በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ፈቃድ አስጣጥ በአንድ መስኮት አገልግሎት መሆን መልካም አጋጣሚዎች እና ፈተናው

መግቢያ

ኢንቨስትመንት ቃሉ እንግሊዝኛ ሲሆን አሁን አሁን ግን በአማርኛ ሥነ ጽሑፍም በጣም እየተለመደ በመምጣቱ የአማርኛውን አቻ ቃል ማለትም “ምዋዕለ-ንዋይ” የሚለው መጠሪያ እስከሚዘነጋ ድረስ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን በየእለቱ ይነገራል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት አዋጅ ቁ.769/2005 ሳይቀር መዋዕለ ንዋይ ከማለት ይልቅ ኢንቨስትመንት የሚለውን ቃል ሙሉ በሙል ተጠቅሟል፤ ስለዚህ በዚህ ረገድ አንባቢውን ግራ ላለማጋባት ሲባል ጸሐፊው ኢንቨስትመንት የሚለውን ቃል ለመጠቀም ተገዷል፡፡ የዚህ ጹሑፍ ዓለማ ለምን ምዋዕለ-ንዋይ የሚለው ቃል ኢንቨስትመንት እየተባለ ተጠራ የሚለው ጉዳይ ባይሆንም አገር በቀል መጠሪያዎችን መጠቀም እንድንለምድና እንድናዳብር አስተያየት ለመጠቆም ነው፡፡

የአንድ ሃገር ለውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ተፈለጊ እና ሳቢ የሚያደርጋት የዘረጋችው ሃገራዊ ምቹ የኢንቨስትመንት ፖሊሲ ነው፡፡ ሆኖም ግን ምቹ የሕግ እና የፖሊሲ ማዕቀፍ መኖሩ ብቻ ፍሰቱን እንዲጨምር ላያደርግ ይችላል፡፡ ለምን ቢባል በተግባር የወጡት ፖሊሲዎች እና ሕጎች በአስፈጻሚው አካል ዘንድ የመተግበራቸው ሁኔታ ስለሚያጠያይቅ ጭምር ነው፡፡ እነዚህ አስተዳደራዊ ሥነ ሥርዓቶች ነጻ የኢንቨስትመንት ፈቃድ በሰጡ አገራት ጭምር ከፍተኛ ስጋት ያጭራሉ፡፡ በብዙ ሃገራትም በርካታ ኢንቬስተሮች የሚያቀርቡት ስሞታ እና እሮሮ በተለይም አሰልቺ ከሆኑ አሰራሮች (hectic bureaucracy) መኖር ጋር ይያያዛል፡፡

እርግጥ ነው ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ጥሩ የሕዝብ ግንኙነት  ወይም የገበያ ጥናት ባለሙያዎች መኖራቸው መልካም ተግባር ነው፡፡ በተለየም ቢዝነስ ተኮር የሕዝብ ዲፕሎማሲ በዚህ ረገድ ተጠቃሽ ተግባር ነው፡፡ ታዲያ በዚህ የማስተዋዋቅ ተግባር የተመሰጡ የውጭ ኢንቬስተሮች የተባለችውን አገር ሄዶ ሁኔታውን ለማየት ከመቼው ጊዜ ልባቸው ይነሳል፡፡ በዚህ ጊዜ ታዲያ የሚሄዱበት አገር አስተዳደራዊ ችግር በስፋት የሚታይበት ከሆነ ኢንቬስተሩ አስቀድሞ ስለሁኔታው ሊወስን ይችላል፡፡ ለአብነት ያህልም ኢንቬስተሩ/ሯ ወደ ተባለው አገር ለማምራት ቪዛ ተይቀው በጣም አሰልቺ ነገር ቢገጥማቸው ከራስ ተሞክሮ ውሳኔ ሊዎስኑ ይችላሉ፡፡ (ፍራንክ ሳደር፡እኤአ 2003፡2)

የተባለውን እሰቸጋሪ ውጣ ውረድ አልፈውም ወደ አገር ቤት ሲገቡ ከሌሎች ቀደምት ኢንቨስተሮች ተሞክሮ በመውሰድ ሊያውጡ የሚችሉትን ወጪ፣ መዘግየት፣ የመንግስት ምላሽ እና ለችግሮች የሚሰጠውን መልስ ከግምት በማስገባት አስቀድመው ትረፍና ኪሳራ (cost-benefit analysis) በመስራት የተባለው አስተዳደራዊ ችግር ይኖራል ብለው ካመኑ ልክ እንደ ሌሎች ተጎጂ ላለመሆን ባመጣቸው እግር ወደ መጡበት አገር ይመለሳሉ፡፡

ሌላው ጉዳይ ፈቃድ ሰጭው አካል የቀረበለትን ማመልከቻ ቶሎ መልስ ካልሰጠበት፣ ግለጸኝነት የሚጎድለው ከሆነ እና በጣም ሰፊ የሆነ ፈቅደ ስልጣን (discretionary power) ሚስተዋል ከሆነ ለሌላ ብልሹ አሰራር ማለትም ጉዳይን በቶሎ ከፍሎ ማስፈጸም (practice of “speed payments”) ተግባር አምርቶ ኢንቨስተሮች ፈቃድ ለማግ ኘት ሲሉ መደለያ እና ማግባቢያ ገንዘብ ለነቀዙ ባለስልጣናት ወይም ወኪሎች እንዲከፍሉ ሊገደዱ ይችላል፡፡

Continue reading
  20753 Hits

The New Investment Proclamation No. 1180/2020: A Brief Overview

 

One part of the economic reform programs taking place in Ethiopia is improving the country's ranking in the World Bank's Ease of Doing Business. As part of the Ease of Doing Business Project, the Ethiopian Investment Commission (EIC) has taken the responsibility of revising the investment proclamation, which was in effect since 2012. After a number of consultations with the private sector representatives and the development community, the final draft has been presented to the House of Peoples' Representatives (HPR) in January 2020 and got approved by the House. After the approval, the law-making process necessitated for it to get publicized in the Federal Negarit Gazette to enter into effect. Accordingly, the new investment proclamation, cited as "Investment Proclamation No. 1180/2020" got publicized on April 2, 2020, officially repealing the long-lasted Investment Proclamation No. 769/2012 as amended from time to time.

 

Following this the Council of Ministers is expected to enact the Investment Regulation, which mainly puts the new proclamation to the ground. The Proclamation more of sets the high-level policy and institutional arrangements in relation to investment.

 

Continue reading
  14949 Hits