የቴምብር ቀረጥ የሚከፈልባቸውና የማይከፈልባቸው ግብይቶች

 

መንግሥት ገቢ ከሚሰበሰብባቸው ምንጮች መካከል የቴምብር ቀረጥ አንዱ ነው፡፡ የቴምብር ቀረጥ ቀጥተኛ ያልሆነ ታክስ ሲሆን፣ የሚሰበሰበውም በተወሰኑ ሰነዶች ላይ እንዲለጠፍ ወይም እንዲከፈል በማድረግ ነው፡፡

በአገራችን የቴምብር ቀረጥ የተጣለው ስለ ቴምብር ቀረጥ አከፋፈል በወጣው አዋጅ ቁጥር 110/90 መሠረት ነው፡፡ የዚህ አዋጅ አፈጻጸም በተለያዩ ባለድርሻ አካላት መካከል ያለው አሠራር ተመሳሳይ አይደለም፡፡ በተግባር በሰነዶች የተለያዩ ግብይቶች (Transactions) የሚፈጸሙ ሰዎች፣ የአገር ውስጥ ገቢ ሠራተኞች፣ ባንኮች፣ ፍርድ ቤቶች ወዘተ የየራሳቸው የአዋጁ አረዳድ አላቸው፡፡ የልዩነቱ ምንጭ አዋጁን ካለማወቅ፣ ከአዋጁ ድንጋጌዎች ይልቅ በልማድ መሥራት፣ እንዲሁም የአዋጁን ክፍተት የሚሟሉ መመርያዎችን አለማወቅ እንደሆነ የተለያዩ ጥናቶች አመልክተዋል፡፡ እነዚህን ችግሮች በመቅረፍ የአዋጁ አፈጻጸም የሕግ አውጪውን መንፈስ እንዲከተል ማስቻል የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ነው፡፡

የቴምብር ቀረጥ የሚከፈልባቸው ሰነዶች

የቴምብር ቀረጥ በሰነዶች ላይ የሚጣል ታክስ ቢሆንም፣ ሁሉም ሰነዶች ላይ የሚጣል አይደለም፡፡ አዋጁ በአንቀጽ 3/12 የተለያዩ ሰነዶችን በመዘርዘር የሚከፈሉበትን ጊዜ፣ ሁኔታና መጠን በግልጽ አመልክቷል፡፡ የአዋጁ ዝርዝር ምሉዕ (Exhaustive) በመሆኑ በማመሳሰል ሌሎች ያልተጠቀሱ (ያልተዘረዘሩ) ሰነዶች ላይ የቴምብር ቀረጥ እንዲለጠፍ ወይም እንዲከፈል መጠየቅ አይቻልም፡፡ የቀረጥ ቴምብር የሚከፈለው በመመሥረቻና መተዳደሪያ ደንብ፣ የግልግል ሰነድ፣ ማገቻ፣ የዕቃ ማከማቻ ማረጋገጫ ሰነድ፣ ውል፣ ስምምነትና የእነዚህ መግለጫ፣ የመያዣ ሰነዶች፣ የኅብረት ስምምነት፣ የሥራ (ቅጥር) ውል፣ የኪራይ፣ የተከራይ አከራይና መሰል መብት የማስተላለፊያ ሰነዶች፣ ማረጋገጫ፣ የውክልና ሥልጣንና የንብረት ባለቤትነትን ማስመዝገቢያ ሰነድ ላይ ነው፡፡ ከእነዚህ ሰነዶች ውጭ ባሉ ሰነዶች ላይ የቴምብር ቀረጥ አይከፈልም፡፡

Continue reading
  16917 Hits
Tags: