አትሌቶች፣ ዶፒንግና ግልግል (arbitration)

 

ማሪዮን ጆንስ፣ ማሪያ ሻራፖቫ፣ ክላውዲያ ፔከንስታይ እና ላንስ አርምስትሮንግን የሚያመሳስላቸው አንዱ በስፖርቱ ዓለም ገናና ስም የነበራቸው መሆኑ ነው፡፡ ማሪዮን ጆንስ የኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ ናት፡፡ አርምስትሮንግ ደግሞ በብስክሌት ግልቢያ የሚያህለው አልነበረም፡፡

ማሪዮን ጆንስ አጭሩን ርቀት በሚያስገርም ፍጥነት ታጠናቅቅ ነበር፡፡ የአሸናፊነት ምልክትም ሆና ለብዙ ዘመን ቆይታለች፡፡ አርምስትሮንግም እንዲሁ፡፡ ከችሎታውና ብቃቱ የተነሳ ስፖንሰሩ ለመሆን ያልተሯሯጠ ኩባንያ አልነበረም፡፡

በአንደኝነት ያላጠናቀቀበት ውድድርም ማግኘት አዳጋች ነበር፡፡ ‹‹ቱር ደ ፍራንስ›› በመባል የሚጠራውን የብስክሌት ውድድር ብዙ ጊዜ አሸንፏል፡፡ በብር ላይ ብር፣ በክብር ላይ ክብር ደርቧል፡፡ እሱ ካለው ዝና የተነሳ የካንሰር ታማሚዎችን የሚደግፈው ‹‹ሊቭ ስትሮንግ›› የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅቱም በርካታ ሚሊዮን ዶላሮች ይጎርፉለት ነበር፡፡ ከእርሱ ጋር መሥራት ‹‹ኩራታችን›› ነው ያሉ ድርጅቶችም ብዙ ነበሩ፡፡ የ44 ዓመቷ ክላውዲያ ፔከንስታይ የበረዶ ላይ መንሸራተት ስፖርተኛ ናት፡፡ ገድሏ እንደሚተርከው ባደረገቻቸው ዓለም ዓቀፍ ውድድሮች 60 ሜዳሊያዎችን አሸንፋለች፡፡

ፍጻሜው

Continue reading
  11536 Hits