ያለዉክልና የሌላን ሰዉ እዳ መክፈል ይርጋን ያቋርጣል?

መግቢያ

ይህ አጭር ጽሁፍ በቅርብ ጊዜ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር መዝገብ ቁጥር 76248 ላይ፤ በኦሮሚያ ጠቅላይና በአዳማ ልዮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች መሰረታዊ የሕግ ስህተት ተሰርቷል ማለት አይቻልም በሚል፤ በሶስት ዳኞች ጥቅምት 6 2005 የተዘጋን ጉዳይ መሰረት አደርጎ የቀረበ ነዉ፡፡ የምንዳስሰዉ ጥያቄ በጽሁፉ ርእስ ላይ የተመለከተዉን ነዉ፤ ያለዉክልና የሌላን ሰዉ እዳ መክፈል ይርጋን ያቋርጣል? ለጽሁፉ አላማ የተከራካሪ ወገኖችን ስም መጥቀስ አስፈላጊ ስላልሆነ አበዳሪ፤ ከሳሽ፤ ተበዳሪ፤ እና የተበዳሪ ልጅ የሚሉትን እንጠቀማለን፡፡ በአጭሩ ፍርድ ቤቶቹ የወሰኑት ባለእዳዉ ሳይሆን ሌላ ሰዉ (የጽሁፍ ዉክልና ሳይሰጠዉ በፊት) በባለእዳዉ ስም ያደረገዉ የእዳ አከፋፈል እንዳልተደረገ ስለሚቆጠር ይርጋን አያቋርጥም በማለት ወስነዋል፡፡

የጉዳዩ መነሻ

ተበዳሪዋ ከኢትዮጲያ ንግድ ባንክ አዳማ ቅርንጫፍ ለንግድ ማስፋፊያ በሚልና ንብረት በማስያዝ በየወሩ ተከፍሎ በአንድ አመት ዉስጥ የሚያልቅ ብድር ወስደዋል፡፡ ነገር ግን አንድም ወር የተስማሙትን ወርሀዊ ክፍያ ሳይፈጽሙ በብድር ዉሉ ላይ የተጠቀሰዉ የእዳ መክፈያ ጊዜ ያልፋል፡፡ የብድር ዉሉ የተፈረመዉ በ25/11/1987 ሲሆን በ24/11/1988 ተከፍሎ ማለቅ ነበረበት፡፡ የተበዳሪዋ ልጅ የመጀመሪያዉን የ28000 ብር ክፍያ በተበዳሪዋ ስም የፈጸሙት በ24/11/1989 ነበር፡፡ ከዛ በመቀጠል በ15/8/1994 በዚሁ ልጅ በተዳሪዋ ስም የ2000 ብር ክፍያ ተፈጽሟል፡፡ ክሱ በቀረበበት ወቅት ከመጀመያዉ ክፍያ ጀምሮ ሲሰላ ከአስር አመት በላይ አልፎታል፡፡ ነገር ግን ከሁለተኛዉ ክፍያ ጀምሮ ከተሰላ አስር አመት አልሞላም፡፡

ተበዳሪዋ ለቀረበባቸዉ ክስ የይርጋ መቃወሚያ አንስተዋል፤ ክሱ በአስር አመት የይርጋ ጊዜ ዉስጥ ስላልቀረበ ይታገዳል በሚል፡፡ ሁለተኛዉን ክፍያ በተመለከተ፤ አልከፈልኩም በክፍያ ሰነዱም ላይ ያለዉ ፊርማ የኔ ፊርማ አይደለም ብለዋል፡፡ ይህንን እኔ ያልከፈልኩትን የሁለተኛ ክፍያ ሰነድ ያቀረበዉ ከሳሽ በይርጋ ቀሪ የሆነዉን የብድር ገንዘብ በፍርድ ቤት ክስ መስርቶ ለማስመለስ እንዲያመቸዉ ነዉ የሚል ነዉ፡፡  

Continue reading
  10855 Hits

FERQE - Agency and Arbitration Under Ethiopian Law

A principal-agent relationship is like a tripartite contract where the agent enters into any legal transaction on behalf of the principal. Art 2199 of the Civil Code defines agency as “a contract whereby a person, the agent, agrees with another person, the principal, to represent him and perform on his behalf one or several legally binding acts.” Such an authority can be conferred by court or by agreement of the parties.

