶችና ግዴታዎች አሉበት? ለመሆኑ አንድ ነጋዴ በሥሙ ያወጣውን የንግድ ፈቃድ ለሌላ ሰው ማከራየትና በኪራይ ውል ማስተላለፍ ይችላል? አከራይቶ ቢገኝስ በወንጀል ሊያስከስሰውና ሊያስቀጣው ይችላልን? የነጋዴነት መብቶችና ግዴታዎች በየትኞቹ ህግጋት ይገዛል? የነጋዴዎችን መብትና ግዴታዎች በዋናነት የሚመለከቱት ሕግጋት በአዋጅ ቁጥር 166/1952 የወጣውና ከመስከረም 1 ቀን 1953 ዓ.ም ጀምሮ በሥራ ላይ የዋለው የንግድ ሕግ፣ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅና ደንብ እና ግብርን የሚመለከቱ ሕጎች ሲሆኑ ሌሎች ህግጋትም እንደ የውል ሕግ፣ የኪራይ ሕግ፣ የአሠሪና ሠራተኛ ሕግ፣ የወንጀል ሕግ.... በነጋዴዎች ላይ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የሚያስከትሉት መብትና ግዴታዎች ይኖራሉ፡፡ በዚህ አጭር ጽሁፍ ስለ ነጋዴዎች መብትና ግዴታዎች በዝርዝር ለመጻፍ የማይቻል በመሆኑ ጽሁፉ ለመዳሰስ የሚሞክረው በነጋዴነት የተመዘገበ የንግድ ፈቃድ የተሰጠው ሰው የንግድ ፈቃዱን ለሦስተኛ ወገን በኪራይ ውል ማስተላለፍ ህጋዊ መብት አለው ወይስ የለውም? የሚለውን ጭብጥ ነው፡፡

  15838 Hits