በኢትዮጵያ አሠሪና ሠራተኛ ሕግ የሥራ ስንብት ክፍያ ምንነትና የሚስተዋሉ አንዳንድ ችግሮች

የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት ለረጅም ጊዜ በተለያዩ የኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ አተሰሳሰቦች የነበረ፤ ያለ እና የሚኖር መስተጋብር ነው፡፡ ታሪኩንም በወፍ በረር መለስ አድርገን ስንመለከት ከካፒታሊስታዊ ሥርዓተ ማኅበር በፊት በነበሩት ሥርዓቶች በተለይም በባሪያ አሳዳሪ /slave-owning/ ሥርዓተ ማኅበር እና በፊውዳል /feudal system/ ሥርዓተ ማኅበር ወቅት ይሰተዋል የነበረው ሠራተኛው እንደ ጪሰኛ የሚቆጠርበት ሥርዓት ነበር፤ የሚያገኘው ጥቅምም ከአሠሪው ምግብ እና መጠለያ እንጂ መደበኛ ደምወዝ አልነበረውም፡፡

  46541 Hits