If it is given by agreement of the parties, it can be either implied or express. The agent is expected to act in strictest good faith and diligently. He must avoid collusion with the third party to avoid conflict of interest. Art 2187(1) orders the cancellation of the agency contract if there is conflict of interest. The agent is accountable to the principal and must confine his/her acts with the scope of authority conferred. Art 2202(1) says that if the scope of the agency is not expressly known, it has to be fixed according to the nature of the transaction.

The scope of agency can be general (Art 2203 in conjunction with 2204) or special agency (Art 2205). An agent cannot sign bill of exchange, effect a settlement, invest capitals, alienate or mortgage real estate, make donations, bring/defend actions or sign arbitration agreement without special authority given to him/her.

For the services offered, the agent is entitled to contractual remuneration. Nevertheless, if remuneration is not stipulated in the contract, “the agent shall not be entitled to remuneration unless he carried out the agency within the scope of his professional duties or where such remuneration is customary” (Art 2220(1)).   

Needless to emphasize, the relation between the agent and the third party is based on the original contract between the principal and the agent. The main theme of this essay is not to talk about the agent-third party relation, but the principal-agent contractual agreement. It is unlikely that the principal-agent agreement will be signed without remuneration. Consequently, if the principal and the agent disagree on any matter, they can resolve their dispute by court litigation or arbitration.

Continue reading
  12983 Hits

የእንደራሴነት ሕግ (Agency Law) ዋና ዋና ነጥቦች

መግቢያ

 

ሰዎች ኑሮአቸውን ስኬታማ ለማድረግ በሚፈጽሙት የእለት ተእለት ተግባራቸው ከሌሎች የማህበረሰቡ ክፍሎች ጋር ዘርፈ ብዙ መስተጋብሮችን የሚፈጽሙ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ይሁንና እነኚህን መስተጋብሮች  በተለያዩ ምክኒያቶች በራሳቸው ለመፈጸም የማይችሉ በሆነ ጊዜ ሥራዎችን ሌላ ሰው እንዲያከናውንላቸው ፍላጎት ሊያድርባቸው እንደሚችል የሚያሻማ አይደለም፡፡

በዚሁ መሠረት ይህንኑ ሥራቸውን ማን፣ መቼ፣ በምን ሁኔታ እና በድካም ዋጋ ክፍያ ወይም ያለ ክፍያ  ሊሠራላቸው እንደሚገባ የመወሰን ነጻነት ሊኖራቸው የተገባ ነው፡፡  

ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ለማለት ባይቻልም አብዛኛው ስለ እንደራሴነት ወይም ውክልና ግንኙነት ጠቅለል ያለ መጠነኛ ግንዛቤ ይኑረው እንጂ በኢትዮጵያ ፍትሕ ሥርዓት ትግበራ መሣሪያ ከሆኑት ሕጎች አንዱ ስለሆነው የፍትሐብሔር ሕግ በልዩ ትኩረትም ስለ እንደራሴነት በቂ እና ጥልቅ ግንዛቤ ይኖረዋል ተብሎ ግምት አይወሰድም፡፡ በዚህም ምክንያት በሥራውም ሆነ በንብረቱ ላይ ሌሎችን ለመወከል የሚወስዳቸውን ጥንቃቄ  ለማወቅ፣ ያሉትን መብቶች እና ስለሚወክለው ሰውም ሆነ የተወከለው ሰው ከሦስተኛ ወገን ጋር ስለሚገባው ግዴታ ያሉበት ኃላፊነቶች ለይቶ ለማወቅ የሚቸገር በመሆኑ በጥቅሙ  እና በመብቱ ላይ ከፍ ያለ ጉዳት ሲደርስበት እንታዘባለን፡፡

