የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት ለረጅም ጊዜ በተለያዩ የኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ አተሰሳሰቦች የነበረ፤ ያለ እና የሚኖር መስተጋብር ነው፡፡ ታሪኩንም በወፍ በረር መለስ አድርገን ስንመለከት ከካፒታሊስታዊ ሥርዓተ ማኅበር በፊት በነበሩት ሥርዓቶች በተለይም በባሪያ አሳዳሪ /slave-owning/ ሥርዓተ ማኅበር እና በፊውዳል /feudal system/ ሥርዓተ ማኅበር ወቅት ይሰተዋል የነበረው ሠራተኛው እንደ ጪሰኛ የሚቆጠርበት ሥርዓት ነበር፤ የሚያገኘው ጥቅምም ከአሠሪው ምግብ እና መጠለያ እንጂ መደበኛ ደምወዝ አልነበረውም፡፡
Copyright © 2024 Abyssinia Law | Making Law Accessible! . All Rights Reserved.
Maintained by Liku Worku Legal Service.