Continue reading
  10889 Hits
Tags:

ስለ እንደራሴ (ውክልና) ሕግ አንዳንድ ነጥቦች

 

 ውክልናን የተመለከተው ሕግ በአገራችን በብዛት ስራ ላይ ከሚውሉ የሕግ ክፍሎች አንዱ ነው፡፡ የኢትዮጵያ የፍትህብሄር ሕግ ቁጥር 2199 ውክልናን እንደተረጐመው “ውክልና ማለት ተወካይ የተባለ አንድ ሰው ወካይ ለተባለው ሰው እንደራሴ ሆኖ አንድ ወይም ብዙ ህጋዊ ሥራዎች በወካዩ ሥም ለማከናወን ግዴታ የሚገባበት ውል ማለት ነው” ይላል፡፡ ከትርጉሙ ለመረዳት እንደምንችለው ውክልና የሚደረገው በወካይና በተወካይ መካከል ሲሆን በውክልናው የሚከናወኑት ስራዎች ህጋዊ መሆን አንዳለባቸው ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ ህጋዊ ባልሆኑ ነገሮች ላይ የሚደረግ ውክልና ተቀባይነት የለውም  ማለት ነው፡፡ በሰፊው ስንመለከት ሁለት አይነት ውክልናዎችን እናገኛለን፡፡ እነሱም በፍተሃብሄር ሕግ ቁጥር 2189 ላይ የተቀመጠው ፍፁም የሆነ እንደራሴነት /disclosed or complete  agency/ እና በዚሁ ሕግ ቁጥር 2197 ላይ የተቀመጠው እንደራሴው በራሱ ስም ተግባሮችን የሚፈፅምባቸው የውክልና አይነት/undisclosed agency/ ናቸው:: ለዚህ ፅሁፍ አላማ ግን  የመጀመሪያው አይነት ውክልና ማለትም ፍፁም የሆነውን የእንደራሴነት አይነት እንመለከታለን፡፡ ይህም በፍትሃብሄር ህጉ ቁጥር 2199-2233 ድረስ ያሉትን የህጉን አንቀጾች የተመለከተ ይሆናል፡፡ በአጠቃላይ በዚህ ፅሁፍ ውስጥየውክልና አስፈላጊነት፣ የውክልና ምንጮች ፣ የውክልና አመሰራረት፣ የውክልና አይነቶች፣ የውክልና ግብ ፣ የተወካይና የወካይ ግዴታዎች፣ ውክልና የሚቋረጥበት ሁኔታ፣ ከውክልና መመሰረት ጀምሮ በውክልና አማካኝነት የሚከናወኑ ተግባሮችና ውጤቶቻቸው ድረስ ወካይ፣ ተወካይና የውክልና ማስረጃውን የሚሰጡ አካሎች ሊያደርጓቸው የሚገባቸው ጥንቃቄዎች የሚዳሰሱ ይሆናል፡፡

 

1.  ውክልና ለምን ያስፈልጋል?

አንድ ሰው አንዳንድ ተግባሮችን በራሱ ከማድረግ ይልቅ ሌላን ሰው በመወከል ተግባሮቹ እንዲከናወኑለት ይፈልጋል፡፡ ለዚህም ምክንያቱ የጊዜ ጥበት፣ የቦታ ርቀት ወይም የሁኔታዎች አለመመቻቸት፣ የእውቀት ወይም የክህሎት አለመኖርና የችሎታ ማነስ ዋናዋናዎቹ ሲሆኑ ሌሎችም በምክንያትነት ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡ 

Continue reading
  27963 Hits
Tags: